GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.
Kanalga Telegram’da o‘tish
1 426
Obunachilar
+124 soatlar
+67 kunlar
-230 kunlar
Postlar arxiv
ጥንቃቄ እናድርግ!!
👉በአዲስ አበባ በከተማ " ጉንፋን መሰል " ህመም መከሰቱና ነዋሪዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው የጤና ባለሙያዎች እየመከሩ ናቸው።
✅ጉንፋን መሰል ህመሙ፦
👉 ከአፍንጫ ብዙ ፈሳሽ መውጣት፣
👉ሳል፣
👉ራስ ምታት፣
👉 ጉሮሮን የማቃጠል ስሜት፣
👉 ድካም፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
✅ህመሙን ለመከላከል እና ለማስታገስ ፦
👉 ፈሳሽ መውሰድ፣
👉ከቅዝቃዜ ራስን ማራቅ (ሙቀቱን የተመጣጠነ ማድረግ)፣
👉 መኖሪያ ቤትን አየር እንዲያገኝ ማድረግ፣
👉 በቂ የሆነ እረፍት መውሰድ እና የመሳሰሉትን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን መክረዋል።
✅በሌላ በኩል ፤ በቤት ውስጥ የእፅዋት ዝርያዎችን በፍም (እሳት) ላይ በማጨስ ጭሱን መታጠን ሳንባ እንዲያብጥ ወይም እንዲቆጣ በማድረግ ለጉዳት እንደሚዳርግ ተናግረዋል፡፡
✅ማህበረሰቡ ፦
👉 በህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥ መስኮቶችን በመክፈት፣
👉በንግድ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ሰው በተሰበሰበበት ቦታዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል በማድረግ፣
👉የእጅን ንፅህና በአግባቡ በመጠበቅ እንዲሁም አስም ያለባቸው ምልክቶቹ እንደታዩባቸው ወደ ህክምና ተቋማት ሄደው መታየት እንዳለባቸው መክረዋል።
👉የዝናብ ወራት ማለፉን ተከትሎ በጥቅምትና ህዳር ወቅት ላይ አብዛኛውን ጊዜ የጉንፋንና ኢንፍሉዌንዛ በሽታ ይከሰታል፡፡
👉" እጅን በመታጠብ፣ አፍና አፍንጫን በመሸፈን በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል " ያሉ ሲሆን በበሽታው የተያዙ ሰዎች በቂ እረፍት በመውሰድ፣ ፈሳሽና ትኩስ ነገሮች በመጠቀምና ተገቢውን ህክምና በማግኘት ስርጭቱ እንዳይስፋፋ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል
via👉 ኢዜአ ነው።
መልካም ቀን👏👏
"ለልጄ በወር 3 ብር ከፍዬ ማስተማር አልችልም እና አንድ ብር አድርጉልኝ"
.
.
ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካ ብሄራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ሽልማትን ከፕሬዚደንት ጆ ባይደን እጅ ዛሬ ተቀብለዋል።
በሳይንስ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ዘርፍ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ የአሜሪካ ዜጎች በሚሰጠው በዚህ ሽልማት ላይ 19 ሰዎች የተካተቱ ሲሆን የፐርዱ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ ፕሮፌሰር ጋቢሳ አንዱ ሆነዋል።
(ስለ ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ባህር ከሆነ ታሪካቸው ቀኝጨብ ላድርግ)
የተወለዱት በምእራብ ሸዋ ከፊንፍኔ 62 ኪ/ሜ ርቀት ላይ በሆለታ እና ጊንጪ መካከል ከምትገኘው ኦሎንኮሚ በ1942 ነው። ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ።
ገና በህጻንነታቸው ወላጆቻቸው በመለያየታቸው ወላጅ እናታቸው ወ/ሮ ሞቲ አያኖ ልጆቻቸውን የማሳደጉን ሀላፊነት ብቻቸውን ተሸክመው ጠላ በመሸጥ ህይወትን ተጋተሩ።
እኩዮቹ ወደ ቄስ ትምህርት ቤት ሲሄዱ አብሬ ካልሄድኩ በማለት ቢያስቸግራቸው ወደ መምህሩ በመሄድ "እኔ ምስኪን ነኝ ለልጄ የትምህርት ቤት የወር ክፍያ የሚሆን ሶስት ብር ማግኘት አልችልምና እባካችሁ አንድ ብር አርጉልኝና ልጄ እንደ እኩዮቹ ተምሮ ይግባ" ብለው መምህሩን ጠየቁ። የእናት ልመና ምን ማለት እንደሆነ የገባቸው መምህር በጠየቁት መሰረት በወር አንድ ብር ከፍለው ልጃቸው እንዲማር ፈቀዱላቸው ። በዚህም መሰረት የዛሬው አለም አቀፋዊ ተመራማሪ ገቢሳ እጀታ ከፊደል ገበታ ጋር ተዋወቀ ። ዛሬ ለእልፍ አለም አቀፍ ሽልማቶች ባለቤት የሆነው ሰው ህይወት ኡደትም አሀዱ ማለት ጀመረች።
እስከ 7ኛ ክፍል የተማሩት እዛው ኦሎንኮሚ ሲሆን ስምንተኛ ክፍል በአካባቢያቸው ስላልነበረ 20 ኪሎሜትር በእግራቸው እየተጓዙ ተከታትለዋል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ የተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በእፅዋት ሳይንስ ከሃረማያ ኮሌጅ በ1965 ዓ.ም ወስደዋል። በ1968 በእፅዋት ሳይንስ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በ1970 በእፅዋት ማዳቀል እና ዘረ መል ምህንድስና አሜሪካ ከሚገኘው ፐርዱ ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት (ሶስተኛ) ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
- ከሁለት መቶ በላይ የጥናት ጽሁፎችን ለህትመት አብቅተዋል፡፡
-አራት መፅሐፎችን የአርትኦት ስራ ሰርተዋል፡፡
-ለ28 አመታት ያህል በአሜሪካ በሚገኘው ፐርዱ ዩኒቨርስቲ ያገለገሉት የአለም ሎሬት ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ ዩኒቨርሲቲው አሉኝ ከሚላቸው ተመራማሪዎችም አንዱ ናቸው።
- ከሰባ በላይ በሚሆኑ ዓለም አቀፍ እና ሀገራዊ ተቋሞች ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ሰርተዋል፡፡
-ለእነዚህ እና መሰል የምርምር ስራዎቻቸው ከ17 በላይ ዓለም አቀፍዊ ፣ አህጉራዊ እና ሀገራዊ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
-በ2009 World Food Nobel Prize የተሸለሙ ሁለተኛው አፍሪካዊ ለመሆን በቅተዋል።
-African Nationality Science Hero Award ከተሸለሙ አፍሪካዊ ሰባት ተመራማሪዎችም አንዱ ለመሆን በቅተዋል።
Repost from Yeka Education
በትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ስርአተ ትምህርት መሰረት የተዘጋጀው አዲሱ የተጓዳኝ ትምህርት ዘርፍ እና የክበባት አደረጃጀት ማንዋል
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
