GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.
Kanalga Telegram’da o‘tish
1 421
Obunachilar
+124 soatlar
+87 kunlar
-630 kunlar
Postlar arxiv
ቀን፡ 22/06/2017ዓ.ም
ትምህርት ቤታችን በ2017 ዓ.ም በአንደኛ መንፈቅ ዓመት በተከናወኑ ተግባራቶች ላይ ከወላጆች ጋር ከታች በተዘረዘሩት ነጥቦች ላይ ተወያይቷል።
👉 በመማር ማስተማር ዙሪያ
👉 በፋይናንስ አጣቃቀም
👉 ስለ ቀጣዩ ትምህርት ዘመን እና
👉መረጃ የሚተላለፍበት መንገድ
በመርሃ-ግብሩ ላይ የት/ቤታችን ባለቤት የሆኑት አቶ አለማየሁ መርጋ እንደተናገሩት የትምህርት ስራ የሁላችንንም የጋራ ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅና በጋራ የሚሰራ ለጋራ ውጤት የምንታትርበት ነው፤ለዚህም ወላጆች ያላችው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ትምህርት ቤቱ የትምህርት አሰጣጥን መሰረታዊ የሚባሉ ደረጃዎች ማሟላታቸውን፣ የምንፈልገውን ዜጋ በመቅረጽ ሂደት ውስጥ ወላጆች የልጆቻቸውን ብቃት በየጊዜው የሚፈተሹበት መስፈርት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት የሚገባ ነው ብለዋል፡፡ የትምህርት ቤቱ ወላጅ ኮሚቴዎችም በበኩላቸው እነዚህ ተግባራት ሲከናወኑ ከትምህርት ተቋማትና ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር መወያየቱና መነጋገሩ የትምህርትን ጥራት በተሻለ መንገድ ለማስጠበቅ የሚያስችል ይሆናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም የተማሪዎች ውጤት ትንተና በየክፍሉ የቀረበ ሲሆን ወላጆች የልጆቻቸውን ውጤት ከክፍል ኃላፊ መምህራን ጋር በመወያየት ውጤቱን ወስዷል ፡፡
🙏🙏🙏❤️❤️❤️❤️❤️❤️🙏🙏🙏
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
