cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ከእግዚአብሔር ጋር ኑ እንታረቅ

🚩 Channel was restricted by Telegram

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat ko'rsatilmaganTil ko'rsatilmaganKategoriya ko'rsatilmagan
Advertising posts
202Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

፨መንፈሳዊ ዜና፨ ፅርሃሞ ድርሃሞ የተሰኘው አጋንንት በስራው ውጤታማ መሆኑን ፅርሃሞ ድርሃሞ በተሰኘው የfacebook ገጹ ላይ አስታወቀ፡፡ ፅርሃሞ ስለ ስኬቱ ሚስጥር ሲገልፅ የሰውን ልጅ በርባው ባርባው ጊዜያቸውን እንዲፈጅ ካርገ በኃላ የመኝታ ሰዓታቸው ሲደርስ በሰላም ያዋላቸውን አምላክ በፀሎት እንዳያመስግኑ በፍጥንት ወደ አልጋቸው በመውርወር እና እንዲተኙ በማድርግ ነው ብሏል፡፡ በተጨማሪም አለ ፅርሃሞ ማልደው ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይሄዱ ብርድልብሳቸውን እንደ ትልቅ የጭነት መኪና በማከበድ እና ጣፋጭ መሰል እንቅልፍ በመልቀቅ መሆኑን ተናግሩል፡፡ በዚህም ስራው በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ምዕመናንን በእንቅልፍ ማሰሩን አስታውቋል፡፡ ለበለጠ መርጃ WWW.ሳትፀልዩ ተኙ .Com ላይ እንገናኛለን ብሏል፡፡ 👉ታድያ ክርከቲያኖች ሆይ በፀሎት በመትጋት ይህን ክፋ መንፈስ መዋጋት አይሻልምን? ✍️ቃልኪዳን ተፈራ ➴📌➴📌➴📌➴📌➴📌➴ @MENFESAWItsufoche 👆👆👆👆👆👆👆👆
Hammasini ko'rsatish...
AddisAbea
Hammasini ko'rsatish...
+ ጊዮርጊስ ሆይ ከእኛ ወገን ነህን? + ወደ አድዋ ከዘመተው ሕዝብ አብዛኛው ባዶ እግሩን ነበር:: ዳዊት ጎልያድን ሊዋጋ ሲወጣ ከያዛት በትር በቀር አብዛኛው ሰው መሣሪያ አልታጠቀም:: አብዛኛው ዘማች ባዶ እጁን የዘመተው ሁለት ነገር አስቦ ነው:: መሣሪያ ባይኖረውም በውጊያው መካከል ከጠላት ጦር መሣሪያ ነጥቄ እዋጋለሁ አለዚያም ከሚወድቁት ላይ መሣሪያ አንሥቼ እዋጋለሁ ብሎ ነበር:: በውጊያው ታንክ በጎራዴ እስከመማረክ ያደረሳቸውም ይህ ቆራጥነታቸው ነበር:: ለመንፈሳዊ ጥንካሬያቸው ደግሞ ምሥጢሩ አብራ የዘመተችው የቤተ ክርስቲያን ጸሎት እና ንጉሡ በድንግል ማርያም ስም ምለው የሠጡት አደራ ነበር:: ለተገፉ የሚቆመው ሰማዕቱ ጊዮርጊስም በግፍ ባሕር አቁዋርጠው በደሃ ሕዝብ ላይ እሳት ከሚያዘንቡት ከአባቱ ዘመዶች ከሮማዊያን ጋር ሳይሆን እንደ ዳዊት በትር ይዘው በእግዚአብሔር ስም ከወጡት ባለማተቦች ጋር በምልጃው ተሰልፎ ዋለ:: በዚያች ዕለት አንድ ጣሊያናዊ ቅዱስ ጊዮርጊስን አግኝቶ ኢያሱ ቅዱስ ሚካኤልን እንደጠየቀው "ከእኛ ወገን ነህ ወይንስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? " ብሎ ቢጠይቀው ኖሮ "እኔ አሁን ከእግዚአብሔር ተልኬ መጥቻለሁ ይልቅስ የቆምክባት መሬት ኢትዮጵያ የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ" ባለው ነበር:: የዐድዋ ዘማቾች ጾመኞች ነበሩ:: እንግሊዝም ጣሊያንም ሰይጣን ይመስል ኢትዮጵያን የተዋጉአት በዐቢይ ጾም ነበር:: "ወድቀህ ብትሰግድልኝ መንገድና ፎቅ እሰራልሃለሁ" ያለንን ጣሊያን አባቶቻችን "ሒድ አንተ ጣሊያን የራስህን እንጂ የእኔን አታስብምና" ብለው ድል ነሡት:: ዘማቾቹ የምግብ እጥረት ቢኖርም እንኩዋን ጾሙን ትተን ካልበላን አላሉም:: ድንገት መሞቴ አይቀር ብበላ ይሻለኛል ሳይሉ ተዋግተው ድል ተቀዳጁ:: እኛ በሰላም ጊዜ የምንተወውን ጾም እነርሱ በጦርነት ላይም ሆነው አልተዉትም:: በዚያ ድል ሀገሪቱ ለዐርባ ዓመት ከጦርነት ስታርፍ ለዕድሜ ዘመንዋ ደግሞ ከቅኝ ግዛት ዐረፈች:: ቅኝ ግዛት ብንገዛ ኖሮ ደሃ አንሆንም ነበር የሚል ሰው አይጠፋም:: ይህንን አሳብ የብዙ አፍሪካውያን ሀገራት ጆሮ አይስማው:: ዛሬ ነጻ ከወጡም በኁዋላ በባርነት ሕሊና የሚሰቃዩ ብዙ ናቸው:: ብዙ በፈረንሳይ የተገዙ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ዛሬም ድረስ በአደራ አስተዳደር በፈረንሳይ በእጅ አዙር ይተዳደራሉ:: በተባበሩት መንግሥታት ሳይቀር ቅኝ ገዢዎቻቸውን ተወካይ ሁነኝ ብለው የሚልኩ ሀገራት አሉ:: ዛሬም ድረስ በአንዳንድ አፍሪካ ሀገራት ጥቁሮች ሊስተናገዱ በተሰለፉበት ሱፐር ማርኬት አንድ ነጭ ከመጣ ሰልፍ ሳይይዝ ቅድሚያ ይስተናገዳል:: (በዓይኔ ያየሁት ነው) ዛሬም ድረስ ብዙ አፍሪካዊያን ጥቁር በአስተሳሰብ ከነጭ በታች ነው ብለው ያምናሉ:: በዜኖ ፎቢያ የገዛ ወንድሞቻቸው አፍሪካውያንን የሚያሰቃዩ ደቡብ አፍሪካውያን ነጭ ሰፈር ግን ዝር አይሉም:: ሂሳብ ስታሰላ ሲያዩህ እንኩዋን አንተ ጥቁር ሆነህ እንዴት ያለ ካልኩሌተር መደመር ቻልክ የሚሉ ሰዎች ተፈጥረዋል:: በአውሮፓ በአሜሪካ ተወልደው አድገው ስኬታማ የሆኑት ጥቁሮች እንኩዋን የቤተሰብ ስማቸው ላይ አያቶቻቸውን በባርነት የገዛው ነጭ ገዥ ስም አብሮ ስለሚለጠፍ የዕድሜ ልክ የበታችነት ይሰማቸዋል:: አባቶቻችን ከብዙ ጣጣ አድነውናል አሁን ራሳችን የምንፈጥረውን ችግር ቢያዩ ለማመን የሚቸገሩ የሚሆኑትም ዘር ሳይለዩ አብረው የተዋደቁት ጀግኖች ናቸው:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬም ቤሩታዊት ኢትዮጵያን ከዘረኝነትና ጥላቻ ደራጎን ይታደጋት ዘንድ የምንማጸንበት ጊዜ ነው:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የካቲት 23 2012 ዓ ም ወላይታ ሶዶ ኢትዮጵያ ፎቶዎች :- ሊባኖስ ቤሩታዊትዋን ባዳነበት ሥፍራ እና ልዳ በቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ሥፍራ የተነሣሁት:: እናንተንም መቃብሩን ለመሣለም ያብቃችሁ:: ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :- የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/ የቴሌግራም ቻናል : https://t.me/deaconhenokhaile የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
Hammasini ko'rsatish...
Henok Haile

Henok Haile, Addis Ababa, Ethiopia. 219,623 likes · 32,472 talking about this. Henok Haile ሄኖክ ኃይሌ

መነበብ ያለበት መጽሐፍ በጉጉት ላይ
Hammasini ko'rsatish...
እውነትን ወደ ማወቅ የደረሰው የፕሮቴስታንት መምህር(Patric M.peace) እንዲህ ይላል"የጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናትን ምን እንደሚመስሉ(ሥርዓተ አምልኮ) ለማወቅ በጥልቀት መመራመር እና ማንበብ ጀመርኩኝ ።በተጨማሪም የጥንታዊቷ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት አባቶችን ህይወት መመርመር ጀመርኩኝ። እናም አንድ ነገር ተረዳሁኝ 'ፕሮቴስታንት(Protestant) ቤተክርስቲያን ብሎ የሚጠራው በታሪክ ውስጥ ካየኋቸው አብያተክርስቲያናት ፈፅሞ የተለየ ነው። ልዩነቱም የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን በመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ የተመሰረቱ አይደሉም በተጨማሪም ልቅ የሆነ የሙዚቃ አምልኮን "አምልኮ" ብላ የምታቀርብ ናት። በተጨማሪም የተወሰኑ ቡድኖች የሚመሠርቱትና የሚመሩት ነው።ጥንታዊቷ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ግን ፍፁም መፅሐፍ ቅዱሳዊ የሆነ ሥርዓተ አምልኮ ያላት እና የተወሰኑ ቡድኖች የማይመሯት(በመንፈስ ቅዱስ የምትመራ):የአምልኮ ሥርዓቷ(ቅዳሴ:ዝማሬ:ማህሌት) ወንጌል(መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነው። ይህም ነፍስ እግዚአብሔርን እንድታገኝ የሚያስችል ነው ።ይህንንም የቤተክርስቲያኒቷን ቅዱሳን አባቶች ህይወት በምመረምር ወቅት አረጋግጫለሁ።" ይህንን ፅሁፉን ሲቋጭ ለፕሮቴስታንት ወንድሞች እና እህቶች "እናም ወንድሞቼ "ቤተክርስቲያን ተመልከቱ"።" ይላል። | ቤተክርስቲያንን አየኋት + አወኳት + ወደድኳት| ቅዱስ ያሬድ | https://t.me/joinchat/VCpy-zCPRXuBKnqT ከታየ ነገር የተወሰደ
Hammasini ko'rsatish...
ከእግዚአብሔር ጋር ኑ እንታረቅ

https://t.me/joinchat/VCpy-zCPRXuBKnqT

የማናውቀውን በጋራ እንጠያየቅ ወቅታዊ ትምህርቶችም ይገኙበታል ለአስተያየት @Test56563737Bot

ወጣት መነኩሴ ወደ አባ እንጦንዮስ መጣ። እየተማረረ እንዲህ አለ "አባቴ ሆይ ከመነኮስሁ ዓሥር ዓመታት አለፉኝ። ነገር ግን የዲያቢሎስን ፈተናውን መታገስ አቃተኝ ፣ እጅግ እየታገለኝ ነው" አባ እንጦንስም ለዚህ መነኩሴ የሚገባውን ምክርና ተግሣፅ ሠጥቶ አሰናበተው። መነኩሴው ከወጣ በኋላ ዲያቢሎስ ወደ አባ እንጦንስ ቀርቦ እንዲህ አለ። "በሕያው እግዚአብሔር እምላለሁ ፣ ይኼ ሰው መመንኮሱንም አላውቅም" እኛ በዲያቢሎስ ተፈተንሁ ለማለት ራሱ ገና ነን ፣ ምክንያቱም የራሳችንን ድካምና ምኞት ገና ድል አልነሣንም። "ምንም እንደ መቅደሱ መንጻት ባይነጻ የአባቶቹን አምላክ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ልቡን የሚያቀናውን ሁሉ ቸሩ እግዚአብሔር ይቅር ይበለው" (2 ዜና 30: 19)
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም ወደዚህ የመወያያ ቡድን(Group) ስለተቀላቀሉ እናመሰግናለን። ✅ ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሰረት #ተሸላሚ ይሁኑ 100ሰዎችAddበማድረግ=10ብር ካርድ 👉 150ሰዎችAddበማድረግ=15 ብር ካርድ 👉 200ሰዎችAddበማድረግ=25ብር ካርድ ይሸለሙ https://t.me/joinchat/VCpy-zCPRXuBKnqT ♻️ሰዎችን ካስገቡ በኋላ "በቅድስና በመኖር እግዚአብሔርን አስደስታለሁ"ብለው ይፃፉ። በመጨረሻም ይህን ያክል ሰው Add አድርጌያለሁ ብላው ለ @Test56563737Bot መልዕክት ይላኩ! መልካም ጊዜ ይሁንልዎ! text Here 🗓 Today : Thursday 10 February 2022 ⏰ Hour : 18:48 This message will be deleted after 3 minutes
Hammasini ko'rsatish...
ከእግዚአብሔር ጋር ኑ እንታረቅ

https://t.me/joinchat/VCpy-zCPRXuBKnqT

የማናውቀውን በጋራ እንጠያየቅ ወቅታዊ ትምህርቶችም ይገኙበታል ለአስተያየት @Test56563737Bot