uz
Feedback
Adoni Gospel channel

Adoni Gospel channel

Kanalga Telegram’da o‘tish

ኢየሱስ፦ የዘላለም መድኃኒት፤ የመጨረሻ መፍትሄ ነው።        Telegram- @adonigospel       Whatsapp 👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X                  

Ko'proq ko'rsatish
4 765
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-147 kunlar
-4230 kunlar
Postlar arxiv
🙏 ባለፉት አምስትና ስድስት ወራቶች ውስጥ እንደተለመደው በተለያየ ችግር ውስጥ ሆናችሁ በጸሎትም፣ በሃሳብም እንድረዳችሁ በውስጥ መስመር የተለያዩ መልዕክቶችን ልካችሁልኝ ምላሽ ያልሰጠኋችሁ ሁላችሁም ከልብ የሆነ ይቅርታን እጠይቃችኋለሁ። ከነበርኩበት ጥልቅ ኃዘን የተነሳ ዝም ማለትን ስለመረጥኩ እኔም ከነበርኩበት ስሜት እስከወጣ ነውና በዚህ መሃል ተቀይማችሁ ብሎክም ያደረጋችሁኝ ሁላችሁን ከልብ ይቅርታ እላችኋለሁ። እግዚአብሔር ባስለመደን ጸጋ እድሜ ጨምሮ ብዙ ለመማማር ያብቃን። በጸሎታችሁ አስቡኝ እወዳችኋለሁ። የክርስቶስ ፍቅር ይብዛላችሁ።❤️ አዶኒ

ክርስቶስን የመምሰል ህይወት ✨ክርስትና እድገት ያለው ሕይወት ነው። ክርስቲያን የሚያድገው ወደጎን አይደለም፣ በቁመትም አይደለም! እድገቱ ክርስቶስን ወደ መምሰል ነው። የተጠራነው እገሌንና እገሊትን መስለን እንድንኖር ሳይሆን ክርስቶስን መስለን እንድንኖር ነው። የክርስቲያን የሕይወት ግብ ሰማይ መድረስ ብቻ ሳይሆን በምድርም ሳለን የክርስቶስን መልክ ተላብሰን መኖር ነው። ብዙዎች ክርስትናን በስም፣ በስርዓት ወይም በውጫዊ ምልክት ለመለካት ይፈልጋሉ።  ይህ የፈሪሳውያን ጠባይ እንጂ የክርስትና ሕይወት ገጽታ አይደለም። ጌታ ኢየሱስ የሚፈልገው የተለወጠ ልብን እንጂ አስመሳይን አይደለም። "ክርስቶስን መከተል በቃል ብቻ አይደለም። ሕይወታችንም የእርሱን ባሕርይ ሊያንጸባርቅ ይገባዋል።"                 ✨መምሰል ድካም አለው። አንድ ተዋናይ የተሰጠውን ገጸ ባህሪ መስሎ ወይም ሆኖ ለመተወን ትጋትን፣ ድካምን፣ ራስን መስጠትን ይጠይቃል። ክርስቲያንም ክርስቶስን ለመምሰል ሜካፕ መሰራት ሳይሆን በጸሎት፣ ቃሉን በማጥናት፣ ህብረት በማድረግ፣ በመንፈሳዊ አገልግሎቶች በመትጋት አልፎም በፀጋውና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው።  እኔ ክርስቲያን ነኝ ካልን አንዳንድ ቀን ሳይሆን ክርስቶስን የምንመስለው ሁልጊዜ ክርስቶስን በሐሳብ፣ በቃልና በሥራ መምሰል አለብን።       ✨ክርስቶስን መምሰል ማለት እንደ እርሱ መውደድ፣ እንደ እርሱ ማገልገል፣ እንደ እርሱ ይቅር ማለት፣ እንደ እርሱ ለአብ መታዘዝ ነው። የጌታ ትሕትና የሕይወቱ ጌጥ ነበር፤ እርሱ ጌታ ሆኖ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ። ይህም ታላቅነት በአገልግሎት እንጂ በሥልጣን እንዳልሆነ ያስተምረናል። ✨ክርስቶስን መምሰል መከራንም ይጠይቃል። ጌታችን እንዲህ አለ፦ "ማንም ሊከተለኝ ቢወድ፥ ራሱን ይካድ፥ መስቀሉንም በየቀኑ ተሸክሞ ይከተለኝ።" እርሱን መከተል ምቾትን ከመፈለግ ይልቅ ለእውነት መቆምን ይጠይቃል።         âœ¨  ክርስትናችን መምሰልን እየተወ ማስመሰልን መልመድ የለበትም። ንግግራችን እንደ ክርስቶስ፣ ተግባራችን እንደ ክርስቶስ፣ ሕይወታችን እንደ ክርስቶስ መሆን አለበት። ለታይታ የምናደርገው ነገር ሁሉ መቅረት አለበት። ሰው የምንረዳው ችግሩን መነገጃ አድርገን ካሜራ ደቅነን መሆን የለበትም። እግዚአብሔር ሸሽጎ በጓዳ እንደሰጠን እኛም የሰዎችን ችግር ሸፍነን በጓዳ ልንቸራቸው ይገባል። ክርስቶስን መምሰል የራስን ዝቅ ማድረግ ጌታን ማጉላት ነው።        ጸሎት           ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፦ ከማስመሰል ህይወት፣ ራስን ከማምለክ ህይወት ነጥቀህ አንተን በቃል ብቻ ሳይሆን በሕይወታችን እንድናሳይህ እርዳን። ሰዎች ርኛን ሲመለከቱ ክርስቶስን ማየት ይሁንላቸው። የአንተን ፈለግ መከተል፣ የአንተን ዱካ እየረገጥን መሄድ ይሁንልን። ትህትናህን አልብሰን፣ ፍቅርህን በልባችን ሙላ። መንፈስ ቅዱስ በነገር ሁሉ እርዳን። የምንሠራው ሁሉ ለክብርህ ይሁን። አሜን። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ኢየሱስ ለእኔ ያላረክልኝ ምን አለ                     ከማህፀን ያየኸኝ፤ በዓላማህ ያኖርከኝ፤ እንደ ዳዊት ከተረሳሁበት ያነሳኸኝ፤ ጸጋህን እንደ ልብስ አለበስኽኝ ጌታ ኢየሱስ ተመስገንልኝ።         እጆቼን ባዶ አልተውከኝም፣ ልቤን ተስፋ አልነሳኸውም፣ ከቀን ወደ ቀን ታማኝነትህን አሳየኸኝ፣ አዕምሮዬን ጠበከው፣ ከብዙ ጉድ አወጣኸኝ ጌታ ኢየሱስ ተመስገንልኝ።         ያልታየኝን አንተ አየኸው፣ ያልቻልኩትን አንተ ሰራኸው፣ የተሰበረውን ልቤን አከምከው፣ የተዘጉ ደጆችን ከፈትክልኝ፣ ያልጠየኩትን ሰጠኸኝ፣ ያላሰብኩትን ጨመርክልኝ፣ በረከትህ ቀድሞ ደረሰልኝ፣ ምህረትህም በፊቴ ሄደ ጌታ ኢየሱስ ተመስገንልኝ።                   የሰጠኸኝን ስቆጥር መጨረሻው አይታወቅም፣ ምህረትህ ከባህር ይሰፋል ታማኝነትህ ከዘላለም ያልፋል። አልተራብኩም ከስጋህ አብልተኸኝ፣ አልተጠማሁም ደምህን አስጎንጭተኸኝ፣ አልተረሳሁም መቃብር ድረስ መጥተህ ፈልገኽኝ ጌታ ኢየሱስ ለኔ ያላደረክልኝ ምን አለ?          ስለዚህ አመሰግንሃለው ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን!! ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ኢየሱስ           ✨የታረድከው ጌታ፤ በክብር በምስጋና፣ በይባቤ ያረከው ጌታ ታማኝነትህ ያልጎደለብን፣ ሁኔታዎች ሲገለባበጡ ፀንተህ የቆምክልን፣ ድል መንሻችን ኢየሱስ ሆይ ተመስገን።     ✨ኢየሱስ ሆይ እንወድሃለን፤ ኢየሱስ ሆይ እናከብርሃለን፤    ኢየሱስ ሆይ እንሰግድልሃለን፤ ኢየሱስ ሆይ ከፍ ከፍ እናደርግሃለን።  ለማንነትህ እንጂ ለስጦታህ አንዘምርም፤ ለፍቅርህ እንጂ ለበረከትህ ብቻ አንሰግድም።  አንተ ወድቀህ ያነሳኸን ጀግና፤ ሞተህ ያኖርከን ወዳጅ፤  ከናንተ በፊት እኔን ያስቀድመኝ ብለህ የሞት ፅዋ የጠጣህልን ኢየሱስ ሆይ እንወድሃለን።       ✨አንተ በረሃችንን የምታረካ፤ ጥማችን የምትቆርጥ ውሃችን፤ ለሊቱን ስንጓዝ የእሳት አምድ ሆነህ የምትመራን፥ በረሃውን ስንጓዝ ደመና ሆነህ የምትጋርደን፤ በጨለማችን ብርሃን፣ በእንባችን መጽናናት፣ በጦርነታችን ድል የሆንክ፣ በድካማችን ኃይል ነህ። ለአንተ አንደበታችን ከዝማሬ አይታክትም፣ ስምህን ከማመስገን ልባችን አይሰንፍም ኢየሱስ ሆይ ተመስገን።      ✨አለን ብለን የምንቆጥርህ ብቸኛና ውድ ሀብታችን፣ ዘመን ቢለወጥ የማትለወጥ አባታችን፣ የማትዋሽ አምላካችን፣ የማትተወን መድኃኒታችን፣ የማትደክም ረዳታችን፣ እንደ ቸርነትህ እንጂ እንደ ስራችን አልኖርንም። ኢየሱስ ሆይ ለዘለዓለም ተመስገን። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

እግዚአብሔር ሁን ያለውን ጉም አይጋርደውም፤ ድምጽን በድምጽ የሚሽር የበላይ ዳኛ ነው። እርሱ ያለው ከአድማስ እስከ አድማስ ያለከልካይ ይሆናል። ተመስገን Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

በክርስቶስ ኑሩ       
"በእኔ ኑሩ፥ እኔም በእናንተ እኖራለሁ፤ ቅርንጫፉ በወይኑ ግንድ ካልኖረ ፍሬ ሊያፈራ እንደማይችል፥ እናንተም በእኔ ካልኖራችሁ እንዲሁ ናችሁ።" — ዮሐንስ 15፥4
         ✨ክርስትና የራሳችንን ኃይል፣ እውቀት፣ ሀብት፣ ዝና፣ ስልጣን ተማምነን የምንኖረው ሕይወት አይደለም። ክርስቶስን አምነን የምንኖረው ጣፋጭ ሕይወት ነው። ክርስቶስ የምንኖርበት ከተማችን ስለሆነ በእኔ ኑሩ አለን።  ቅርንጫፍ ከወይኑ ግንድ ከተለየ እንደሚደርቅ ሁሉ እኛም ከክርስቶስ ተለይተን መንፈሳዊ ፍሬ ማፍራት፣ ስኬታማ ሕይወትም ሊኖረን አንችልም። ስለዚህ ግንዳችን ከሆነው ከክርስቶስ ጋር በየቀኑ መጣበቅ፣ ልብን በፊቱ በማፍሰስ፣ የክርስቶስን ፍቅር በመቀበልና ለሌሎች በማሳየት፣ በእምነት በመታዘዝ፣ በመንፈስ ቅዱስ በመመራት የራሳችንን ፍቃድ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፍቃድ በመመላለስ በክርስቶስ ውስጥ መኖር እንችላለን።                    ✨ይህን ማድረግ የልባችንን በር ለክርስቶስ እየከፈትን እርሱ በልባችን ተንሰራፍቶ እንዲኖርበት ያደርገዋል። ክርስቶስ በእኛ ውስጥ በመንፈሱ ይኖራል። እርሱ በእኛ ውስጥ ሲኖር ሕይወታችን ይለወጣል፤ ቁጣችን በትዕግስት፤ ጥላቻችን በፍቅር፤ ፍርሃታችን በእምነት ይለወጣል። ይህ የክርስቶስ ሕይወት በእኛ መገለጡ ማሳያ ነው።            ✨ቅርንጫፍ ከግንዱ እስከተጣበቀ ድረስ ብቻ ነው ፍሬ ማፍራት የሚችለው። ቅርንጫፉ ከግንዱ ጭማቂ እንደሚቀበል እኛም ከክርስቶስ ጸጋ፣ ኃይል እንቀበላለን። ብሎም ከክርስቶስ ጋር ስንኖር የመንፈስ ፍሬ እናፈራለን።       ✨ወዳጆቼ ዛሬ ከክርስቶስ ሊለዩን የሚሞክሩ ብዙ ነገሮች አሉ። የዓለም ፍቅር፣ የገንዘብ ፍላጎት፣ ኃጢአት፣ መንፈሳዊ ስንፍና፣ ምቾቶቻችን ሊላለዩን ይችላሉ። ጌታ ግን በእኔ ኑሩ ብሎ ይጠራናል። በእርሱ የሚኖር ሰው ከፈተና ንፁህ ይሆናል ማለት ሳይሆን ፈተናን ድል የሚነሳበት ጥበብ፣ ኃይል ይቀበላል ፈተናውንም ድል ይነሳል ማለት ነው። ✨ከእኛ የሚፈለገው ብዙ ድካም አይደለም። ከእርሱ ጋር የማያቋርጥ ሕብረት፣ ጸሎት፣ ንስሐ፣ ቅዱስ ቁርባን ነው። ልባችንን ለእርሱ መክፈት ራሳችንንም በእርሱ ላይ መጣል ነው። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

"ክርስቶስን ከልብህ አትለይ፤ እርሱ ከአንተ አይለይም።"
የልባችን ንጉስ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በልባችን ለአንድ ፍቅረኛችን ከምንሰጠውን ስፍራ በታች ለክርስቶስ አንስጠው። እርሱ ብቸኛ የልባችን ዙፋን የሚገባው ንጉሳችን ነው። ኢየሱስ ቀዳሚም ተከታይም የሌለው መውደዳችን ነው። ከልባችንም ከአንደበታችንም የማይለይ ውዳችን ነው። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፦ ልቤ ለአንተ ይሁን። ሐሳቤ ወደ አንተ ይመለስ። እግሬ በመንገድህ ይራመድ። ሕይወቴም ለክብርህ ይሁን። አሜን ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

እግዚአብሔር የገለጠውን በእምነት ተቀበል፤ ያልገለጠውን በትሕትና ተወው። john Chrysostom
እግዚአብሔር ራሱን በገለጠበት መጠን ማወቅ ግዴታ ነው። ራሱን ከገለጠበት በላይ ለማወቅ መጣር በተሸከምናት አዕምሮ የሚሆን አይደለም። ይህ የተሸከምነው ስጋ ደስታንም ሀዘንንም በሙሉነት መሸከም አይችልም። እግዚአብሔርን አቅም ኖሮን በሙሉነት ልንረዳው ይቅርና አንዳንድ ሰርፕራይዞችና ድንጋጤዎችን እንኳ መቆጣጠር አቅቶን ራሳችንን እንስታለን። እግዚአብሔር ለእኛ አዕምሮ በሚበቃ መልኩ ራሱን ገልጧል። የገለጠው ብቻውን በቂ ነው። የተገለጠውን ተረድተን ሳንጨርስ ስላልተገለጠው ማንነቱ ለማወቅ አንቆፍር። እግዚአብሔር ማለት የተረዳነውም ያልተረዳነውም፣ ያወቅነውም ደግሞም ያላወቅነውም ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን እንዳናውቀው አይከለክልም፤ በተቃራኒው እርሱን እንድናውቀው ይጋብዘናል። ነገር ግን ከገለጠው በላይ በግምት ወይም በሰው ፍልስፍና ለመድረስ መሞከር ተገቢ አይደለም። እኛ የምናውቀው እርሱ በቃሉና በክርስቶስ የገለጠልንን መጠን ነው። እግዚአብሔርን እንደቃሉ እንድናውቀው ይርዳን፤ መንፈስ ቅዱስ ይግለጥልን። አሜን! ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ጸሎት
" ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።" ሰቆ 3:23
        አቤቱ የልቤ አምላክ እግዚአብሔር አመሰግንሃለሁ። ማደሪያህ የተባረከ ይሁን። ዓይኖቻችንን ከፍተህ ብሩኹን ቀን እንድንመለከት ስለረዳኸን ተመስገን። ምህረትህ የመቆማችን ምስጢር ነውና ምህረትህ ምርኩዝና እድል ስለሆነን እናመሰግንሃለን።       አቤቱ ልዑል ሆይ እርጅና የማያውቅህ የትላንቱን ጭንቀት፣ ያለፈውን ሃዘን፣ የከረመውን ስህተት፣ የተጫነንን ሸክም አራግፈህ የፍቅር ጸዳል ስላበራህልን እናመሰግንሃለን።         አባት እግዚአብሔር ታማኝነትህ ብዙ ነው። ሰዎች ሲለዋወጡብን፣ ሁኔታዎች ሲቀየሩብን፣ ዓለም ስትናወጥብን አንተ ግን አልተለወጥህም፤ ሳትንሸራተት በብዙ ታማኝነት ደግፈኸናል። ዛሬም በአንተ ላይ ልባችን ይወድቃል።          አንተ ከክፉ ወጥመድ፣ ከማንኛውም ስውር ፈተና፣ ከራሳችንም ጭምር ጠብቀን። ቃልህን ቃላችን አድርግልን ለሰው ጠገን አድርገን። በሄድንበት የአንተን መዓዛ የምንነሰንስ ባሪያዎችህ አድርገን። ለደከሙት ብርታት፣ ለታመሙት ፈውስ፣ ለተጨነቁ እውነተኛ መጽናናት፣ ለታወኩ የአዕምሮ ሰላም ነህና ይህን ለሚሹ ሁሉ ዛሬ ችግራቸው ሁሉ በኃይልህ ይተካላቸው።         አሜን ላሉት ሁሉ ይደረግላቸው። በምትወደው ልጅህ በኢየሱስ ስም። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ማንም አይፈልገኝም፣ ሰው እረስቶኛል ለምትሉ ሁሉ
“ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም” (ዮሐንስ 14፥18)
✨ይህ ቃል ልብን ከማሞቅ አልፎ እቅፍፍ አድርጎ ይደግፋል። መተው፣ መረሳት የሰው ልጅ ብርቱ ህመም ነው። እኛ ብዙዎችን እንደረሳነው ሁሉ እኛም በሌሎች ዘንድ እንረሳለን። የረሳናቸውን አስታውሰን ከምንፀልይላቸው ይልቅ የረሱንን አስታውሰን እናዝናለን።     âœ¨  ሀብታም ብትሆንም ትረሳለህ: ድሀ ብትሆንም ትረሳለህ፣ ትንሽ ብትሆንም ትረሳለህ : ትልቅ ብትሆንም ትረሳለህ፣ ወንድ ብትሆንም ትረሳለህ ሴት ብትሆኚም ትረሺያለሽ። ላለመረሳት፣ ላለመተው ምንም ዋስትና የለንም። እኛ እንኳን አጠገባችን ያሉ ሰዎችን ይቅርና እግዚአብሔርን የምንረሳ ደፋሮች፣ አዝለነው የምንዞረውን ሞትን የምንረሳ ምስኪኖች ነን።       âœ¨  እናቴ በቀን ውስጥ በትንሹ ሁለት ጊዜ ትደውላለች። ምግብ በላህ? ራስህን ጠብቅ፣ አታምሽ በጊዜ ና! የሁልጊዜ ድምጿ ነው። ወደቤት እስክገባ ደጅ ደጅ እያየች ትጠብቀኛለች፤ ከለመደችው ሰዓት ገፋ ብሎ ካመሸሁባት ልብስ ይዛ አደባባይ ቆማ ትጠብቀኛለች። ለቤተሰብ ሁሉ ደውላ ልጄ ጠፋ ብላ ታስጨንቃቸዋለች። የእርሷ እንዲህ መጨነቅ ራሷን መጉዳት ለኔ ቢከብደኝም እውነተኛ ፈላጊዬ እንደሆነች ሳስብ ደግሞ ደስታ ይሰማኝ ነበር። እርሷን ካጣሁ በኋላ ስልኬ ላይ ስልኳ መጮህ ሲያቆም፣ በር በር አሻግሮ የሚጠብቀኝ ሳጣ ልቤ ያዝናል። እኔ እናቴን በሞት አጥቼ ነው ልበ አምላክ ዳዊት ግን በህይወት እያሉ ነው የረሱት የዘነጉት እግዚአብሔር ግን አስታዋሽ አባትና እናት ሆነው።     âœ¨  ዛሬም ይህ ስሜት የሚሰማችሁ ሰዎች ትኖራላችሁ። አንዳንድ ጊዜ በሕይወታችሁ ብቻችሁን የቀራችሁ ይመስላችኋል። ሰዎች ሊተዉን ይችላሉ፣ ጓደኞች ሊርቁን ይችላሉ፣ ሁኔታዎችም ልባችንን ሊያስጨንቁ ይችላሉ። ነገር ግን ኢየሱስ የሰጠን ተስፋ ከሁሉ በላይ ነው፤ “አልተዋችሁም” ይለናል። ሁልጊዜ ከእኛ ጋር ነው  ፈፅሞ ከህይወታችን አይለይም ማለት ነው።       âœ¨á‰ á‹°áˆľá‰łá‰˝áŠ•áˆ ሆነ በሐዘናችን፣ በስኬታችንም ሆነ በፈተናችን እርሱ አይለየንም። እኛ እርሱን ስንፈልገው ይቀርበናል፣ ስንጸልይ ይሰማናል፣ በቃሉም ያበረታታናል። ምንም ዓይነት ችግር ቢኖር እግዚአብሔር አይተወንም። እርሱ የታመነ አምላክ ነው። ሰው ከጎናችን ቢሆን ጊዜያዊ ነው ጊዜያዊ ያልሆነው አምላክ ለዘላለም ከእኛ ጋር ነው።     âœ¨ አንድ ፅሁፍ ሳነብ የወደድኩት ነው። "አንድ በእድሜ የገፉ አባት የእጅ ስልካቸውን ይዘው ሰሪ ቤት ይወስዱታል። ልጄ ይቺ ስልክ ተበላሽታብኝ ነው እባክህ አስተካክልልኝ ይሉታል። ልጁም ተቀብሎ ስልኩን ሲፈትሸው ስልኩ ምንም አልሆነም ይሰራል። አባቴ ስልኩ እኮ ምንም አልተበላሸም ይሰራል አላቸው። እኙህም አባት ታዲያ ለምንድነው ልጆቼ ደውለውልኝ የማያውቁት አይፈልጉኝም ማለት ነው" ብለው ልባቸው እያዘነ ስልካቸውን ይዘው ተመለሱ።  ልጅ ወላጁን ይተዋል፣ ይረሳል፤ ወላጅም ልጁን ይረሳል። ለአፍታ ግን አይኖቹን ከእኛ ላይ የማይነቅል፣ በምንም ሁኔታ ውስጥ የማይተወን አልተዋችሁም ብሎ ቃል የገባልን ጌታ አለ።       âœ¨ á‹¨áˆ˜á‰°á‹áŁ የመረሳት ስሜት ሲሰማችሁ ይህን አስታውሱ የማይረሳው ጌታ ከእኔ ጋር ነው በሉ!! ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ምድረ በዳ የሆነባችሁ ምንድነው?
"አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።" (መዝሙር 63፥1)
           ያማረ የተዋበ ከተማ እንዳለ ሁሉ አንዳች የሌለበት ምድረበዳም አለ። ምድረበዳ ስንል አሸዋ፣ ደረቅ ስፍራ፣ ውሀ የሌለበት በረሃ፣ ለስጋችን የማይመች ስፍራ ነው። ልክ እንደዚሁ ሁሉ የነፍስም ምድረ በዳ አለ። ሰላም ማጣት፣ ብቸኝነትና ሀዘን ውስጥ መግባት፣ ተስፋ መቁረጥ የነፍስ ምድረበዳ ውስጥ መግባት ነው።            ዳዊት ንጉስ ነው። ይቺ ዓለም ንግስናንም ምድረበዳንም የምናይባት ናት። ይሄንን መዝሙር እየዘመረ ያለው በንግስናው ዙፋኑ ላይ ሳይሆን እየተንከራተተ በምድረ በዳ ተሰድዶ፣ በጠላቶቹ ተከቦ ነው። በዚህ ጊዜ ለስጋው ምቹ ሁኔታን ማግኘት ሲገባው ፍላጎቱ የነፍሱን ምድረበዳ የሚያረካውን እግዚአብሔርን ማግኘት ነው።        በዚህ ጊዜ ያልተጠማ አለ ማለት አይቻልም። በምድረ በዳ ውስጥ ያላለፈ ወይም እያለፈ ያልሆነ የለም። ምድረበዳ ውስጥ ከሆንን የተጠማነው ምንድነው? ገንዘብ፣ ፍቅር፣ ስልጣን፣ እግዚአብሔርን?  ወይም ምን? ዳዊት ግን ለደረቀው አፉ ውሀ እያስፈለገው ነፍሴ አንተን ተጠማች ይላል። ምድራዊ ነገሮች ጊዜያዊ እርካታን ይሰጡን ይሆናል እንጂ ለነፍሳችን ጥማት እርካታን ሊሰጡን አይችሉም።        ዳዊት ምድረ በዳ ውስጥ ሆኖ ጠላቶቼን መደምሰሻ ኃይል ስጠኝ፣ ከዚህ ምድረበዳ የምወጣበትን መንገድ አበጅልኝ፣ ወደ ንግስናዬ መልሰኝ ሳይሆን የማለዳ ተግባሩ እግዚአብሔርን መፈለግ፣ ወደ እግዚአብሔር መገስገስ ነው። ወደ እግዚአብሔር የምንገሰግሰው በልባችን ነው። እግራችን ሊያረፍድ ይችላል ልባችን ግን ሳይዘገይ ገስግሶ ይደርሳል። እኛ እግዚአብሔርን የምንፈልገው ነገሮች ባልተሳኩልን ጊዜ፣ ነገሮች በተበላሹብን ጊዜ ነው። እግዚአብሔርን እንደ አደጋ ጊዜ መውጪያ ብቻ የምንገለገልበት መሆን የለብንም። ከእርሱ የምናስቀድመው ነገር ሊኖር አይገባም። በደስታችንም፣ በሃዘናችንም፣ በጉልበታችንም፣ በስብራታችንም፣ በጉብዝናችንም ወቅት ወደርሱ ልንገሰግስ ይገባል።          ያለ እግዚአብሔር ምቹው ቦታ ምድረበዳ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር ምድረበዳው ገነት ነው። በሕይወታችን ምድረበዳዎች የሚገጥሙን እግዚአብሔርን አጥብቀን እንድንፈልገው ነው። እግዚአብሔርን ለመፈለግ ለማግኘት ምቹ ቦታ ሳይሆን ምቹ ልብ ብቻ ነው የሚያስፈልገው። ዳዊት በምድረበዳ እግዚአብሔር ከፈለገ እኛም በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እግዚአብሔርን ፈልገን ማግኘት እንችላለን። ጸሎት         አቤቱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ የነፍሳችን እርካታ ነህ፣ የህይወታችን ልምላሜ ነህ ነፍሳችን በአንተ ትርካ፤ ህይወታችን በአንተ ትለምልም። ምድረበዳችንን አርካው። ረድዔታችን ሆይ ተመስገን። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

መባረክን ተባረኩ ✨እግዚአብሔር ዘንበል ይበልላችሁ።      ✨ከዘመን መለዋወጥ፣ ከቀናት መፈራረቅ በስተጀርባ የማይለወጥ ጽኑ ደስታና ውስጣዊ እርካታን ይስጣችሁ።    ✨ነፍሳችሁ ሁልጊዜ ሰላም የምታገኝበትን መንገድ ይምራችሁ።      ✨በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎች ሁሉ የእናንተን ብርሃን አይተው የሚደሰቱ ያድርጋችሁ።        ✨ህይወታችሁ እንደ ምንጭ ውሃ ሁልጊዜ የሚፈልቅ፣ እንደ ፅኑ ዛፍ ሁልጊዜ የሚያፈራና ለሌሎች ጥላ የሚሆን ያድርገው።     ✨መንገዳችሁ ከእሾህና ከእንቅፋት የጠራ ህይወታችሁ ደግሞ እንደማለዳ ፀሐይ ብሩህና ተስፋ የሞላበት ይሁን።       ✨ፍቅራችሁ እንደ ወይን ጠጅ በቆየ ቁጥር የሚጣፍጥ፣ ትዕግስታችሁን እንደ ባህር ሰፊ ያድርገው።       ✨ክፉ አይንካችሁ፣  ደስታ አይራቃችሁ፣  ያሰባችሁት ይቅናችሁ፣ ቤታችሁ በሳቅ ይሙላላችሁ፣ ወጥታችሁ በሰላም ግቡ፣ መልካም ነገር ይሁንላችሁ። በጌታችን በኢየሱስ ስም አሜንንን። Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

የማለዳ ጸሎት የዘላለም አምላክ፣ የሰማይና የምድር ፈጣሪ፣ የሕይወቴ እረኛ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፍጹም በሆነ ምስጋና በፊትህ እሰግዳለሁ። ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኸኝ፣ እስትንፋስን ሰጥተህ በሕይወት ያቆየኸኝ፣ ከጭንቅና ከብዙ መከራ በቸርነትህ የጋረድኸኝ አንተ ነህ። ጌታ ሆይ፦ ስለማውቀውና ስለማላውቀው፣ በስውርና በግልጽ ስለደረስክልኝ ረዳትነትህ ስምህ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን። በድካሜ ጊዜ ብርሃን ስለሆንኸኝ፣ በመውደቄ ጊዜ እጅህን ዘርግተህ ስላነሳኸኝ፣ ዓለም ስትፈርድብኝ አንተ ግን በፍቅርህ ስለቀረብኸኝ አመሰግንሃለሁ። አቤቱ የቆምኩበትን መንገድና በፊቴ ያለውን ሕይወት አንተ ታውቃለህ። በዚህ ፈታኝና እረፍት በሌለው ዓለም ውስጥ ያለ አንተ ረዳትነት መቆም አልችልም። ስለዚህ ዛሬ አእምሮዬን ከሚያውኩ ድንገተኛ ፍርሃቶች፣ ከጭንቀትና ተስፋ ከመቁረጥ መንፈስ እንድትጠብቀኝ እማጸንሃለሁ። ​ እግሮቼ በሰላም መንገድ ላይ ይሂዱ፤ ውሳኔዎቼንና ሥራዎቼን ሁሉ ሰማያዊ ጥበብህን በመሙላት ባርክልኝ። ​ ለምወዳቸው ሰዎች ሁሉ ጤናን፣ ፍቅርንና አንድነትን ስጥ። በየቀኑ ከክፉ ነገር ሁሉ ጠብቃቸው። ​ በሀገሬ ላይ የሚፈሰውን ደም ገድብ። ሁከትንና ጦርነትን አስወግድ፤ ሰላምህንና በረከትህን በምድራችን ላይ አውርድ። የተራቡትን አጥግብ፣ የታመሙትን ፈውስ፣ ያዘኑትንም አጽናና። በምትወደው ልጅህ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜንን!! Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ለራሳችሁ ብቻ አታስቡ ✨ከኮረናም ከኤች አይ ቪ'ም ከካንሰርም በላይ እያንዳንዱን ሰው እየጎዳ ያለው በሽታ እኔነት ነው። እኔነት ማለት እኔ ብቻ ልክበር፣ እኔን ብቻ ይመቸኝ፣ እኔ ብቻ ልኑር፣ የእኔ ብቻ ይሙላ፣ እኔ ብቻ ይመርንኝ ብሎ በስግብግብነት መጥበብ ነው። ብዙ ሰው ራሱን በእኔነት አጥር አጥሮ በስግብግብነት ራሱን ገንዞ ይኖራል። በእኔነት የምናሳካው ስኬት የምንደርስበት ከፍታ የለም።         ✨እግዚአብሔር ከሚፀየፈው በሽታ አንዱ እኔነት ነው። ለዚህ ነው ከእናነት አጥር እንድንወጣ የሚያዘን።  
በፊልጽ 2:4 እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።”
          ✨እያንዳንዱ ለልሹ የሚጠቅመውን አይመልከት ማለት ሰው ፍቃድ፣ ስሜት፣ ዓላማ ያለው ፍጡር ነውና ለልሹ ምንም አያስብ፣ ፍላጎቱን ይግታ፣ራሱን ፈፅሞ ይርሳ ማለት አይደለም።  ሃሳቡ በራሱ ጥቅም ላይ ብቻ አያጠንጥን፣ መነሻውን ለልሴ ብሎ አይጀምር፣ ልቡን በስግብግብነት አይሙላ ማለቱ ነው። ✨ሰው እኔነትን ብቻ ገንዘቡ ሲያደርግ ከሰውም ከእግዚአብሔርም ይነጠላል። ክርስትና ከእኔነት ወደእኛነት መለወጥ ነው። "እያንዳንዱ ለልሹ የሚጠቅመውን አይመልከት” ሲል፣ ራሳችንን ፈጽመን እንድንረሳ ወይም ፍላጎታችንን እንድንበድል ማለቱ አይደለም። ይልቁኑ፣ እይታችን በራሳችን ጥቅም ላይ ብቻ እንዳይታጠርና ልባችን በስግብግብነት እንዳይጠብብ ማስጠንቀቂያ ነው። ልሾ ወዳድነት ሰውን ከእግዚአብሔርም ከሰውም ይለያል። እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት የሚጀምረው ከእኔነት ወደ "እኛነት" ስንሻገር ነው።          ✨ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የራሱን ጥቅም፣ የራሱን ክብር፣ የራሱን ፍላጎት አልፈለገም። ክብሩን ጥሎ ክብራችን ሆነ፣ ጥቅሙን ጥሎ ለጥቅማችን ሞተልን።   
" በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።” (ፊልጵስዩስ 2:5)።
✨በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረው አሳብ እኛን ለማዳን ራሱን ባዶ ማድረግ፣ የባሪያን መልክ መያዝ ነበር እኛም የክርስቶስን ፈለግ መከተል ይኖርብናል። ለምናውቀው ሰው ብቻ ሳይሆን ለማናውቀውም የክርስቶስ ደም ለፈሰሰለት የሰው ልጅ ሁሉ መልካምና ቅን መሆን አለብን።                ✨ባልንጀራችን ሩቅ የምንፈልገው አይደለም፤ በዙሪያችን ያሉ የኛን ፍቅር፣ ፀሎት፣ እርዳታ የሚሹ ሁሉ ባልንጀራዎቻችን ናቸው። ለእነዚህ ሰዎች ሲያዝኑ ማፅናናት፣ ሲቸገሩ መርዳት፣ ሲራቡ ማብላት ይገባል። የሌሎች ህመም ህመማችን፣ የሌሎች ስኬት ስኬታችን መሆን አለበት። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ልባችሁ በደስታ እንዲሞላ ትፈልጋላችሁ?   
  " ልቡ የሚያዝን ሰው ዘመኑ ሁሉ የከፋች ናት፤ የልብ ደስታ ግን ሁልጊዜ እንደ ግብዣ ነው።" ምሳሌ 15:15
      âœ¨áˆ•á‹­á‹ˆá‰łá‰˝áŠ•áŠ• የሚወስነው ሁኔታ ሳይሆን የልባችን አመለካከት ነው። ምድር ላይ ሀዘንም ደስታም አለ። ሀዘንንም ደስታንም የሚያስተናግደው ልባችን ነው። ግን እንዴት ነው የሚዬስተናግደው?  ❄️ አንዳንዱ ችግር ሲገጥመው በችግር ውስጥ እድልን ያያል፤ ችግሩን እንደ መልካም አጋጣሚ ይቆጥረዋል። አንዳንዱ ደግሞ በመልካም አጋጣሚ ውስጥ እንኳ ል ችግርን ብቻ ያያል። ልዩነቱ የችግሩ መግዘፍና ማነስ ሳይሆን ልዩነቱ ልባቸው ውስጥ ነው። ሕይወታችንን እያጨለመ ያለው ችግራችን ሳይሆን ሾለ ችግር ያለን አመለካከት ሊሆን ይችላል።     âœ¨  ዛሬ ሼል የለህም? ገንዘብ አንሶሃል? ብዙ ፈተና እያለፍክ ነው? .... ነገር ግን እነዚህ ነገሮች የህይወት መጨረሻ አይደሉም። እነዚህ ሁሉ ከውጪ የመጡ ፈተናዎች ናቸው አንተ ግን ውስጥህን በተስፋ ሙላ፣ በምስጋና ሙላ፣ በእምነት ሙላ። ✨አበቃልኝ አትበል! በእግዚአብሔር እቀጥላለሁ በል። ጨልሟል አትበል! እግዚአብሔር ያነጋልኛል በል። ተዘጋ አትበል! እግዚአብሔር ማንም የማይዘጋው በር ይከፍትልኛል በል። ተሸንፌያለሁ አትበል! እግዚአብሔር እያስተማረኝ ነው በል። የዛሬ ሐዘንህ የነገ ደስታህን ሊያዘጋጅ ይችላል። የዛሬ እንባህ የነገ ምስክርነትህ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር የሰጠህን ሕይወት በፍርሃት ሳይሆን በእምነት ኑር። በማጉረምረም ሳይሆን በምስጋና ኑር። በተስፋ ቁም፤ በድፍረት ሥራ፤ በእግዚአብሔር ታመን።       âœ¨ የሕይወታችን አስኳል ያለው ልባችን ላይ ነው። ልባችን ሃዘንን ካረገዘ የሚወለደው ሁሉ ህይወትን የሚያከብድ ተስፋ መቁረጥ፣ ቂም፣ ፍርሃት፣ ጥላቻ ነው። ልባችን ደስታን ሲመላ ህይወታችን በእግዚአብሔር በረከት ይጥለቀለቃል።
" ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።" ፊልጵ 4:4
✨ደስታ ምርጫ ሳይሆን የክርስቶስ ትዕዛዝ ነው። አለመደሰት የእግዚአብሔር ቃል አለመታዘዝ ነው። ስለዚህ ልባችንን ዕለት ዕለት ደስተኛ ልናደርጋት ይገባል። የልባችንን ደስታ በሀብት ለማምጣት፣ በሁኔታ ለማግኘት አንናፍቅ በዚህ አይመጣም። ይልቁንም በእግዚአብሔር በመታመን፣ በምስጋና እንዲሁም በሰላም የሚመጣ ደስታ ነው። እንዲህ ያለ ሰው ችግር ቢገጥመውም ተስፋውን አያጣም። ክርስቶስ በልባችን ሲነግሥ በሁሉም ሁኔታ ውስጥ የማይጠፋ ደስታ እናገኛለን። ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ኢየሱስ ይጠጋጋን ✨እውነተኛ ወዳጅ ለልብ የተጠጋ ነው። አስመሳይ ወዳጅ ግን ለኪሳችን የተጠጋ ነው። እውነተኛ ወዳጅ ከአስመሳይ ወዳጅ በቁጥር ያነሱ ናቸው። እውነተኛ ወዳጅ በድንገት የሚገኙ ሳይሆን የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው። ዓለም ላይ ያለውን ብርና ወርቅ ከማግኘት በላይ አንድ እውነተኛ ወዳጅ ማግኘት ይበልጣል። ምክንያቱም ወርቅና ብር በሕመም ቀን አያስታምሙም፣ ብርና ወርቅ የሰውን ቦታ አይተኩም፣ ልባችን ሲሰበር አያጽናኑንም። እውነተኛ ወዳጅ ግን የችግሮች ሁሉ መፍትሄ፣ የህይወትም መድኃኒት ነው። በአስመሳይ ሰዎች ህይወት ሲከብድ በእውነተኛ ወዳጅ ደግሞ ህይወት ይቀላል። ✨ ሰው ሁሉ ወዳጅ አይደለም፤ ጓደኛም ሁሉ ወዳጅ አይደለም። ወዳጅ በቀን በፀሀይ መብራት አብርተን ብንፈልግ የማናገኘው እግዚአብሔር ብቻ የሚቸረን ስጦታ ነው። ምድራዊ ወዳጆቻችን ቀን ሲጥል ገሸሽ ይላሉ፣ በጥቅም ሊለዩን ይችላሉ፣ ከኛ ጋር እስከዘመን ፍፃሜ ለመጓዝ በጨረታው አይገደዱም። ከወዳጅ በላይ ወዳጅ የሆነ ግን አንድ አለ። እርሱም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይባላል። ሰዎች የልባችንን እንባና ስብራት ላያዩልን ይችላሉ፤ አንዳንዴም የውስጣችንን ምስጢር ስንነግራቸው በቁስላችን ላይ እንጨት ሊሰዱበት ይችላሉ። ኢየሱስ ግን ሳይፈርድብን የሚያደምጥ፣ በኃጢአትና በበደል ስንወድቅ እንኳ በምሕረቱ እጆቹን ዘርግቶ የሚቀበለን ወዳጅ ነው። ለልብ የሚጠጋጋ ወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።  
   “ብዙ ወዳጆች ያሉት ሰው ይጠፋልል፤ ከወንድም ይልቅ አጥብቆ የሚጠጋጋ ወዳጅ አለ።” (ምሳሌ 18:24)
ďťż        âœ¨áŒŒá‰łá‰˝áŠ• ኢየሱስ ወደኛ የመጣው ስጋን የለበሰው ወዳጅ ሊሆነን ነው፣ ለህመማችን መድኃኒት ሆኖ ሊወዳጀን ነው። ኢየሱስን ወዳጅ ያደረገ ለሰው ወዳጅ መሆን ይችላል፣ ሌሎችን ያለምክንያት መውደድ ይጀምራል፣ ጥቅምን ሳያይ ፍቅርን ያስቀድማል፣ ቅናትን አስወግዶ መልካምነትን ገንዘቡ ያደርጋል፣ ከወንድም ይልቅ አጥብቆ የሚጠጋጋ፣ ሰውን ከነጉድለቱ የሚቀበል ይሆናል።     ✨ እውነተኛ ወደሆነው ወዳጅ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኑ ቅረቡ! ፊቱ ብታለቅሱ የማይታዘባችሁ፣ ማጣታችሁን ብትነግሩት የማይጠየፋችሁ፣ ኃጢአታችሁን እያወቀ የሚያቅፋችሁ፣ ሸክማችሁን የሚያራግፍላችሁ ብቸኛ ወዳጅ ነው።  ሰው ንቋችኋል እርሱ ግን ከእናንተ ጋር ማዕድ ይቆርሳል። ሳንፈልገው ፈልጎን በራችንን ያንኳኳል፣ ራሳችንን እየዳበሰ ያጽናናናል።     ይህ ኢየሱስ ይጠጋጋችሁ!! ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

ይስማችሁ!! ✨ ሰውማ እንኳን ልቡን ጆሮውን ይነሳሃል።  âœ¨áˆ°á‹áˆ› የራሱን ችግር ሰው ላይ ተንፍሶ ያንተን ችግር ለመስማት እድል አይሰጥህም።   âœ¨ ሰውማ የራሱ ህይወት፣ ጭንቀትና ውጥረት ስለሚበዛባበት የሌላውን ሰው ስሜት ለመሸከም የሚያስችል ስሜታዊ አቅም ያጣል። ✨ሰውማ በትዕግስት ተረድቶ ከመደገፍ ይልቅ ነገሮችን በራሱ መነፅር አይቶ ይፈርድብሃል።  âœ¨áˆ°á‹áˆ› ለመረዳት ሳይሆን መልስ ለመስጠት ይሰማሃል። ወዳጄ ሆይ፦     
እግዚአብሔርማ
"ገና ቃል ከአንደበቴ ሳይወጣ፥ አቤቱ፥ አንተ ሁሉን አወቅህ።" — መዝሙረ ዳዊት 139:4    â„️ ገና ቃል ሳታወጣ በውስጥህ ያለውን ስሜት በደንብ ይረዳሃል። ያልተደራጀውን ሃሳብህን በሙሉ አስቀድሞ ያነበዋል። ኮልታፈነትህን አስተካክሎ ይሰማሃል።      
እግዚአብሔርማ
❄️ እንኳን ለሰው ለራስህም ግራ የገባህን የልብህን ያውቅልሃል። ሳይሰለችህ ያለ ምንም ፍርድ በፍጹም ፍቅር ይሰማሃል።        እግዚአብሔርማ      â„️ ከሰው ያጣኸውን እውነተኛ መደመጥ፣ መረዳትና እረፍት ይሰጥሃል።           
ምን እንደምትነግረው እያወቀ የሚያዳምጥህ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X

photo content

ሰላም ለእናንተ ይሁን! በውድ እናቴ ሞት ምክንያት በደረሰብኝ ከባድ የሃዘን ወቅት በአካል በመምጣት፣ በስልክ በመደወልና በፅሁፍ መልዕክት በማፅናናት አብራችሁኝ ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው። አመሰግናችኋለሁ። ወንድማችሁ አዶኒ

ተመስገን በየዕለቱ ሸክማችንን አንከባለህ ደስታን የምታስታጥቀን፣ ደከመኝ ብለህ ቸል ሳትለን በትዕግስት ያዘልከን፣ እፎይ ያልንብህ ማረፊያችን እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሃለን።        በፊታችን፣ በኑሯችን፣ በሕይወታችን የማይቻሉ የሚመስሉ ነገሮችን እንድናምንብህ ልባችን እንዳይርድብህ ልዑል ሆይ ለመንህ።        እኛ ላይ ማየት የምትወደውን አንዳች ነገር ሳታይ እንዳትመለስ ዓይኖችህን እንዳናስርባቸው የፈተልከውን ነጩን ሸማ ኢየሱስን አልብሰን።         እያበጀኸን፣ እየሰራኸን ነውና በናዝሬቱ ጌታ በኢየሱስ ስም ተመስገን። አሜንን ✍አዶኒ              Telegram👉 t.me/adonigospel    Whatsapp👉 https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X