cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

كنز من كنوز الجنة

★ የቱን ይመርጣሉ!!!★ ✔ ቻናላችን በውስጡ ከሚሰጣቸው ትምህርቶች መካከል ፦ ✔ ቁርኣን በተለያዩ ቃሪዎች ፣ ✔ እውነተኛ ቂሷዎች / ታሪኾች ፣ ✔ አጠር አጠር ያሉ ዳዕዋዎች ፣ ✔ ት/ት አዘል ቀልዶች ፣ ✔ ኢስላማዊ ጥያቄ እና መልሶች ። ✔ ዓላማዬ የአሏህን ቃል የበላይ ማድረግ ነው! ለአስተያየቶ፦ @Ami_new_bot

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
474
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
Name-Miqbas From-jima Code 12 የኔ ልዩ ጓደኞች እኔ ከሁሉም በፊት  እንኳን ለኢደል ፊጥር በሰላም አደረሳችሁ ለማለት መጀመሪያ መሆን እፈልጋለሁ  🥰🥰 #EID_MUBAREK እንዳሸንፍ Like አድርጉኝ 🙏🙏 Like ለማድረግ @nas_with_Palestine photo ለመላክ @nas_ali_af
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
Name-Miqbas From-jima Code 12 የኔ ልዩ ጓደኞች እኔ ከሁሉም በፊት  እንኳን ለኢደል ፊጥር በሰላም አደረሳችሁ ለማለት መጀመሪያ መሆን እፈልጋለሁ  🥰🥰 #EID_MUBAREK እንዳሸንፍ Like አድርጉኝ 🙏🙏 Like ለማድረግ @nas_with_Palestine photo ለመላክ @nas_ali_af
Hammasini ko'rsatish...
المتنقبة! هي الملكة.... في كل وقت، ومكان وزمان መተነቁብ ሴት! በማንኛው ጊዜ በየትኛውም ቦታና በማንኛውም ዘመን። ንግስቲቷ እሷ ብቻ ናት!
Hammasini ko'rsatish...
ስለ ወሎ — ከሚሴ አንድ ልበል‼ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ✍(የከሚሴ ህዝብ በእምነቱና በወሎዬነቱ የማይደራደር፤ በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል በአብሮነት እሴት እንዲሁም ለሃገሩ ባለው ፍቅር የማይታማ፣ እንግዳ አክባሪና ጀግና ህዝብ ነው።) || ብዙዎች የወሎዋ ፈርጥ—የወሎዬወች መድመቂያ ይሏታል! ከሚሴ ከተማ በሰሜናዊው ምስራቅ ኢትዮጵያ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የታቀፈች የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር ስር የምትገኝ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር ዋና ከተማ ስትሆን ከመዲናችን —አዲስ አበባ በ 325Km ርቀት ላይ ያረፈች፤ ከወሎዋ ደሴ ከተማ ደግማ በ 74Km ርቀት ላይ የምትገኝ እንዲሁም ከባህር ጠለል በላይ 1424m ከፍታ ላይ ያረፈች፤ "ከወንዝም ወሎ ቦርከና ይፈሳል ሞልቶ ቁንጅና" የተባለለትን የቦርከናን ወንዝ እንደ መቀነት የታጠቀች፣ በተፈጥሯዊ መልከዓ-ምድር ገፅታዋ የተስተካከለች በሰሜናዊው ምሥራቅ ኢትዮጵያ በቀድሞው የወሎ ክፍለ-ሀገር ውስጥ የምትገኝ ከተማ ናት። * በእርግጥ "ከሚሴ" የሚለው ስም የመጣው ከዓረብኛ ቃል እንደሆነ ይታመናል፤ "ኻሚስ" ማለትም "አምስት የሳምንቱ አምስተኛ ቀን ወይም "ሐሙስ" ማለት ሲሆን ትንሽ የመንደሩ ሰዎችና እዛውንቶች ሐሙስ ቀን ይሰባሰቡበት ከነበረው ዛፍ ስር ገበያ እንደጀመሩ ታሪካናት ያስረዳሉ። ሐሙስ ቀን ገበያው የተደረገበት የሳምንቱ ቀን ነው። : ይህም ማለት የከተማው ትልቅ ገበያ ሐሙስ ቀን ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በኦሮምኛም ሆነ በዓረብኛ "ሀሙስ—ኸሚስ" ስለሚባል ከዚህ በመነሳት 1935 E.C "ከሚሴ" የሚለውን ስያሜ እንዳገኘች ይነገርላታል። * ከሚሴ የተቆረቆረችው የኢጣሊያ መንግስት ሁለተኛውን ወረራ ከኤርትራ በመነሳት ድንገተኛ ወረራዉን ከጀመረ በኋላም ነበር። በ2ኛው የጣሊያን ወረራ ወቅት መስራቾቿ ከአዲስ አበባ በወሎ አስመራ በመዘርጋት ላይ በነበረው የጥቁር—አስፓልት መንገድ ስራ ላይ ተሳታፊ የነበሩት ሁለት ሱዳናዊ ወንድማማቾች እንደሆኑ የእድሜ ባለቤቶች ይናገራሉ፤ ይሁን እንጅ በከብት ጥበቃ ስራ ላይ ያሉ ሰዎች እና ደረሳዎች ማረፊያ ሰርተው የሚያርፉበት አከባቢ እንደነበረም ይነገራል። : በአሁን ሰአት ላይ ከሚሴ በልማት ጎዳና፣ በኢኮኖሚ ፍሠት፣ በኢንቨስትመንት መዳረሻነት ራሷን በማነቃቃት ላይ የምትገኝ እንደ ብርሀን ጮራ እየፈነጠቀች፣ እንደ አበባ እየፈካች ያለች ከተማ ናት! * የከሚሴ ህዝብ በእምነቱና በወሎዬነቱ የማይደራደር፤ በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል በአብሮነት እሴት እንዲሁም ለሃገሩ ባለው ፍቅር የማይታማ፣ እንግዳ አክባሪና ጀግና ህዝብ ነው። : ለዚያም ነው ከሚሴን ብዙዎች እንዲህ በማለት የሚገልፆት:- የቆንጆወቹ መፍለቂያ፣ የውቦቹ መንደር፣ የዑለሞች ሀገር፣ የጀግኖቹ መብቀያ፣ የፍቅር ማምረቻ፣ የኢትዮጵያዊን ተምሳሌት፤ በመቻቻል፣ በፍቅር፣ በመከባበር ላይ የተመሰረተች ከተማ ነች። * ✔️ በጥቅሉ የወሎ ህዝብ ማለት ስምህን ሳያቆላምጥ ለመጥራት የሚከብደው፣ የዋህ፣ ከሰው ጋር በቀላሉ ተግባቢ፣ እንግዳ አክባሪ፤ ለሀገሩ ጥልቅ ፍቅር ያለው ህዝብ ነው። Photo Credit: 📷Ashu Habesha * ነሐሴ 13, 2014 E.C August 19, 2022 G.C || Anu
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰሞኑን ሳይንቲስቶች በ2050 ዘላለም ለመኖር የሚያስችለንን ጥናት እያደረግን ነው ብለዋል። ይህ ጉዳይ አደም ገና በጀነት እያለ ሞክሮት የተባረረበት ነው። አላህ አደምን እንደፈጠረው ሟች መሆኑን ነግሮት ነበረ። ከዚያም ለመፈተኛ አንዲት ዛፍ ተከለና ከዚች እንዳትበላ አለው። አደምና ሀረዋ የጀነት ኑሮ ስለጣማቸው ዘላለም መኖርን ፈለጉ። ሸይጧንም ይህቺን አጋጣሚ በመጠቀም ወደ እነሱ መጥቶ፦ «ጌታችሁም መልአኮች እንዳትሆኑ ወይም ከዘላለም ነዋሪዎች እንዳትሆኑ እንጂ ከዚች ዛፍ እንዳትበሉ አልከለከላችሁም አላቸው።» (አዕራፍ 20) እነሱም ዘላለም መኖርን በጣም ተመኝተው ነበርና ከዛፊቱ በሉ። ነገርግን የሸይጧን ቃል ውሸት ሆነና መሸፈኛቸው ከላያቸው ላይ ተገፍፎ ራቁታቸው ቀሩ። አላህም በሰሩት ጥፋት ምክንያት ወደ ምድር ጣላቸው። አሁን ከብዙ ዘመናት በኋላ ሳይንቲስቶች እንደገና ዘላለም ለመኖር እየሰራን ነው ይላሉ። በእርግጥ ዘላለም መኖርን መመኘት ተፈጥሯዊ ነው። ነገርግን የአላህ ቀደር ቀድሞ ተፅፏልና የሚቻል አይደለም። አላህ እንዲህ ብሏልና፦ «ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት። ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሳዔ ቀን ብቻ ነው። ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ። ቅርቢቱም ህይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ አይደለችም።» (አል-ኢምራን 185) ========== ربنا لا تأخذنا بما فعل السفهاء منا... ========= t.me/silatullah_4u
Hammasini ko'rsatish...
01:32
Video unavailableShow in Telegram
00:59
Video unavailableShow in Telegram
#ፂማችሁን በተለያየ ቅርፅ ለመትቆረጡ ሰዎች ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን የሰጡት ምላሽ።
Hammasini ko'rsatish...
ማፍቀርም መፈቀርም ከአላህ ነው ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ውድ ባለቤታቸውን እናታችን ኸዲጃን ረዲየላሁ አንሃ አስመልክተው እዲህ ብለዋል ፍቅሯን ከአላህ ነው የተሰጠሁት ። ስለዚህ ፍቅር እሪዝቅ ነው ና ከረዛቂው እንጠይቅ ። 🤲የአላህ በሁሉም ባለትዳሮች በመሀላቸው ፍቅርን ሪዝቅን አዝንብላቸው። ያላጋባም ሳልህ ሚስት ሳልህ ባል ይወፍቀው።። ልጅም ያጣ ልጅ ይስጠው። ጤና ያጣ ጤናውን ሚያገኝበት የተቸገረ ከችግሩ ሚላቀቅበት ቀን አድርግለት አሪፍ ጁምዓ ለሁላችን ይሁን ። አላሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዱና ወመውላና ወሸፊዑና ሙሐመድ( ሰ ዐ ወ) ሰሉ አለ ነቢ።
Hammasini ko'rsatish...
የግቢ ህይወት! ======= እህት ወንድሞቼ ዛሬ ስለ ግቢ ህይወት አንድ ነገር እላችኋለሁ። የግቢ ህይወት ለሴት ልጅ መቼም ቢሆን አልመክርም። ሴት ልጅ በኢስላም ነው የተከበረቺው፣ ኢስላም ለሴት ልጅ መብት መከበርና መጠበቅ የሚቆም ብቸኛው ዲን ነው። ሴት ልጅ ዲኗ ካዘዛት ውጭ የሆኑ ስራዎችን ወይም ዲኗ የከለከላት የሆኑ ስራዎችን ከሰራች ኢስላም ያለበሳት የምን ግዜውም የልእልና ካባ ታወልቀዋለች። ሴት ልጅ ደካማ ናት። ብቻዋን ነገራቶችን ለመቋቋም ይከብዳታል ከጎኗ የሚያበረታታት ወንድም ትፈልጋለች። በካምፓስ ውስጥ ደሞ ከቤተሰብ ርቃና ተነጥላ ነው ምትሄደው ከማንም በላይ freedom ይሰማታል የሚቆጣጠራት ቤተሰብ ስሌለለ ያሻትን ሁሉ ትሰራለች። አስሩ ወንድ ጋር ትገናኛለች፣ ወንዱ ምግብ ይጋብዛታል ድብርቷን ያነሳላታል...ማታ ማታ ደሞ ከ library እስከ dorm ድረስ ሸኘኝ ብላው ተያይዘው ይጓዛሉ...ይሄ ሁሉ የሚሆነው በሀራም ነው። ሙስሊም ሴት እንዴት ካፊር ወንድ ጋር ትላላጣለች? ያውም ሂጃቧን ኢስላም ያለበሳትን የልቅና ካባ ለምንስ ታወልቃለች? ስለሷ መብት ሲሟገት እንዳልነበር, ሴት ልጅ ከነ ህይወቷ አትቀበርም ስላለ፣ ሴት ልጅ በሀይድ ጊዜ ጂማእ አትደረገም(የነሳሮች አካሄድ) ወይ እንደ የሁዶች ለብቻዋ አንድ class ውስጥ አትደነቅርም። እሷም የአላህ ፍጥረት ናት። እናት ስትሆን ጀነት በግሯ ስር ትሆናለች።... ብሎ ኢስላም ስላከበራትና ስላላቃት የሷ ውለታ ይሄ ይሆናል በአላህ። ዲኗን የምትይዘው ደሞ በስንቱ ወንድ ትፈተናለች ያም እየሄደ ይተነኩሳታል ሰሏማን ያሳጣታል፣ እየደወለ ይረብሻታል፣ ከዴኗ ሊያሰናክላት ይሞክራል፣ መንሀጇን ሊያስረሳት ይፈልጋል...። ታዲያ ይሄ ሁሉ ፈተና ያለበት ቦታ ላይ ለምንስ ትመጣለች? በትምህርቴ ላይ ህልም አለኝ ትዪ ይሆናል! .... ግን እንኳን አንድ ህልም አይደለም ለምን ሺ ህልም አይኖርሽም ከዲንሽ ካራቀሽ ካለሽበት የመንሀጅ አቋም ካንሸራተተሽ በወንዶች ፈተና ከወደቅሽ፣ ከማንም አጅነብይ ወንድ ጋር ከተላላጥሽ፣ ዲንሽ ከከለከለሽ ቦታ ከተገኘሽና ካዘዘሽ ቦታ ካልተገኘሽ..ወላሂ ሱመ ወላሂ የትምህርት ህልምሽም ይሁን ትምሀርትሽ ላንቺ አጥፊዎችሽ ናቸው። ለዱንያ ህልም ተብሎ የነገው ቤትሽን የምታበላሺበት ምንም አይነት ምክንያት የለሽም። ከነገው ቤትሽ የሚያዘናጉሽ ነገራት በሙሉ ባንቺ ላይ አጥፊዎች ናቸው። ➱እህት ወንድሞቼ እያወቃችሁ እህቶቻችሁን ዘመናዊ ፊትና ውስጥ አትዱሉ ለነሱ ህይወት መበላሸት፣ ለነሱ ከዲን እውቀት መራቅ፣ ከነሱ ከመንሀጃቸው መንሸራተት..ምክንያት አትሁኑ። ሴት ልጅ የምትከበረው በአባቷ ቤት ነውና እዛው ክብሯን ጠብቃ እንድትኖር አድርጉ። ======== ✍miqbas hadi ======== t.me/silatullah_4u
Hammasini ko'rsatish...