uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 383 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 582-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 194-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 383 obunachiga ega bo‘ldi.

09 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 38 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.91% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.42% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 370 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 449 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 25 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 10 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 383
Obunachilar
-124 soatlar
-67 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
ሥርዐተ ማኅሌት ዘልደት፡፡ ወረቦቹን በድምፅ ከፈለጉ በሚከተለው የቴልግራም አድርሻችን ያገኛሉ፤ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚ
+5
ሥርዐተ ማኅሌት ዘልደት፡፡ ወረቦቹን በድምፅ ከፈለጉ በሚከተለው የቴልግራም አድርሻችን ያገኛሉ፤ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን የልደት ማኅሌትን እነሆ ብለናል፤ እንደ የደብራችሁ ይትበሃልም እንድትጠቀሙበት የላይ ቤቱንም የታች ቤቱንም አንድ ላ አዘጋጅተነዋል፡፡ (ደብራችሁ በላይ ቤት አቋቋም የሆነ ‹‹ዘቀሃ ኢየሱስ›› የሚለውን እንድትመለከቱ፤ ደብራችሁ በታች ቤት አቋቋም የሆነ ‹‹ዘአደባባይ ኢየሱስ›› የሚለውን እንድትመለከቱ እናሳስባለን፡፡ መልካም ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ (የወረቡ ድምፅ የመምህር አባ ናሁ ሠናይ ነው፡፡) # ፠በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ # ፠በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብረ ሰላም፤ ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ፡፡ (#የሰላም_ማደሪያችን_የሆነችው_ቅድስቲቱ_የተለየችው_ደብረ_ሰላም_፤ ሁላችን ወደ እናታችን ማርያም እንሰገድ፡፡) (በታላ
+1
ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብረ ሰላም፤ ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ፡፡ (#የሰላም_ማደሪያችን_የሆነችው_ቅድስቲቱ_የተለየችው_ደብረ_ሰላም_፤ ሁላችን ወደ እናታችን ማርያም እንሰገድ፡፡) (በታላቁ ደብራችን የነበሩ ቀደምት ሊቃውንት፤ ለደብራችን ለቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ብቻ ከደረሱት ከ850 በላይ ወረቦች መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህ ወረብ ለ21 ዓመታት ሳይባል ቆይቶ ዘንድሮ በወርኀ ጽጌ ተወርቧል፡፡ ድምፁ፤ ከደብራችን ሊቃውንት መካከል የአንጋፋው የአጋፋሪ ይሁኔ ነው፡፡ # ፠በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ # ፠በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ጸልዩ በእንተ አውስትራልያ፡፡ (ሁላችንም የልደትን በዓል ከዋዜማው ጀምሮ ስናከብር፤ ቢያንስ 1ድ አቡነ ዘበሰማያትና ሰላም ለኪ እያልን እናስብ) #በአውትራሊያ_ሕዝቡ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ (ግብረሰዶም
+9
ጸልዩ በእንተ አውስትራልያ፡፡ (ሁላችንም የልደትን በዓል ከዋዜማው ጀምሮ ስናከብር፤ ቢያንስ 1ድ አቡነ ዘበሰማያትና ሰላም ለኪ እያልን እናስብ) #በአውትራሊያ_ሕዝቡ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ (ግብረሰዶም) በአደባባይ ወጥቶ ሕጋዊ ይሁን ይፈቀድልን ብሎ ድምጽ ሰጥቶ በፓርላማ ካጸደቀበት ጊዜ ጀምሮ በከባድ የእግዚአብሔር ቁጣ ፤ ሰው ሊያጠፋው የማይችል የሚያቃጥል እሳት ሀገሪቱ ላይ እየወረደና እየናጣት ይገኛል፡፡ እስከአሁን በተነሳው እሳት፤ * 24 ሰዎች፣ * 500 ሚሊዮን እንስሳት፣ * 8,000 ተኩላዎች ተቃጥለው መሞታቸው ተነግሯል፡፡ ከ 5.5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ (በስፋት ቤልጅየምን የሚያክል) የሀገሪቱ ክፍል በእሳቱ ተቃጥሏል፡፡ ከ 10,000 ማይሎች በላይ ርዝመት ባለው የእሳት አደጋ ምክንያት ከ 1,400 በላይ ቤቶች ወድመዋል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች ሕንፃዎች እና የመሠረተ ልማት ግንባታዎችም ወድመዋል፡፡ እስካሁን በቊጥር ያልተገለጸም ውድመት መድረሱ እየተነገረ ነው፡፡ ከጫካ እሳት ጢስ በሚወጣው መርዛማ ጋዝ ምክንያት እስከአሁን ከ10 ሚሊዮን ሰዎች ወይም ከዚያ በላይ መተንፈስ ችግር እንዳጋጠማቸው ተነግሯል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከከባድ ሙቀት፣ አመድ እና ከተቃጠሉ አቧራ ማምለጫ መንገድ አጥተው በየከተሞቹ በከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ መሆናቸው ተነግሯል። ** በአ.አ. ለስማቸው መጠርያ ስትሰጥ እንጂ ስታወግዝ ያልታየህ የኢትዮጵያ መንግሥትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ ይህንን አጸያፊ ተግባር የሚያከናውኑና የሚደግፉ እንዲሁም በየቤተ እምነቶች ያሉ ተባባሪዎች ከአውስትራልያ ልንማር ይገባል!!፡፡ የምድሩ እንዲህ ካቃጠለ በገሃነም እሳትማ ምን ይጠብቀን ይህንን!!!???? ‹‹ከሴትም ጋር እንደምትተኛ ከወንድ ጋር አትተኛ ፤ ጸያፍ ነገር ነውና፡፡›› (ዘሌዋ.18፥22)

#ንቃህ_መዋቲ_፤ #አንተ_የተኛህ_ንቃ_፡፡ #በአርሲ ነገሌ የመስቀል ጠላቶች በሆኑ የዘመኑ ባለሥልጣናት ከነበረበት ከመስቀል አደባባይ ተነሥቶ ወደ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እንዲወሰድ ተድርጓል፡፡ #በሆሳዕና የጥምቀት በዓል ማክበርያ ቦታ እንዳይኖር ተደርጓል፡፡ #ይግባኝ_ለክርስቶስ_፤ #ባለፉት_2ት_ #ዓመታት_በቤተ_ክርስቲያናችንና_ምዕመናኖች_ላይ_የተፈጸሙብን_ግፎች_፤ ፠ 158 በግፍ የተገደሉ ምዕመናን ፤ ፠ 44 አካላዊ ጥቃት የደረሰባቸው ምዕመናን፤ ፠ 417 ሀብት ፥ ንብረት የወደመባቸው ምዕመናን፤ ፠ 6450፤ ከቀያቸው፥ ከሰፈራቸው፥ ከመንደራቸው የተፈናቀሉ ምዕመናን፤ ፠ 38፤ ተገደው ሳይፈልጉ እንዲሰልሙ የተደረጉ፤ ፠ 17፤ ሙሉ ለሙሉ የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት፤ ፠ 13፤ ንዋያተ ቅድሳትና ሌሎች ንብረቶች የተዘረፉና የተቃጠሉባቸው አብያተ ክርስቲያናት፨ እንዲሁም #በሰሞኑ (በታኅሣሥ ወር) #በምዕመናን)_ላይ_የደረሱብን_ግፎች_፤ ፠ በሻሸመኔ ነጠላ የለበሱ እየተቀሙ በየመንገዱ በእሳት ተቃጥሎባቸዋል፡፡ ፠ ሰው በሀገሩ (በሻሸመኔ) ልብሱ በሃይማኖት ምክንያት ተቃትሎበታል፤ ፠ የሃይማኖት ሥርዐት የምናከብርበት መስቀል በአርሲ ነገሌ ከቦታው ተነስቷል፤ ፠ በሆሳዕና ጥምቀተ ባሕር ማክብርያ እንዳይኖረን ተደርጓል፡፡ #የአርሲ_ነገሌ_መስቀል_ከነበረበት_ቦታ_መነሣትን_በተመለከተ_፤ *መስቀሉን ከመሬት ላይ እንጅ ከክርስቲያኖች ልብ መንቀል አይቻልም፤ *ቀድሞም ለመስቀል ጠላቶች ነበሩ ዛሬም ለመስቀሉ ጠላቶች የሆኑና የመንግሥትን ሥልጣን ከለላ ያደረጉ ተነሡ፡፡ *በሀገር ሰላም እየተሰበከ የሰላም ምልክት የሆነውን መስቀል መንቀል በውኑ ሰላም ያመጣልን!? *ኦርቶዶክስ ሀገር በሆነችበት ኢትዮጵያ፤ ኦርቶዶክስን ለማሳደድ የሚደረጉ ተግባራት ሁሉ ሊቆሙ ይገባቸዋል፡፡ *የአንድን ግለሰብ መብት እናከብራለን የሚለው መንግሥት የቤተ ክርስቲያንን ግፍ ፥ የሕዝቡን ጩኸት ሊመለከት፤ ትክክለኛ ፍርድም ሊሰጥ ይገባዋል፤ ያን ማድረግ ካልቻለ መንግሥት አይደለምና!!!!፡፡ #በሆሳዕና_የጥምቀተ_ባሕር_እንዳይኖር_የተደረገ_ሴራን_በተመለከተ_፤ *ለቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥምቀት ምንም ቦታ አልሰጥም ያሉት ሥልጣንን ተገን ያደረጉ *በአንጻሩ ለፓስተር ሣሕሉ፤ 50,000 ካሬ ለፓስተር ዮናታን፤ 100,000 ካሬ ለፓስተር እስራኤል፤ 36,000 ካሬ ለከተማው አህዮስ መቆሚያ፤ 5000 ካሬ በአጠቃላይ፤ 191,000 ካሬ ሰጥተዋል፡፡ የአርሲ ነገሌና የሆሳዕና ምዕመናን ኀዘናችሁ ኀዘናችሁ፥ ልቅሷችሁ ልቅሷችን ነው፤ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ፍርዱን ይስጠን፨፡፡፨ #ንቃህ_መዋቲ_፤ #አንተ_የተኛህ_ንቃ_፡፡

#የጥድ (#የገና) #ዛፍ #በቤተ_ክርስቲያንና_በመጽሐፍ_ቅዱስ_እይታ_ ፠#የጌታችን_ልደት_December_25 #ወይስ_ታኅሣሥ_29 _(በ4ት ዓመት በ28) ፠ #የጥድ_ዛፍ_መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ወይስ_የአውሮፓውያን_ባህል_? ፠ #የጥድ_ዛፍን_ምዕራባውያን_የሚቀበሉበት_ምክንያትና #_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? ፠ #ሳንታክሩዝ (#የገና_አባት?) #ማነው? #የጌታችን_ልደት_December_25 #ወይስ_ታኅሣሥ_29 _(በ4ት ዓመት በ28) ፠፨፠ ምዕራባውያን የጌታችንን ልደት የሚያከብሩበት ምክንያት፤ 1ኛ) በ December 25፤ የጥንታውያን የግብጽ የፀሐይ አምላክ ‹‹ራ›› የተባለው ጣዖት የተወለደበትና በዘንባባ ዛፎች መሃል የሚመለክ፤ ከታች የሰው ሰውነት ራሱ የአሞራ ጭንቅላቱ ላይ ፀሐይን የከበበ ዘንዶ ያለበት ጣዖት የሚያመልኩበት ነው፡፡ 2ኛ) በDecember 25፤ ሚትራስ፤ በመካከለኛው ምሥራቅ የሚታወቅ ባዕድ አምልኮ የሚመለክበት በመሆኑ፤ 3ኛ) በ December 25፤ ሳተርን ሊያ፤ የጥንት የሮማ የእርሻ አምላክ በመባል የሚታወቅ ነው፡፡ በራቁት ጭምር ብዙ ኃጢአት የሚገበርለት ነው፡፡ በ3ኛውና በ4ኛው ይህን ጣዖት አንቀበለም በማለታቸው በርካቶች ሰማዕትነት ተቀብለውበታል፡፡ (ካቶሊካውያን ከላይ የጠቀስናቸውን የባዕድ አምልኮ እናስተዋለን ሲሉ ነው ዲሴምበር 25 የደነገጉት) ፠፨፠ እኛ ኢትዮጵያውያን ግን የነቢያትን ትንቢት ፥ የአበውን ቀመር (የ15ቱ ሱባኤያትን ቀምረን)፤ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረትነት ነው፡፡ #ምዕራብውያን_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? በምዕራቡ ዓለም ሰዎች በአንድ ዓመት ውስጥ የሚመጣ ሁለት/፪/ ክስተቶች አሏቸው፡፡ 1ኛ) የዘጠኝ ወር ክረምት ሲሆን 2ኛ) ለሦስት ወራት የሚቆይ የበልግ ጊዜ ነው፡፡ በዘጠኝ ወር ክረምት ሲሆን ለዘጠኝ ወር ያህል መሬት ልምላሜ አትሰጥም፡፡ ዛፎች ይሰባበራሉ፡፡ ቅርንጫፎች ቅጠሎች ይወድቃሉ፡፡ ፍሬዎች ይረግፋሉ፡፡ በክረምት ወራት በሚዘንበው ዝናብ በረዶ የቀላቀለ በመሆኑ የበረደው ክምር መሬቱን ስለሚሸፍን መሬት በረከቷን አትሠጥም በእዚህ የተነሳ ለዘጠኝ ወራት ያህል ይራባሉ፡፡ ይጠማሉ፡፡ ታዲያ በእነርሱ አመለካከት ይህንን የክረምት ወቅት የጨለማ እና የክፉ አምላክ ዘመን በመሆኑ ነው እንጂ ደግ አምላክ ቢሆንማ እንደዚህ አያሰቃየንም ብለው ያስባሉ፡፡ በሁለተኛው ክስተት ማለትም ለሦስት ወራት ያህል ፀሐይን የሚያዩበት አርሰው ፥ ዘርዘርተው የሚያመርቱበት ለዘጠኝ ወራት የሚሆናቸውን ቀለብ የሚሰበስቡበት ነው፡፡ በአጠቃላይ የልምላሜ፣ የጥጋብ እና የተስፋ ወራታቸው ነው፡፡ በዚህም እንደ እነርሱ አመለካከት ይህን የበጋ ወቅት የብርሃን የደጉ አምላክ ዘመን ይሉታል፡፡ #ምዕራብውያን_ለምን_ልደትን_በጥድ_ዛፍ_ያከብራሉ? በእነርሱ ፍልስፍና ምንታዌ/ሁለት/ አማልክት አሉ ብለው ያስባሉ፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በክረምቱ የዘጠኝ ወራት ውስጥ ብዙ ዛፎች ሲገነደሱ፣ ሲቈረጡ ፣ ፍሬያቸው ሲረግፍ አንድ ዛፍ ግን ፍሬው ሳይረግፍ ሳይገነደስ የዘጠኝ ወር ክረምቱን ያሳልፋል፡፡ ይህም ዛፍ ጥድ ነው፡፡ ጥድ ዛፍ ከሌሎች ዛፎች ሁሉ ጠንክሮ ፀንቶ የሚቆየው በተፈጥሮ ፅኑ ጠንካራ በመሆኑ እንጂ ሌላ ተአምር ኖሮት አይደለም፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ አውሮፓውያን ለገዛ ሓሳባቸው ሲሉ ጥድ ምንም አለመሆኑ ደጉ አምላክ ያንን የክፉ አምላክ ዘመን የሚያሳልፈው በጥድ ዛፍ ውስጥ ስለተሸሸገ ነው፡፡ የጥድ ዛፍ ለደጉ አምላክ ቤተ መቅደስ ነው ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ይህ የጥድ ዛፉን በዓመት በዓመት ክረምቱ አልቆ በጋው ሲገባ የደጉ አምላክን መቅደስ እያስጌጡ በጥድ ያመልኩ ነበር፡፡ የክርስትና ሃይማኖት ሲስፋፋና ሲቀበሉ ይህን አምልኮታቸውን አዲስ ከተቀበሉት ሃይማኖት ጋር በማስተሳሰር ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት አዲስ ስም ሰጥተው ይጠቀሙበት ጀምረዋል፡፡ ከጌታችን ልደት ጋር ያስተሳሰረው ይህ ብቻ ሳይሆን የደጉ አምካቸውን መቅደስ የሚስጌጡበት ማለትም ክረምቱ አልቆ በጋው የሚገባበት /የዘመን መለወጫው/ እና የጌታችን የመድኃኔታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በጊዜ አቈጣጠራቸው መገናኘቱ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የድሮ ባህሎቻቸውን እንዳይረሱ ቀናቶቻቸውንም ጭምር ስማቸውን በአማልክቶቻቸው ሰይመውታል፡፡ ለምሣሌ፤ ቀኑ ስያሜውን ያገኘው *Monday (ሰኞ) --------------------------- Moon day ጨረቃን የሚያመልኩበት ቀን *Sunday (እሑድ) ----------------------- Sun day ፀሐይን የሚያመልኩበት ቀን *Saturday (ቅዳሜ) ----------------------- Star day ኮከብን የሚያመልኩበት ቀን *Tuesday (ማክሰኞ) -------------------- Tues day (“Thuse” የተባለ ጣኦታቸውን የሚያመልኩበት ቀን) ** የX MASS tree (የገና ዛፍ) የተጀመረው ከሳተርን ሊያ (የጥንት የሮማ የእርሻ አምላክ) ሲሆን፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በቤቱ ያስገባው የጀርመኑ ሃገር የመናፍቅ ሰባኪ ማርቲን ሉተር ነው፤ ወደ አሜሪካ ደግሞ በ1830ዎቹ ከጀርመን ወደ አሜሪካ የተሰደዱ ፔንሲልቫንያዎች ናቸው ከክርስቶስ ልደት ጋር እያያዙ ማክበር የጀመሩት፤ በ1940ዎቹ በአሜሪካና በሌሎቹም ዓለማት እየተስፋፋ መጣ፡፡ ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች የእነርሱን ተከትለን እንዴት ወደ ስሕተት አንዴት እንገባለን!!፡፡ ነገር ግን ከአንድም ሁለቴ ተሳስተናል፡፡ ፠ አንደኛ ሁለት አምላክ አለ ብለን የምናምን አይደለንም ፠ ሁለተኛ እግዚአብሔር ይህችን ቅድስት ሃገር ስለባረካት ክረምቱ ፪ ወራት ብቻ መሆኑ ነው፡፡ በክረምቱም ይህንን ያህል የበረዶ ግግር የለብንም፡፡ ስላደረገልን ነገር ሁሉ ማመስገን አለብን እንጂ፡፡ #ሳናታክሩዝ_፤ አንዳንዶች በ4ኛው ክ/ዘመን ከተነሣው ቅዱስ ቅዱስ ኒኮላስ ጋር አገናኝተው ለልጆች ስጦታ ከሚሰጠው ጋር ለማገናኘት ይሞክራሉ ግን ይህ ሐሰት ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ አስተሳሰብ፤ *ሳንታክሩዝ መጥቶ ሌሊት ስጦታ ይላል በሚል ሕፃናቱ፤ ሐሳባዊ በሆነ (በስዕል ነጭ ረዥም ጢም ያለውን ሰው አለ ብለው ሐሰት እንዲማሩ) ያደርጓል፤ ስጦታውን የሚሰጡ ቤተሰቦች ሆነው ሳለ፡፡ *ሰዎች በጌታ ልደት መወለዱን ሳይሆን ሳንታክሩዝ ይመጣል ብለው እንዲያስቡ አድርጓል፤ * ከማንኛውም ነገር ነላይ የጌታ ልደት ይበልጣልና መታሰብ ያለበት የጌታ ልደት እንጂ ሳንታክሩዝ መሆን የለበትምና፡፡ እንግዲህ ብርሃን ከጨለማ ጋር ምንም ኅብረት እንደሌለው አውቀን የምናደርገውን ከማድረጋችን በፊት ልንጠይቅ ልንሰማ ልንማር ያስፈልጋል፡፡ አባቶቻችን የልደትን በዓል እንድናከብር ያስተማሩን ዛፍ ቆርጦ በማቆም ሳይሆን የተደረገልንን ድኅነት እያሰብን(አምላክ ሰው ሆኖ እንዳዳነን) ፥ እንደ መላእክት እንደ እረኞች በስብሐተ ለእግዚአብሔር ፥ እጅ መንሻ አምሃ በመስጠት ፥ በመረዳዳት ፥ የታመመን በመጠየቅ ሊሆን ይገባል፡፡ ወዳጆቼ ሆይ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ፡፡ /1ኛ ቆሮ. 10/ /ይሁዳ 1፥4/ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ /ምንጭ፤ የፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔትና የመ/ር ለማ ‹ወዳጆቼ ሆይ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ› የሚል ስብከት፡፡) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የብፁዕ አቡነ ዳንኤል ሥርዐተ ግብዐተ መሬት፤ ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ 11ድ ሊቃነ ጳጳሳትና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በደብረ ሊባኖስ ገዳም ተፈጸመ፡፡ • በ75 ዓመታቸው ያረፉት ብፁዕነታቸው አስከሬን፤ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፤ በሀጋረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀውስጦስና በሌሎች 10ር አበው ሊቃነ ጳጳሳት ታጅቦ ማምሻውን ደብረ ሊባኖስ ገዳም የደረሰ ሲኾን፣ ዐርብ ታኅሣሥ 24 ቀን ታቦተ ተክለ ሃይማኖት ወጥቶ ታሪከ ዜናቸውን ተንቦ ቅዳሴ ተቀድሶ ድርገት እንደተወረደ በተዘጋጀለት ቦታ በክብር አርፏል፡፡ ከዜና ታሪካቸውም በአጭሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፤ • ከዐድዋ እስከ ደጋሐቡር – ከደቡብ አፍሪካ እስከ አሜሪካ ብሔር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ሐዋርያዊነት፤ • ሰባኬ ወንጌል – መምህር – ማሕሌታዊ – አስተዳዳሪ – የተሟላ አገልግሎት በተወዳጅ ሰላማዊ አባትነት፤ ፠ ልደት፤ በፊት ስማቸው አባ ፍቅረ ማርያም ታደሰ የተባሉት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል፣ ከአባታቸው ከአቶ ታደሰ ይልማ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደብሪቱ አየለ፣ በ1937 ዓ.ም. በሸዋ ክፍለ ሀገር በፍቼ አውራጃ ልዩ ስሙ ግምብቹ በዓለ ወልድ አካባቢ ተወለዱ፡፡ ፠ ትምህርት፤ በተወለዱ በሰባት ዓመት ዕድሜአቸው ለትምህርት ሲደርሱ በታላቁ ገዳም በደብረ ሊባኖስ፡- • ከመምህር ገብረ ጊዮርጊስ ንባብ እና ዳዊት • ከየኔታ ንጉሤ እና ከአለቃ መኰንን ፆመ ድጓ፣ ምዕራፍ በወሎ፤ • ከየኔታ ወልደ ሰንበት ቅኔ ከነአገባቡ • ከአለቃ ድንቁ ትርጓሜ ሐዲሳት በጎንደር ክፍለ ሀገር • አቋቋም ከየኔታ ጌራ እና ከየኔታ ሚናስ ተምረዋል፡፡ • ቅዳሴ ከየኔታ ገብረ እግዚአብሔር ኀይሉ እና ከመምህር ገብረ ሊባኖስ በደብረ ኣባይ አስመስክረዋል፡፡ • በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፣ ከታላቁ አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በነገረ መለኰት ከፍተኛ የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡ • በአሜሪካን ሀገር በሜኒሶታ ክፍለ ሀገር በቶማስ ዩኒቨርሲቲ በቴዎሎጂ በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡ ፠ ሥልጣነ ክህነት፤ • ዲቁና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ በደብረ ሊባኖስ ገዳም • ቅስና ከብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በአኵስም • ቁምስና ከብፁዕ አቡነ አብርሃም ምሥራቅ ሐረርጌ ተቀብለዋል፡፡ ፠ አገልግሎት እና ሓላፊነት፤ በዐድዋ አውራጃ በአይስሐ ወረዳ በአርባእቱ እንስሳ በመርጌትነት እና በመምህርነት አገልግለዋል፡፡ እንዲሁም በዚኹ አውራጃ፣ በእንትጮ ወረዳ በሚገኘው በታላቁና አንጋፋው የደብረ ዳሞ ገዳም በመመንኰስ በደብሩ በግብረ ክህነት እና በማስተማር ሲያገልግሉ ኖረዋል፡፡ ቀጥሎም በወሎ ክፍለ ሀገር በአሳይታ አውራጃ በሚሌ ወረዳ የሚገኘውን የቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስቲያን በመመሥረትና በማስተዳደር አገልግለዋል፡፡ በኦጋዴን ደጋሐቡር አውራጃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በመኾንና በስብከተ ወንጌል ሠርተዋል፡፡ በገለምሶ አውራጃ በደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ በመኾንና በስብከተ ወንጌል አገልግለዋል፡፡ በድሬዳዋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በእልቅና ተመድበው ሠርተዋል፡፡ እንደገናም በሐረር ክፍለ ሀገር በአሰቦት ገዳም ተሹመው ሥርዐተ ገዳሙን በመጠበቅና የመናንያኑን መብት በማስከበር አበምኔት ኹነው አገልግለዋል፡፡ በሸዋ ክፍለ ሀገር በናዝሬት አውራጃ በደብረ ዘይት ወረዳ በሚገኘው በታላቁ የዝቋላ ገዳም አበምኔት ተሹመው ሥርዐተ ገዳሙን በመጠበቅ አስተዳድረዋል፡፡ የውጭ ሀገር አገልግሎትን በተመለከተ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየላከቻቸው በምሥራቅ አፍሪቃ፥ በሱዳን፣ በኬንያ፣ በዝምባቡዌ/ሐራሬ/፣ በደቡብ አፍሪቃ አገልግለዋል፡፡ በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ከአምስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጋራ በመመሥረትና በማቋቋም፣ በእልቅና፣ በግብረ ክህነት እና በስብከተ ወንጌል አገልግለዋል፡፡ በሜኒሶታ ግዛት የደብረ ሰላም መድኃኔዓለምን ቤተ ክርስቲያን በመመሥረት እና በማቋቋም አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ብፁዕነታቸው ይህን ሰፊ ሐዋርያዊ አገልግሎት በውጭው ክፍለ ዓለም ሲሰጡ ከቆዩ በኋላ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሦስት የቤተ ክርስቲያን ምሁራን ጋራ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ተልከው ለስምንት ወራት የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር በማካሔድና በማስተማር አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በእልቅና ሠርተዋል፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ዲን በመኾን አገልግለዋል፡፡ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ሓላፊ በመኾንም አመራር ሰጥተዋል፡፡ በምዕራቡ ክፍለ ዓለም ለብዙ ጊዜ በአገልግሎት እንደ መቆየታቸው በእንግሊዝኛ ቋንቋም የሚያስተምሩት ብፁዕነታቸው፣ በተሟላው የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸው፥ በማሕሌት እና በትምህርተ ወንጌል የሚወደዱ፣ ለብሔር አቀፉም ኾነ ለዓለም አቀፉ ተልእኮ የሚፋጠኑ፣ የሰው ፍቅር እና መግባባት ያላቸው ተወዳጅ ሰላማዊ አባት ነበሩ፡፡ ፠ ማዕርገ ጵጵስና፤ በዚህም የአገልግሎት ፍሬያቸው ተመዝነው ብቁ ኾነው በመገኘታቸው፣ ሐምሌ 9 ቀን 1997 ዓ.ም. በተደረገው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ከሌሎች ዕጩ ቆሞሳት ጋራ ተወዳድረው ከፍተኛ የድምፅ ብልጫ ስላገኙ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለማዕርገ ጵጵስና ተመርጠው፤ ተሹመዋል፡፡ ኤጲስ ቆጶስነት የተሾሙበትን የአሶሳ ሀገረ ስብከት ጨምሮ፣ በምዕራብ ሐረርጌ፣ በምሥራቅ አፍሪቃ(ጅቡቲ እና ኬንያ) እንዲሁም ድሬዳዋ አህጉረ ስብከት፣ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በትጋትና በሰላማዊነት ሲፈጽሙ ቆይተው፣ በተወለዱ በ75 ዓመታቸው፣ በሰላመ እግዚአብሔር ዐርፈዋል፡፡ ለብፁዕነታቸው አስከሬን፣ ዛሬ ከቀትር በኋላ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ሽኝት የተደረገ ሲኾን፣ በብፁዓን አባቶች ታጅቦ ማምሻውን ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደርሷል፡፡ በብፁዕነታቸው ቃል እና በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት፣ ሥርዐተ ቀብራቸው፣ ነገ ዓርብ፣ ታኅሣሥ 24 ቀን 2012 ዓ.ም.፣ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት እና ምእመናን በተገኙበት ከቀኑ በ9፡00 በደብረ ሊባኖስ ገዳም ይፈጸማል፡፡ የብፁዕ አባታችንን ነፍስ ከማኅበረ ቅዱሳን ይደምርልን፤ የጸሎታቸው በረከት ይድረሰን፤ አሜን፡፡ ምንጭ፤ በኤጲስ ቆጶስነት ሢመታቸው የወጣው ዜና ሕይወታቸውና ከደብረ ሊባኖስ የተጠናከረው መረጃ ምንጫችን፡፡

#ዐርብ_ቅዳሜና_እሑድ_፤ ++ የጸሎት መርሐ.ግብር፥ በጾሙ ማብቂያ (ከዐርብ - እሑድ፤ ማታ ማታ) ++ የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ (ቅዳሜ በ10 ሰዐት) ++#፻፶፭ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ /የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፮፡፡ (ዐርብ_ታኅሣሥ_24፤ #ከ፲፪-፪ ሰዐት) *+* የአራዳና ጉለሌ ክ/ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በሰ/ት/ቤታችን አገልግሎትና መምርያ ቦታን በተመለከተ ቅዳሜ #ታኅሣሥ_25 #ከቀኑ_በ10_ሰዐት እንድንወያይ ጥሪ ስላደረገ፤ አባላት በሙሉ በተጠቀሰው ሰዐት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። (የቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት)

ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/ **ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡ **ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡ **ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ **ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ **ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ **ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡ **ኢዩኤልም ‹‹የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ፣ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር፡፡ ስለእርሷ ‹ይህች ማናት/› ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት፡፡ እርሱም ‹ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት፣ በእርሷም የተጎሳቆሉ አሕዛብ ይድናሉ፤ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት› ብሎ ነገረው፡፡›› **ዳዊትም በመዝሙሩ ‹‹እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ፣ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ፡፡ ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ፣ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው፡፡›› ዳግመኛም አብ አለ ‹‹ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ፣ እንደ መልከ ጸዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ፣ ከማለም አይፀፀትም፡፡›› ዕንባቆምም ‹‹አቤቱ ድምፅህን ሰምቼ ፈራሁ ሥራህንም አይቼ አደነቅሁ፤ በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ›› (ዕን ፫፥፪) **ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ‹‹በበረት ውስጥ የዓለም ገዢ መተኛት እጅግ ድንቅ ነው፤ በበረት ከጽርሐ አርያም ይልቅ ረዘመ፤ ከምድር ዳርቻም ሰፋ፤ ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ (ሕዝ 1፡18-23፣ ዳን 7፡9) ብለው ተናገሩላት፡፡ #ኢትዮጵያና ግብፅ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርሰቶስ ልደት በዓልን ታኅሣሥ 29 ቀን (በ4ት ዓመት 1ዴ ታኅሣሥ 28) ያከብራሉ፤ ለምን የሚለውን ከባሕረ ሓሰብ ሊቃውንትና ከመጻሕፍት እንድታነቡ እየጋበዝን ይህን ሁኔታ በጥልቀት ካጠኑት ዐበይት ሊቃውንት መካከል ዋናዎቹ #ማሪ ኤፍሬም ሶርያዊ፤ #ሰዒድ ወልደ በጥሪቅ፤ #መበንጋዊ/ማኅቡብ/፤ #ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ/አልአሚድ/፤ #ወልደ መነኰስ፤ #ሐዋርያት በዲድስቅልያ አንቀጽ 29 ገጽ 37፤ ሊቃውንት ወመምህራን ዘኢትዮጵያ ወግብፅ /ለአብነትም ከኢትዮጵያውን ደብረ ቢዘንና የጕንዳጒንዶ ሊቃውንት፣ አለቃ አሥራስ የኔሰው፣ አለቃ ሰዐት ከብቴ … እንዲሁም ቅዱስ ድሜጥሮስና ዮሐንስ አቤልሄሬም(ዮሐንስ አቡሻኽር) ከግብፅ ሊቃውንት/ ይጠቀሳሉ፡፡ #ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር የተባበረላቸው ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕና #ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤ #ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤ #አቡነ አካለ ክርስቶስ፤ #አቡነ መዝራእተ ክርስቶስ፤ #መስፍኑ ኢያሱ፤ #የገርአልታው አቡነ ዳንኤል፤ #ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ጌና_እና_ልደት_ ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹#ቤዛ_ኩሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤