cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

PENTECOSTAL TUBE

የመንፈሳዊ ትምህርቶች የቴሌግራም ቻናል ይህንን ቻናል ጆይን በማድረግ በእግዚአብሔር ቃል ትምህርት ይለምልሙ፣ይባረኩ። የእግዚአብሔር ቃል ታሪካችሁን ይቀይራል። የእግዚአብሔር ቃል ፍፃሜያችሁን ያሳምራል። በዚህ ቻናል 📍ከ350,000📍 በላይ ትምህርቶች ታገኛላችሁ። የእግዚአብሔር ፀጋ ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን:: ለወዳጅዎ ሼር ሼር ሼር ሼር ማድረግ አይርሱ

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
822
Obunachilar
-124 soatlar
-17 kunlar
-430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

💐 ሬማ ዴይሊ(ሬማ በየእለቱ) ዕለታዊ የእግዚአብሔር እንጀራ መንፈሳዊ ዕይታ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1 : 17-19 💐መንፈሳዊነት ከሚለካባቸው መለኪያዎች አንዱ ጤናማ መንፈሳዊ ዕይታ አንዱ ነው። መንፈሳዊ ዕይታ ሲባል እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ ከሚያይበት አቅጣጫ የማየት ብቃት ማለት ነው።መንፈሳዊ ዕይታ እግዚአብሔር እንደሚያየው ማየት ነው። ዕይታ ውጫዉ ሳይሆን ውስጣዊ ነው። ዕይታ የሚለውን የበለጠ የሚገልፀው የእንግሊዝኛው ቃል ይመስለኛል።ዕይታ የሚለው INSIGHT ነው። IN ---የውስጥ SIGHT---ዕይታ። ስለዚህ ዕይታ ከልቦና አይን ጋር የተቆራኘ መሆኑን እንረዳለን። 💐በመንፈሳዊ ቋንቋ ዕይታ ማለት ከመንፈሳዊ አለም ጋር ተግባብተን የምንኖርበት የልቦና ብርሃን ነው።መንፈሳዊ ዕይታ አስተሳሰብን፣ መረዳትን፣ምልከታን፣ በአጠቃላይ የአዕምሮን ቅኝት የሚመለከት ጉዳይ ነው። 💐 ከላይ በመግቢያ ጥቅሳችን ላይ እንዳነበብነው አዲስ ፍጥረት የሆነ አማኝ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ያደርግ ዘንድ ይበልጥ እግዚአብሔርን ማወቅ እንዳለበት ይናገራል። ሐዋርያው ጳውሎስ የአይን መከፈት ወይም የልቦና አይኖች መብራት ከእግዚአብሔር ጋር ላለን መንፈሳዊ ግንኙነት ዋነኛ ነገር መሆኑን እያስረዳ ነው። 💐 አይን እንዴት ይከፈታል??? ብዙ ጊዜ የአይን መከፈት አስፈላጊ እንደሆነ ይሰበክና እንዴት አይን እንደሚከፈት ግን ይዘነጋል። ሐዋርያው ጳውሎስ ሁለት መንፈሳዊ ምስጥራትን ጠቅሷል። 1ኛ የጥበብ መንፈስ -----ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ማድረግ እንድንችል መንፈስቅዱስ የሚሰጥን ጥበብ ነው። 2ኛ የመገለጥ መንፈስ---- እግዚአብሔርን በመንፈስ ማወቅ የሚያስችል የመንፈስቅዱስ አሰራር ነው። 💐 አማኝ የጥበብና የማስተዋል መንፈስን ሲካፈል የሚረዳቸው መንፈሳዊ እውነታዎች 1ኛ የመጥራቱ ተስፋ --በክርስቶስ የመጠራትን(የመዳንን ምስጢር ይረዳል። 2ኛ በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደሆነ ይረዳል። 3ኛ ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ ይረዳል። 💐የጥበብና የማስተዋል መንፈስ ለአማኝ የአይን መከፈት ወሳኝ ናቸው። ምክንያቱም እግዚአብሔርን በጭንቅላት ብቻ መረዳት አንችልም። እግዚአብሔር ከጭንቅላታችን ያለፈ አምላክ ነው። የእግዚአብሔር ጥበቡ ማስተዋሉ በሰው አዕምሮ የማይመረመር እጅግ የላቀ አምላክ ነው። ለዚህ ነው የጥበብና የመገለጥ መንፈስ ያስፈለገው። 💐እግዚአብሔርን ያለ እግዚአብሔር እርዳታ ማወቅ አይቻልም። አንዳንድ ጠቢብ ነን የሚሉ ሰዎች እግዚአብሔርን በራሳቸው ጥረትና ልፋት ለማወቅ ይሞክራሉ። ነገር መቼም አያውቁትም። 💐እግዚአብሔር ወደተናገረው ነገር መድረስ የሚቻለው እርሱ ያየልንን ማየት ሲቻል ብቻ ነው።መንፈሳዊ ዕይታችን ከተንሸዋረረ ህይወታችንም እንደዛው ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን እለት እለት እንዲከፍት የጥብና የማስተዋል መንፈስ እንዲሰጠን አጥብቀን ልንፀልይ ይገባል። እለት እለት የእግዚአብሔርን ቃል እናሰላስል። ©✍ነቢይ መሳይ እግዚአብሔር ይባርኮት!✋🙏 ትውልድ በእግዚአብሔር ቃል ይለወጣል!! ትውልድ በእግዚአብሔር ቃል ይሞላል!! የእግዚአብሔር ቃል አያረጅም የኢየሱስ ቃል አያረጅም ዘላለም ይኖራል እያበራ ከሚያምኑት ጋራ @FullPentecostalChurch @FullPentecostalChurch
Hammasini ko'rsatish...
2
Repost from PENTECOSTAL TUBE
አንብበው ለወዳጅዎ ያካፍሉ ❤️🦋            የሰውን ውለታ አንርሳ!             አመስጋኞች እንሁን! በአገልግሎት ዘመኔ ከተለያዩ ሀገር ዜጎች ጋር የመገናኘት እድሉ ገጥሞኛል። ለምሳሌ ኮርያኖች፣አሜሪካውያን፣እንግሊዞች፣ሱዳናዊያን፣ኤርትራውያን፣ናይጄሪያዊያን በጥቂቱ ይገኙበታል። ታዲያ ከነሱ ምን ተማርክ ካላቹኝ THANK YOU ማለትን ወይም አመስጋኝነት ወይም ውለታ አለመርሳትን ነው። ለምሳሌ  ኢትዮጵያ በንጉሱ ዘመን ወታደሮችን ወደ ኮርያ በማዝመት ኮርያን ረድታ ነበር። ይህ የሆነው ከአምሳ አመታት በፊት ነበር። ነገር ግን ኮርያኖች አሁንም ድረስ ኢትዮጵያ ያረገችውን ውለታ አልረሱም። ለዚህ ውለታ ሲሉ ዛሬም ድረስ ሚሸነሪ ሆነው፣ የነፃ ህክምና አገልግሎት በመስጠት በበጎ አድራጎት ወዘተ በሀገራችን ይሰራሉ። ነጮች ከሀበሻ ማህበረሰብ በላይ ጥቂት አድርገህ ብዙ ያመሰግኑሀል። ይህ ድንቅ ባህል ነው። ስለዚህ እኛም ሰዎች በአንድ ወቅት ስላደረጉልን መልካም ነገር ሁሉ ልናመሰግን ይገባል። ምንም እንኳ ሰዎች ዛሬ ላይ ቢሳሳቱ፣ትናንት የነበራቸውን መልካም ስራቸውን ቢተው፣ አቋማቸውን ቢቀይሩም፣ አመስጋኝ መሆን ግን የኛ ፈንታ ነው። መቼም የሰውን ውለታ አንርሳ። ደህንነት ያሰተማሩንን ወንጌላውያን፣ ያሳደጉንን መጋቢዎች፣የተባረክንባቸውን የእግዚአብሔርን ሰዎች፣ ለቁም ነገር ያበቁንን ቤተሰቦቻችንን፣ ሲፀልዩልን የነበሩ ሰዎችን፣  አብረውን ረጅም የተጓዙ ጓደኞቻችንን፣ በመከራ ቀን ያበረቱንን ሰዎች፣ ወደፊት እንድንሄድ መሰላል የሆኑን ሰዎች፣የቀለም አስተማሪዎችን ወዘተ ሁሉ ልናመሰግን ይገባል እንጂ ልናዋርዳቸው ፣ ጣታችንን ልንቀስርባቸው ፣አይገባም። አመስጋኝነት የክርስትና አንዱ ምልክት ነውና። ሰዎች ያደረጉልንን ልንረሳ አይገባም። 📣 ከዚህ ቀደም አንድ ምሳሌ ሰማሁ:- በአንድ ሀገር ውስጥ አንድ ንጉስ ነበር። ይህ ንጉስ አስር የዱር ውሾች ነበሩት። ስህተት የሠሩትን አገልጋዮቹን በውሾች ያስነክስና ያሰቃይ ነበር። ከእለታት አንድ ቀን ከአገልጋዮቹ አንዱ የተሳሳተ አስተያየት ለንጉሱ ሰጠ። , እናም ንጉሱ የዚህን አገልጋይ አስተያየት አልወደደውም ነበር። ንጉሱም. አገልጋዩን ወደ ውሾች መኖርያ እንዲወረወር ​​አዘዘ። አገልጋዩም፣  “ንጉስ ሆይ ለአሥር ዓመታት አገልግዬሃለሁ፣ እና ይህን ታደርግብኛለህ? እባክህ ወደ እነዚያ ውሾች ከመወርወርህ በፊት አስር ቀን ስጠኝ!” አለ። ንጉሱም በሀሳቡ ተስማሙ። በእነዚያ አስር ቀናት ውስጥ አገልጋዩ ወደ ውሾቹ ጠባቂ ሄዶ ለሚቀጥሉት አስር ቀናት ውሾቹን ሊያገለግል እንደሚፈልግ ነገረው። ጠባቂው ግራ ገባው ነገር ግን ተስማማ። ከዛ አገልጋዩ ውሾቹን መመገብ፣ ማጽዳት፣ ማጠብ እና ሁሉንም አይነት እንክብካቤ ማድረግ ጀመረ። አሥሩ ቀንም ካለፈ በኋላ ንጉሡ አገልጋዩን ለቅጣቱ ወደ ውሾች እንዲወረወር አዘዘ። እሱ በተጣለ ጊዜ ነጣቂ ውሾች የአገልጋዩን እግር  መላስ ጀመሩ። ንጉሱም በሚያየው ነገር ግራ ተጋብተው። "ውሾቼ ምን ነካቸው?" አለ። አገልጋዩም "ውሾቹን ያገለገልኳቸው ለአሥር ቀናት ብቻ ነው, እና አገልግሎቴን አልረሱም። እኔ ግን አሥር ዓመት ሙሉ አገልግዬሃለሁ ነገር ግን ሁሉንም ረሳህ። አለ። , ንጉሱም ስህተቱን አውቆ ሎሌውን እንዲፈታ አዘዘ። አመስጋኞች እንሁን! የሰውን ውለታ አንርሳ! ✍ነቢይ መሳይ አለማየሁ ለወዳጆቻችሁ ሼር @FullPentecostalChurch @FullPentecostalChurch @FullPentecostalChurch
Hammasini ko'rsatish...
🥰 3
Photo unavailableShow in Telegram
ኦሪት ዘዳግም 31 8፤ በፊትህም የሚሄድ እርሱ እግዚአብሔር ነው፤ ከአንተ ጋር ይሆናል፥ አይጥልህም፥ አይተውህም፤ አትፍራ፥ አትደንግጥ፡ አለው።
Hammasini ko'rsatish...
3🔥 1
Hammasini ko'rsatish...
Lamesginih-Zema-for-Christ-New-DVD.m4a10.92 MB
WHAT IS LOVE? - DR MYLES MUNROE Love is not enough for a successful marriage. Love can be deceiving and may not be a reliable qualification for marriage. Love may bring happiness, but it does not necessarily provide the tools and skills needed to make a marriage work. A successful marriage requires knowledge and understanding about how to live and commit to your partner. Understanding how to navigate the challenges of a committed relationship is a crucial element for a lasting and fulfilling partnership. Love can make us believe that we can overcome any obstacles in a relationship. However, the reality is that many divorced individuals were once deeply in love with their partners. This challenges the notion that love is what keeps a marriage together. Love alone does not guarantee success in marriage. While love brings happiness, it lacks the necessary ingredients to sustain a marriage. Knowledge is what truly makes a marriage work. Many people enter into marriage solely based on their feelings of love, without considering the practical aspects and challenges of living with someone. Our culture places a strong emphasis on emotions, leading us to make impulsive commitments without considering the practical aspects of a long-term commitment. To protect and sustain a marriage, individuals need to acquire knowledge about how to navigate the complexities of a long-term commitment. This knowledge may include understanding effective communication, conflict resolution, compromise, and the ability to adapt to change. By possessing this knowledge, individuals can better equip themselves to build and maintain a successful marriage. In conclusion, love is not the sole determinant of a successful marriage. Instead, knowledge about how to navigate the complexities of a committed relationship is crucial for a lasting and fulfilling partnership.
Hammasini ko'rsatish...
1
የአዲስ ኪዳን ሊቀ ካህናችን የኢየሱስ ክርስቶስ እና የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት አገልግሎት በንጽጽር። 1. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት እንሰሳን ሲሠው ቆይተዋል፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ክርስቶስ ግን የሠዋው ራሱን ነው (ዕብ 9፥12፣ 10፥8-10፣ ዘሌ 16፥15)። 2. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ስለ ኃጢአት የሚያቀርቡት መሥዋዕት ጊዜያዊ ማስተሰረያ ነው፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ያቀረበው መሥዋዕት ዘላለማዊ ማስተሰረያ ነው (ዕብ 10፥ 12፣ ዘሌ 5፥4-6)። 3. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት አንዱ ሲሞት ሌላው ሲተካ ብዙዎች ናቸው ካህናት የሆኑት፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ግን አንድና አንድ ብቻ ነውና የማይለወጥ ክህነት አለው (ዕብ 7፥23-24)። 4. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ያገለገሉት ከሙሴ ጊዜ ጀምሮ በመገናኛው ድንኳንና ከሰለሞን ጊዜ በኋላ ደግሞ በቤተ መቅደስ ነው። የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ክርስቶስ ግን በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለችው፣ የምትሻለውና የምትበልጠው የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው (ዕብ 8፥2፣ 9፥11-12)። 5. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት የሚያቀርቡት የእንሰሳ መሥዋዕት አገልግሎት ማጠናቀቂያ ስላልነበረው ሊቀ ካህናቱ ተግባራቸውን ፈጽመው ሊቀመጡ አልቻሉም፤ ነገር ግን የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ የመሥዋዕትነት አገልግሎት ለአንድ ጊዜ ስለተጠናቀቀ እና ተጨማሪ መሥዋዕት ስለማያስፈልግ በአብ ቀኝ ተቀምጧል (ዕብ 1፥3፣ ዕብ 9፥6-7፣ 10፥11-14)። 6. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት በሕግ መሠረት ሲያገለግሉ ቆይተዋል፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን በሚሻል ተስፋ ቃል በተመሠረተ ኪዳን አገልግሏል (ዕብ 8፥3-4)። 7. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ካህናት የሆኑት ያለ መሐላ ነው፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ክርስቶስ ኢየሱስ ግን እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት ዘላለማዊ ክህነት በእግዚአብሔር ተምሎለታል (ዕብ 7፥29-21፣ መዝ 110፥4)። 8. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ስለ ድካማቸው አስቀድመው ለራሳቸውና ለቤተ ሰባቸው መሥዋዕት ያቀርባሉ፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን አየሱስ ክርስቶስ ግን ፍጹምና ጻድቅ ስለሆነ ለራሱ ማቅረብ አላስፈለገውም ( ዕብ7፥27፣ 9፥6-16፣ ዘሌ 16፥11-19)። 9. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ሰዎች እንዲሁም ኃጢአተኛ ሰዎች ናቸው፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ግን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ነው ( ዕብ 1፥1-3፣ 1ጢሞ 2፥5-6)። 10. የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት መሥዋዕቱን የሚያቀርቡበት መሠዊያ ማለትም በሰው የተተከለው የማደሪያው ድንኳን ራሱ ደም መርጨትና መቀደስ ያስፈልገው ነበር፤ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያገለግልባት ግን በሰው እጅ ሳይሆን በራሱ በጌታ የተተከለች ስለሆነች ፍጹም ናት (ዕብ 8፥2፣ ዘሌ 8፥10-11)። 11. የብሉይ ኪዳን ሊቃነ ካህናት የሚያቀርቡት መሥዋዕት ሰዎችን ከኀጢአትና ከሞተ ሥራ ሕሊና ሊያነጻቸው አልቻለም፤ ነገር ግን የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ጊዜ ደሙን በማቅረቡ በክርስቶስ ኢየሱስ ለሚያምኑት ከሞተ ሥራ ሕሊና ነጻ መሆንና መቀደስ ሆኖላቸዋል (ዕብ 10፥3-4፣ 10-11)።
Hammasini ko'rsatish...
2🔥 2
00:57
Video unavailableShow in Telegram
21.50 MB
አብ በመንፈስና በእውነት የሚያመልኩትን ይሻልና!
Hammasini ko'rsatish...
01:07
Video unavailableShow in Telegram
📣ቀኑ እየደረሰ ነው! ተመዝግበዋል? 📣 🔸የፊታችን  ሚያዚያ 23፣24 እና 25 🔸ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ 🔸በአ.አ ምስራቅ መሰረተ ክርስቶስ  ቤ/ክ  ልባችንን በተስፋ ኃይል ልናቀጣጥል እና ከመለኮታዊው ቃል ጋር ያለንን ግንኙነት ለማጠናክር ታላቅ ትምህርታዊ ድግስ ተሰናድቷል። በእግዚአብሄር ቃል ብርሀን ነጋችንን ለማየትና ለማቀድ ወደምንታጠቅበት ወደዚህ ታላቅ ጉባኤ ሁላችሁም ተጋብዛችኃል። ይደውሉ ይመዝገቡ 0912296536/ 0116670057/ 0983115932 #elpis #elpisforafrica #tothenations #africa #gospel #christian #news #hope
Hammasini ko'rsatish...
21.43 MB
01:05
Video unavailableShow in Telegram
73.72 MB
2
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.