uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 335 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 641-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 191-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 335 obunachiga ega bo‘ldi.

14 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -76 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.40% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.40% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 435 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 595 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 25 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 15 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 335
Obunachilar
-124 soatlar
-67 kunlar
-7630 kunlar
Postlar arxiv
በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ #አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ #አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ሥርዐተ_ከተራ ፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡ ፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤ *ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡ *የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤ *መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡ *እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡ *ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡ *የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ *ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡ **ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡ ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡ የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡ #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤ #ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ #ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ #ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ #ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ #ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/ #ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡ ትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡ #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤ #ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ #ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ #ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ #ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ #ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/ #ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/

#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ? #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ) #ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡ #ከተራ_ለምን_ተባለ? በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ #አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ #አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ሥርዐተ_ከተራ ፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡ ፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤ *ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡ *የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤ *መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡ *እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡ *ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡ *የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ *ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡ **ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡ ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡ የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለ#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ? #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ) #ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡ #ከተራ_ለምን_ተባለ? በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ

#የጥምቀት_በዓል_አከባበር_በአዲስ_አበባ_ከእንጦጦ_ጋራ_ጥግ_እስከ_ጃንሆይ_ሜዳ_ በአዲስ በአበባ ያሉ ገዳማትና አድባራትም በቦታ ርቀት እስከ ተለያዩበት ቀን ድረስ በእንጦጦ ጋራ ጥግ በአንድ ላይ በመፈናኘት ያድሩ ነበር፤ ኋላ ከቦታ ርቀት በኋላ የተቀሩት በጃንሆይ ሜዳ ማደር ጀምረዋል፡፡ እያደረም ሌሎች ገዳማትና አድባራት ሲመሠረቱ ከጃንሆይ ሜዳ በተጨማሪ ለአጥቢያቸው በሚቀርብ ቦታ ማደር ጀመሩ፡፡ ፠ በዓለ ጥምቀት በጃን ሜዳ (ጃንሆይ ሜዳ) መከበር የጀመረው ከ1887 ዓ.ም. አንስቶ መሆኑ ይነገራል፡፡ ስያሜውምና አጀማመሩም ጃንሜዳ የሚለው ጃን፥ ጃኖ ከሚለው ጋራ የተዛመደ ሲሆን ነገሥታት ለመሾም ለመሻር፣ ዳኝነት ለመስጠት፣ ሊቃውንትን ለመሾምና፣ ዐዋጅ ሲያስነግሩ በቤተ መንግሥታቸው አቅራቢያ በሚገኝ ሜዳ ላይ የጃኖ ድንኳን ተክለው ያስነግራሉ፤ ይህም ሜዳ ከጃኖ ጋራ እየተናበበ የቦታ መጠሪያ ሁኗል፡፡ ለምሳሌ፤ ‹‹ጃን ተከል›› በጎንደር ነገሥታት፤ ‹‹ጃን መራቂ›› በላስታ ነገሥታት፤ ‹‹ጃን ተራራ›› በአማራ ሳይንት በአፄ በዕደ ማርያም ‹‹ጃን ሜዳ›› በደብረ ታቦርና በአዲስ አበባ ናቸው፡፡ ፠ አዲስ አበባ መዲና በሆነችበት ሰዓት ‹‹መሐል ሰፋሪ‹‹ የሚባሉ የመኳንንት ጕባኤ በዚሁ በጃንሜዳ በስውር ዐድማ የሚያደርጉበት ሆነ አድማውን ሲያደርጉም በጃን ሜዳ ያለው የጃኖው ድነኳን ከሩቅ እንዳይታይ በማቅ ይሸፈን ነበር፡፡ እቴጌ ጣይቱ ይህን የመሰለ ሜዳ የክፉ ምክር መምከሪያ ሆኖ ከሚኖር ተባርኮ ለጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቢሆን ብለው ለአፄ ምኒልክ ሃሳብ አቀረቡላቸው፤ አፄ ምኒሊክም ማለፊያ ብለው ሐሳባቸውን በመቀበል ጃን ሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ እንዲሆን አዘዙ፡፡ እንዲሁም የአፄ ምንሊክ አልጋ ወራሻቸው ልጅ ኢያሱ መሆኑን በግንቦት 10 ቀን 1901ዓ.ም. ዐዋጅ ያስነገሩበት፤ ‹‹ንሥረ ተፈሪ›› የተባለው የመጀመሪያው አውሮፕላንም በ12921ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ያረፈውም በዚሁ ሜዳ በመሆኑ ጭምር ስያሜው ጃንሆይ ሜዳ ተባለ፡፡ ፠ በ1887ዓ.ም. በዓለ ጥምቀትን ለመጀመሪያ ጊዜ በጃን ሜዳ በሕብረት ያከበሩት የመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን፣ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነበሩ፡፡ ፠ እስከ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ መን ድረስ ግን ታቦታቱ ወደ ቀበና ወንዝ (አፈ ንጉሥ ጥላሁን ሰፈር፤ ከፈረንሳይ ኤምባሲ በታች) ከከተራው አንስቶ አድረው በጥምቀት ዕለት ወደ ጃንሜዳ ይመለሱ ነበር፡፡ ሌሎችም በየሰበካቸው በሚገኝ አምች ቦታ ሲያከብሩ ቆይተው በ1939ዓ.ም. ከንሜዳ እጅግ በጣም ብዙ ያልራቁት (የካ ሚካኤልና ቅዱስ ዑራኤል) በንጉሠ ነገሥቱ ጥሪ ተደርጎ ወደ ጃናሜዳ እንዲመጡ ተደርጎ ነበር፤ ሆኖም ሕዝብ እየበዛ ስላስቸገረ በየአቅራቢያቸው እንዲያድሩ ተድርጓል፡፡ ፠ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኀይለ ሥላሴ በ1936 ዓ.ም በስፍራው የውኃ ቧንቧ እንዲዘረጋ፣ ባሕረ ጥምቀት ገንዳ በግንብ እንዲሰራ፣ የኤሌክትረክ መብራት በቦታው እንዲገባ አድርገዋል፡፡ ዙሪያውን በግንብ ተሰርቶ በቧንቧ የብረት ማገር ውብ ሆኖ እንዲታጠርና በዐፀድና በአበባዎች እንዲያጌጥ አድርገዋል፡፡ ይህ ቦታ ኋላ በ1994ዓ.ም. እድሳት ተደርጎለታል፡፡ ፠ እስከ ቅርብ ጊዜያትም ድረስ ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱ ታቦታት ከነድርባቸው ነበር፤ ለምሳሌ ቀቀጨኔ ደብረ ሰላም ከቅዱስ ገብርኤል ጋራ ነበረ፤ ኋላ ግን ድርብ ታቦታት ቀርተው ዋናውን ይዘው የሚወርዱ ሆኗል፡፡ በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ውስጥ እስከ 2010ዓ.ም ድረስ ….. ባሕረ ጥምቀት (አብሕርተ አጥማቃት) አሉ፡፡ ፠ እስከ 1958ዓ.ም. በምስካየ ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ማኅበርና በጠቅላይ ቤተ ክህነት የታሪክ ድርሰትና ስብከት ክፍል አስተባባሪነት ከኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. ሐዋርያዊ ድርጅት፣ ከሊቃውንትና ከመምህራን፣ ከሰዋስወ ብርሃንና ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በተውጣጡ መምህራን በባሕረ ጥምቀቱ የስብከተ ወንጌልና፣ የመዝሙርና የድራማ መርሐ ግብር ያቀርቡ ነበር፡፡ በ1959ዓ.ም. አካባቢ ጥቂት ሰንበት ት/ቤቶች የደንብ ልብስና ነጠላ በማድረግ ታቦታቱን አጅበው አውጥውና አጅበው በመመለስ የበዓሉ ድምቀት እየሆኑ መጡ፡፡ በአሁኑ ወቅት በጃንሜዳ የሚያድሩ ታቦታት 12 ናቸው እነርሱም፤ 1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤ 2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤ 3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ 4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤ 5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው) 6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤ 8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤ 9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤ 10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤ 11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ 12ኛ.  ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot2719

ብፁዕ አቡነ ሣዊሮስ የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ
+7
ብፁዕ አቡነ ሣዊሮስ   የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ንብረዕድ ኤልያስ አብርሃ በመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ መላከ ምህረት ቆሞስ  አባ ገብረመድህን ንጉሴ የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅን ጨምሮ ሌሎች የቤተክህነቱ እና የሀገረ ስብከቱ .ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች በተገኙበት የጃንሜዳ ጥምቀተ ባህር እና አጠቃላይ የስራው ሁኔታ ጉብኝት ተደረገ። በጉብኝቱ  ወቅት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ቀሪ ስራዎች በመጠናቀቃቸው መደሰታቸውን ገልፀው የዘንድሮው የጥምቀት በዓል ተረኛ አዘጋጅ የሆነውን የቀጨኔ ደብረሠላም መድኀኔያለም እና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የስራ ሀላፊዎችን አመስግነዋል። በ2018 ዓ.ም ተረኛ አዘጋጅ  የሆነው የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉሀን ቅዱስ ገብርኤል አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሠላም  ዓምደወርቅ ደሴ ደብራቸው ለበዓሉ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጸው፤ በዓሉ የሠላም እና የፍቅር እንዲሆን ተመኝተዋል ።

#ጥምቀት_በኢትዮጵያ፤ ፠ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠመቀው የንግሥት ሕንደኬ በጅሮንድ አቤላክ(ባኮስ) ‹‹እነሆ ውኃ አለ፣ ታድያ መጠመቅን ማን ይከለክለኛል?›› /የሐዋ. ፷፥፳፱-፴፮/ ብሎ በሐዋርያው ፊልጶስ በተጠመቀ ጊዜ ነው፡፡ ይህ ሥርዐት ግን ተስፋፍቶ የቀጠለው በነገሥታቱ በአብርሃ ወአጽብሐ (315-351ዓ.ም.) የቤተ መንግሥቱ ጃንደረባ በነበረውና ኋላ ጳጳስ በሆነው በፍሬምናጦስ(አባ ሰላማ) ዘመን ነው፡፡ በዓሉ ግን አሁን በምናከብረው ዓይነት ስዕላዊ በሆነ መልኩ መከበር የጀመረው ከማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድ ዜማ መስፋፋት ጋራ በአፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (530-544ዓ.ም.) እንደሆነ ይነገራል፡፡ ፠ ገዳማቱና አድባራቱም በአቅራቢያቸው ወደሚገኙ የውኃ ምንጮች በተናጥል በመውረድ በዓለ ጥምቀትን ያከብሩ ነበር፡፡ ተቀራርበው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያሳድሩ ዐዋጅ የታወጀው፥ ትእዛዝ የተላለፈው በጻድቁና በጠቢቡ ንጉሥ ላልይብላ(1140-1180ዓ.ም.) ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ በዚሁ ዘመን የነበሩት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአኵሱም በመቀለና በመርጡለ ማርያም ያሉ ጥምቀተ ባሕሮችን ባርከዋል፤ በአፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን ደግሞ በአቡነ ተክለሃይማኖት አሳሳቢነት ሥርዐተ ጥምቀቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዐዋጅ ታውጇል፡፡ እስከ አጼ ዘርዐ ያዕቆብ ድረስም ታቦታቱ ዕለቱን ጠዋት ወጥተው ማታ መለሱ ነበር፤ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ግን ታቦታቱ በዋዜማው ጥር 10 ከሰዐት በኋላ ወደ ትምቀተ ባሕር ወርደው እንዲያድሩ፤ አገሩንም በኪደተ እግር እንዲባርኩ፤ በሄዱበት መንገድም እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡ ቀጥሎም አፄ ናዖድ ሕዝቡ ታቦታቱን አጅቦ ወደ ጥምቀተ ባሕር እንዲሄድ በዐዋጅ አስነገሩ፡፡ ይህ ሥርዐትም እስካሁን ከኛ ዘንድ ደርሷል፡፡ በዘመናት ውስጥም የጥምቀት በዓል ሲከበርባቸው ከነበሩ ቦታዎች ዐበይቶቹን ለመጥቀስ ያህል፤ #በአኵሱም_የንግሥተ_ሳባ_መዋኛ_ ‹‹#ማይ_ሹም›› #በጎንደር_የአፄ_ፋሲል_መዋኛ_ገንዳ #በቅዱስ_ላሊበላ_የዮርዳኖስ_ወንዝ #በሸዋ_የአፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_ፍርድ_መስጫ_አደባባይ #44ት #ታቦታት_የሚያድሩበት_የሸንኮራ_ሜዳ ‹‹#ኢራንቡቴ_ጥምቀተ_ባሕር›› #በአዲስ_አበባ_የጃንሆይ_ሜዳ_ (ጃንሜዳ) #በአዲስ_አበባ_የእንጦጦ_ማርያምና_ቅዱስ_ራጕኤል_ታቦት_ማደሪያ  #ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ ዐበይቶቹ ናቸው፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot 

(‹‹የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦትን ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡›› ኢያሱ ፫፥፫) #ጥምቀትን_በአዲስ_አበባ__በየትኛው_ጥምቀተ_ባሕር_ያከብራሉ_፤ #በአዲስ_አበባ_በ10ሩም #ክፍለ_ከተሞች_የሚገኙ #76ት #የጥምቀተ_ባሕር_ቦታዎችና_ወደ_ጥምቀተ_ባሕሩ_የሚወርዱትን_179 #ገዳማትና_አድባራት_እነሆ_ጽፈንላችኋል፡፡ (እኛ በአ.አ. ከሚገኙ 76ት ጥምቀት ባሕር መካከል፤ ብዙ ታቦታት የሚወርዱበትን የጃንሜዳን ፎቶ ለጥፈንላችኋል፤ እናንተም በየአካባቢያችሁ ያሉትን በ‹ኮሜንት› መጻፊያ ላይ ለጥፉልን፡፡)       #share ፠ ፠ ፠ #በአራዳና_ጉለሌ_ክፍለ_ከተማ_ (7ት ጥምቀተ ባሕር) #፩ኛ) #በጃንሆይ_ሜዳ_ (በጃንሜዳ)፤ /በአዲስ አበባ ትልቁና የ12 አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት የሚያድሩበት) 1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤ 2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤ 3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ 4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤ 5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው) 6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤ 8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤ 9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤ 10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤ 11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ 12ኛ.  ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡ #፪ኛ) #እንጦጦ_ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ 1ኛ. እንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤ.ክ. 2ኛ. እንጦጦ ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም #፫ኛ) #ሽሮ_ሜዳ_ወረዳ_01 ፥ #ቀበሌ_02_ 1ኛ. ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ #፬ኛ) #አዲሱ_ገበያ_ 1ኛ. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ 2ኛ. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለሃይማኖት 3ኛ. ድል በር መድኃኔዓለም #፭ኛ) #ወረዳ_3ና_4 (19 ቀበሌ) 1ኛ. መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም #፮ኛ) #ሸጎሌ_መንገድ_ 1ኛ. ጉለሌ(ሸጎሌ) ቅድስት ኪዳነ ምሕረት #፯ኛ) #ወረዳ_7_ቀበሌ_15(ቤልኤር፤ ኳስ ሜዳ) 1ኛ. ቀበና ምሥራቀ ፀሐይ መድኀኔ ዓለም ፠ ፠ ፠ #በየካ_ክፍለ_ከተማ_ (14ት ጥምቀተ ባሕር) #፰ኛ) #ወረዳ_8(22 አካባቢ፤ ባልደራስ አጠገብ) 1ኛ. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል 3ኛ. ቀበና ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ኪዳነ ምሕረት #፱ኛ) #ወንድይራድ_ትምህርት_ቤት_አካባቢ_(ኮተቤ) 1ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ኮተቤ (ኋላ ሲ.ኤም.ሲ.) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል 3ኛ. መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና 4ኛ. ሲ.ኤም.ሲ. አቡነ ተክለ ሃይማኖት 5ኛ. ደብረ አራራት ቅዱስ አማኑኤል 6ኛ. ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ 7ኛ. ኮተቤ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲ኛ) #ዋሻ_ተክለ_ሃይማኖት_ጠበል_ቦታ 1ኛ. ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. አንቆርጫ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል #፲፩ኛ) #በግ_ተራ 1ኛ. ኮተቤ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት #፲፪ኛ) #ላምበረት_ቤተ_ክርስቲያኑ_አካባቢ 1ኛ. ላምበረት ደብረ ፀሐይ አቡነ አረጋዊ #፲፫ኛ) #ጉራራ_አካባቢ 1ኛ. ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲፬ኛ) #ወረዳ_10 #ከጉራራ_ከፍ_ብሎ_ፖሊስ_ሴንተር_አጠገብ 1ኛ. ደብረ መድሐኒት ዳንሴ መድኀኔዓለም 2ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል #፲፬ኛ) #ሎቄ_ቤተ_ክርስቲያን_አካባቢ 1ኛ. ሎቄ መ.ጸ. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፲፭ኛ) #ኬንያ_ኤምባሲ_ጀርባ_(በግ ተራ) 1ኛ. ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም #፲፮ኛ) #መሪ_አደባባይ 1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ 2ኛ. መሪ ደብረ ታቦር ቅዱስ ፋኑኤል #፲፯ኛ) #አባዶና_ካራ_አሎ_አርሴማ_ጠበል_አካባቢ_(ገበያው መሐል) 1ኛ. ካራ አሎ ደብረ ቀርሜሎስ መድኀኔ ዓለምና አቡነ ገሪማ 2ኛ. ካራ አሎ ቅድስት ሥላሴ 3ኛ. አባዶ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ 4ኛ. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፲፰ኛ) #አባዶ_አካባቢ 1ኛ. አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል #፲፱ኛ) #አያት_አካባቢ 1ኛ. ጣፎ መ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አያት ደ/ክ ቅድስት ማርያም #፳ኛ) #አባዶ_ኮንዶሚንየም 1ኛ. አባዶ ጽርሐ አርያም ቅድስት ማርያም 2ኛ) ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ) ደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ 4ኛ) ደብረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም 5ኛ) አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 6ኛ. ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ 7ኛ. ኢያሪኮ ቅዱስ ገብርኤል ፠ ፠ ፠ #ልደታ_አዲስ_ከተማና_ቂርቆስ_ክፍላተ_ከተማ_ (5ት ጥምቀተ ባሕር) #፳፩ኛ) #ቂርቆስ_አካባቢ 1ኛ. ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ #፳፪ኛ) #ኦሎምፒያ_ቦሌ_ማተሚያ_ቤት_አካባቢ 1ኛ. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ 2ኛ. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ #፳፫ኛ) #ልደታ_ክፍለ_ከተማ_ሜትሮሎጂ_ጀርባ 1ኛ. ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ጎላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ቅዱስ ሚካኤል #፳፬ኛ) #ሳር_ቤት_ኮንዶሚንየም 1ኛ. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም #፳፭ኛ) #ቄራ_አካባቢ 1ኛ. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ፠ ፠ ፠ #ኮልፌ_ቀራንዮ_ክፍለ_ከተማ_(9ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፳፮ኛ) #መድኀኔ_ዓለም_ከፍተኛ_መሠናዶ_ትምህርት_ቤት_(ራስ ኀይሉ ሜዳ) 1ኛ. መርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል 2ኛ. ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል 4ኛ. ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ 5ኛ. ጠሮ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ #፳፯ኛ) #ሳንሱሲ_መናፈሻ_አጠገብ 1ኛ. አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አስኮ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 4ኛ. ፍኖተ ሎዛ ብርጭቆ ማርያም #፳፰ኛ) #ወረዳ_15_(አርሴማ ጠበል /አወልያ ትምህርት ቤት ጋር/) 1ኛ. ቃሎ ተራራ አቡነ ሀብተ ማርያም #፳፱ኛ) #ገዳመ_ኢየሱስ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅጽር_ግቢ_ውስጥ 1ኛ. ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ 3ኛ. ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ 4ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም 5ኛ. ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 6ኛ. መርካቶ ደብረ ገሊላ አማኑኤል 7ኛ. ገዳመ ኢየሱስ #፴ኛ) #ወረዳ_5_ #ጻድቃኔ_አካባቢ_ታቦት_ማደርያ 1ኛ. ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ገብረ ክርስቶስ 2ኛ. ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ

#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት፡፡ ✤✤✤✤✤ “ኑ ፥እንውረድ ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማ ቋንቋቸውን እንደባልቅባችው።” ዘፍ 11፥7 #በባቢሎን የነበሩት በሰናዖር ሰፊ ሜዳ አግኝተው ‹ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ› አገር እናቅና እስከ ሰማይ የመሚደርስ ግንብ እንስራ ተባባሉ ፤ማይ አይኀ በወረደ ጊዜ እንዳያጠፋን የምንጠጋበት ግንብ እንስራ  ብለው ሥራ ጀመሩ ፤ አንድም ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እርሱን ገለን ሞትንም እናጠፋለን ሲሉ፡፡ ✤ይህንን ግንብ #43 ዓመት ሰርተውታል ቁመቱም  #5433 ከ2 ስንዝር ነው፤ በፀሐይም እያበሰሉ ይበሉ ጀምረው ነበር   ፡፡ ✤ከዚያም ሆነው ጦር እየሰበቁ ይወረውሩ ጀመር ሰይጣን ከደመና በምትሀት ደም እየቀባ ይልክላቸዋል እነርሱም ደሙን እያዩ ‹‹ አሁን አብን ወጋነው አሁን ወልድን ወጋነው ….›› ይሉ ጀመር እግዚአብሔርም የሰናዖርን ግንብ ይጥልባችው ዝንድ ‹‹ንዑ ንረድ ወንዝርዎ ✤ ከመ ኢይሳምዑ   ነገሮሙ አሐዱ ምስለ ካልኡ፤›› አሉ   የአንዱን ቋንቋ አንዱ እንዳይሰማው ወርደን ቋንቋቸውን እንለያየው ፡፡ ሥላሴ ፍጥረት ሁሉ ቢጎዳ አይወዱምና #72_ቋንቋ አመጡባቸው፤ አንዱ እሣት አምጣ ሲለው አንዱ ውሃ ያመጣል አንዱ ጭቃ ሲል ደግም እንጨት ያመጣለታል፡፡ ✤ከዚያም ትተው ወረዱ ነገር ግን ግንቡን እንደ ጣዖት አርገው ማምልክ ሲጀምሩ ሥላሴ ጽኑ ነፋስ አስነስተው  በትነውታል፡፡ #ምሥጢረ_ሥላሴን ሲያስረዳ ( “እግዚአብሔርም አለ” አንድነታቸውን ሲያጠይቅ ድግሞም ኑ እንውረድ አለ  ፤ ሶስትነታቸውን ሲያጠይቅ፤)  (ዘፍ 11) #ባቢሎን ማለት ዝርው (ዝሩት) ሲሆነ ቋንቋ እና በቦታ ስለተለያዩበት ስያሜውን አግኝቷል (እግዚአብሔር ቋንቋን በትኗልና፣ አህዛብንም በዓለም ሁሉ በትኗልና፡፡ ‹‹…ሥላሴ ሕጸበኒ ወአንጽሐኒ እምአበሳየ በሐሊበ ምሕረትከ ›› ሰይፈ ሥላሴ ዘዓርብ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፲. #ሐረር_ሐድሬ_ጥቆ_መካነ_ሥላሴ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ሐረርጌ ሃገረ ስብከት፥ ሐረር ከተማ፥ ሐድሬ ጥቆ ወረዳ፤ (በአፄ ኀይለ ሥላሴ በ1941-43 ዓ.ም. የተሠራ) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሐረር፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን) /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥር ፯፤ #በዓለ_ሥላሴ_ (#ዝርወተ_ባቢሎን)፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_ቅድሥት_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈረሱበት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው #፳፭ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የቅድስት_ሥላሴ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፲፭ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #መካነ_ሥላሴ ( #መንበረ_ፀባዖት_ቅድስት_ሥላሴ_ቤ.ክ.)፤ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻው፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ 4 ኪሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → 4 ኪሎ፤ ፪. #መንበረ_ስብሐት_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ሽሮ ሜዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከአራዳ ጊዮርጊስ)(ከመርካቶ)(ከቦሌ)(ከካዛንቺስ)(ከስታዲየም) → ሽሮ ሜዳ፡፡ ፫. #ደብረ_ሲና_ቅዱስ_እግዚአብሔር_አብ፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ በአዲሱ ገበያ በቀጨኔና በእንጦጦ መሃል ላይ የሚገኝ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → አዲሱ ገበያ(ቀጨኔ) → ቅዱስ እግዚአብሔር አብ፡፡ ፬. #መሪ_ምሥራቀ_ፀሐይ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት መሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → መሪ/አያት/፡፡ ፭. #ካራ_አሎ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ካራ አሎ፡፡ ፮. #ጠሮ_ደብረ_ብርሃን_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ከተማ፥ ጠሮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ/መርካቶ/ → ኮልፌ፡፡ ፯. #ጀሞ_ፈለገ_ኮሬብ_ቅድስት_ሥላሴና_ቅድስት_ማርያም አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ ሸዋ ዳቦ ቤት /ሜክሲኮ/ → ጀሞ፡፡ ፰. #ደብረ_ቀራንዮ_መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቀራንዮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → ቀራንዮ፡፡ ፱. #አየር_ጤና_አንቀጸ_ብርሃን_ቅድስት_ኪዳነ_ምሕረት፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አየር ጤና፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፲. #ሰፈረ_ገነት_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 4፤ ታክሲ፤ ከሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፲፩. #ፈለገ_ብርሃን_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፲፪. #ቂሊንጦ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9 ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → /በጎሮ/ ቂሊንጦ ወይም ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፲፫. #ኤረር_ጽርሐ_አርያም_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፬. #መሪ_ቅድስት_ሥላሴ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ መሪ አያት፥ ወረዳ 13፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → መሪ/አያት/፡፡ ፲፭. #ቦሌ_ኆኅተ_ብርሃን_ቅድስት_ማርያም፤ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የቅድስት_ሥላሴ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፲ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (ከ2014 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ የብዙ ቅዱሳን /የአባ ዐምደ ሥላሴ፣ የአባ ክፍለ ማርያም፣ የ7ቱ ዘሥላሴ፣ የአባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ፣ …….. ) መፍለቂያ፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራ (መተማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር/አዘዞ/ → ሸዲ/መተማ/ → በእግር፡፡ ፪. #ዱጉም_ሥላሴ_ገዳም፤ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ገርዓልታ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ → በመቀለ (በጎንደር) → ገርዓልታ፡፡ ፫. #ደብረ_ወገግ_አሰቦት_ቅድስት_ሥላሴና_አቡነ_ሳሙኤል፤ (በ13ኛው ክ/ዘመን በታላቁ ጻድቅ በአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተስፋፋ፥ ቅዱስ ዑርኤል የጌታን ደም በጽዋው የመጨረሻውን እንጥፍጣፊ ያፈሰሰበት፥ በርካታ ቅዱሳን የተሰወሩበት፥ አሁንም የሚሠወሩበት፥ የምሥጢር ቦታ) አድራሻ፤ ሐረርጌ፥ አሰበ ተፈሪ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ናዝሬት/አዳማ/→ አሰበ ተፈሪ → አሰቦት፡፡ ፬. #ሰሜን_ሸዋ_ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_፤ (በ14ኛው ክፍለ ዘመን በዓፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የተመሠረተ፡፡) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን ከተማ፡፡ ፭. #መካነ_ሥላሴ_ደቡብ_ወሎ_ወረኢሉ፤ (በ1500ዓ.ም. በዐፄ ናዖድ የተመሠረተና በልጁ በዐፄ ልብነ ድንግል ሥራው የተጠናቀቀ፤ ባለ 16 መንበር፥ በዕንቊና በወርቅ የታነጸ የነበረ፤ /ኋላ በግራኝ የፈረሰ/፤ ነገር ግን ጽላቱ በዐፄ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ቀድሞ 4 ኪሎ መካነ ሥላሴ አሁን መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል የሚጠራው)፤ ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና በቀድሞው ቅርጹ በባለ 16 መንበር ተደርጎ 2009 ዓ.ም. አካባቢ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በመገንባት ላይ ይገኛል፤ (ለሕንፀታ ቤቱ ሁላችንንም ያብቃን)፡፡ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ወረኢሉ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወረኢሉ፡፡ ፮. #ፀዓዳ_አምባ_ቅድስት_ሥላሴና_አቡነ_ሰይፈ_ሚካኤል_ገዳም፤  (በ1669 ዓ.ም. የተገደመ፤ መሄጃ መንገዱ እጅግ አስደናቂና በ2ቱም በኩል ገደል የኾነ) አድራሻ፤ ኤርትራ፥ ዞባ አንሰባ፥ ከረን፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ (በአውሮፕላን)→ ኤርትራ → ከረን → /25ኪ.ሜ/ ፀዓዳ አምባ፡፡ ፯. #ጎንደር_ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_፤ (በጥር 26 ቀን 1683 ዓ.ም. በዓፄ አድያም ሰገድ የታነጸ፤ በጎንደር ከተማና ዙሪያ ከሚገኙ 44ቱ ታቦታተ ጎንደር በአሠራሩ ልዩ የኾነ፤ በ1880ዎቹ ድርቡሽ ጎንደር ከተማን ሲያጠፋ ከ44ት አብያተ ክርስቲያናት በተአምራት ሳይቃጣል የቀረ፤ የታላላቅ ሊቃወንት /የእነ ሊቁ ክፍለ ማርያም/ መፍለቂያ፡፡ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፰. #ናርጋ_ሥላሴ_ገዳም፤ (በጣና ሐይቅ ላይ ካሉ ደሴቶች ትልቁ በሆነው በደቅ(7ት ደብር ሃገር) ደሴት ከሚገኙ 7 ገዳማት አንዱ)፡፡ (በአፄ በካፋ ባለቤት በበእቴጌ ምንትዋብ /1730-1755 ዓ.ም./ የተሠራ፤ ግድግዳዎቹ በሚያስደንቁና ልቡናና መንፈስን በሚመስጡ ሥዕላት ያሸበረቁ፡፡) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጣና ሐይቅ (ከባሕር ዳር ከተማ ሰሜናዊ 37 ኪ.ሜ ርቀት ላይ /በጀልባ 3 ሰዓት/፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባህር ዳር/ጎንደር → በጀልባ/በታንኳ/ /በመርከብ/ ናርጋ ሥላሴ፡፡ ፱. #ጨለቆት_ሥላሴ_ትግራይ፤ መቀለ አጠገብ፡፡ (በ1787 ዓ.ም. የተመሠረተ ሲኾን ተካዩ ደጃዝማች ወልደ ሥላሴ ክፍለ ኢየሱስ ሃገረ ገዢ ናቸው) (የታላላቅ ሊቃውንት መፍለቂያ ነው፤ ለአብነትም በዐፄ ዮሐንስ /1864 – 1881ዓ.ም./ ዘመነ መንግሥት አራት ጳጳሳትን እንዲያመጡ ከተላኩት መካከል አንዱ ሊቅ አለቃ ዐሥራት ዘውጉ ዘጨለቆት ሥላሴ ናቸው፡፡) (የእንግሊዝ ጦር ዐፄ ቴዎድሮስ በመቅደላ ሰብስቦት የነበረውን ዘርፈው ሲወስዱ የበዛባቸውን ለዚህ ደብር ሰጥተው ሄደዋል፡፡) አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት ፥ እንደርታ አውራጃ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ /እንደርታ/፡፡