cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Abune Gorgorios

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
5 215
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+177 kunlar
+7830 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Hammasini ko'rsatish...
ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ? የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ነገ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ። በዌብ ሳይት 👉 https://eaes.edu.et/ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት 👉 6284
Hammasini ko'rsatish...
ከ810ሺህ በላይ ተማሪዎች ወድቀዋል! በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ ገደማ ተማሪዎች መካከል፤ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ የማለፊያ ነጥብ ያመጡት ተፈታኞች ብዛት 27,267 ተማሪዎች አሊያም 3.2 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 16,451 የማታ ተማሪዎች መካከል፤ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡት 12ቱ ብቻ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል። እነዚህን አሃዞች ዛሬ ሰኞ መስከረም 28፤ 2016 በሰጡት መግለጫ ይፋ ያደረጉት፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ባለፈው ዓመት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር “በጣም ከፍተኛ የሚባል መሰረታዊ ለውጥ የለም” ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል፤ 1,328ቱ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል። አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ማሳለፋቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 94.5 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ማሳለፋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል ! የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ  ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ይሆናል በቻናላችን ምትገኙ  ውጤቱን በመጠበቅ ላይ ምትገኙ መልካሙን ሁሉ እመኝላችኋለሆ!❤️
Hammasini ko'rsatish...
01:04
Video unavailableShow in Telegram
ለልጆቻችሁ ማስተማር ያለባችሁን ለማግኘት Follow me https://vm.tiktok.com/ZMjmcNy23/
Hammasini ko'rsatish...
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን።                                        መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም “አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ፥ በአንዳች ነገር ማሰናከያ እንዳንሰጥ እንጠንቀቅ።” (፪ ቆሮ.፮፥፯።)                                                 በመምህር ፈቃዱ ሣህሌ       ልዑል እግዚአብሔር እንኳን ለወርኃ ጽጌ አደረሳችሁ!!! እንደሚታወቀው ወርኃ ጽጌ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ እንዲሁም ከአረጋዊው ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ተሰዳ በምድረ ግብጽና በኢትዮጵያ ለተንከራተተችበትና የተለያዩ መከራዎችን ለተቀበለችባቸው ዘመናት መታሰቢያ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም በየዓመቱ ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ባሉት ፵ ቀናት ውስጥ በተለይም ሰንበተ ክርስቲያንን እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በማክበር ታሳልፋለች። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ይህ ወቅት ከሚከበርባቸው ልዩ ልዩ መንገዶች መካከልም የሚከተሉት ይገኙባቸዋል። ሀ. በማሕሌት አባቶቻችን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፥ ካህናተ እግዚአብሔር አምመውና ጠምጥመው፥ ጥንግ ድርብና ካባ ለብሰው በየአድባራቱና ገዳማቱ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ለስብሐተ እግዚአብሔር ይሰየማሉ። ከማታ ጀምረው ሌሊቱን በሙሉ ማሕሌተ ጽጌን ቆመው ሥርዓተ ማሕሌቱን ሲያደርሱ በማደር፣ በቅዳሴና በጉባኤ ወርኃ ጽጌን ያከብራሉ። የተቻላቸውና የበረቱ ምእመናንም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመገኘት በእልልታና በጭብጨባ እያመሰገኑ በማደር ቅዳሴውን በማስቀደስ፣ ሥጋውንና ደሙን በመቀበል፣ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማትና በመዘመር የበረከቱ ተሳታፊ በመሆን ያከብሩታል። ለ. በዝክር ምእመናንና ምእመናት በአብዛኛው በየንስሐ አባቶቻቸው እየታዘዙ፥ አንዳንዶችም በግል ፈቃዳቸው (ፍላጎታቸው)፥ ከንስሐ አባታቸው ጋር ተማክረው የቻሉ ፍሪዳውን አርደው፣ አወራርደውና አጣፍጠው፥ ጠጁን ጥለውና ጠላውን ጠምቀው በማቅረብ መላ ሌሊቱን ሲያገለግሉ ያደሩ ካህናትን፣ ነዳያንንና እንግዶችን በመመገብ ያከብሩታል። ያልቻሉም ቤት ያፈራውን በፍጹም ደስታና ፈቃደኝነት አቅርበው እየዘከሩ ያከብሩታል። ሐ. በጾም አንዳንዶች ደግሞ (አሁን በርከት እያሉ ነው፤) የጌታችንን፣ የእመቤታችንን፣ የአረጋዊው ዮሴፍንና የሰሎሜን ስደታቸውንና መከራቸውን (መራብ መጠማታቸውን) በሚገርም ሁኔታ እየጾሙ በማሰብ ያከብሩታል። ይህም ጿሚዎቹ ለእመቤታችንና ለጌታችን ያላቸውን ጽንዐ ፍቅር በግልጽ የሚያሳይ ታላቅ ተጋድሎ ነው። ዳሩ ግን በማወቅም ይሁን ባማወቅ በአንዳንዶቹ አጿጿም ላይ የሚታዩ ስሕተቶች ስላሉ እንዲያረሟቸው ለማስቻል እንጠቁማቸዋለን። ስሕተቶቹን በመፈጸም ላይ ያሉ ጿሚዎች ሰይጣን ለማግኘት የሚጓጉትን በረከት እንዳያሳጣቸው ክፍተቶቻቸውን መሙላት፥ ግድፈቶቻቸውንም ማስተካከል ይጠበቅባቸዋል። 1ኛ. “እንጾማለን!” ብለው የወሰኑ ክርስቲያኖች በቅድሚያ ይህ የዐዋጅ ጾም ሳይሆን የፈቃድ ጾም መሆኑን መረዳት ይኖርባቸዋል። 2ኛ. በመቀጠልም የፈቃድ ጾም አጿጿምንም (ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ) ጠንቅቆ መገንዘብ ይጠበቅባቸዋል። እነዚህም፦ •  ይህን ጾም ከመጾም አስቀድሞ ሰባቱን የዐዋጅ አጽዋማት እየጾሙ መሆናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። ወርኃ ጽጌን መጾም ትሩፋት ሲሆን ሰባቱን የዐዋጅ አጽዋማት (የነቢያት፣ የነነዌ፣ ዐቢይ፣ የጋድ/ገሃድ/፣ የሐዋርያት፣ የድኅነት/ረቡዕና ዓርብ/፣ የፍልሰታ አጽዋማትን) መጾም ግን ርትዕ ነውና። (ይህ የፈቃድ እነዚያ ግን የትእዛዝ ናቸውና።) •  መጾማቸውን ከንስሐ አባታቸው በስተቀር ማንም እንዳያውቅባቸው በጣም መጠንቀቅ አለባቸው። ለሰው ካወጁት (ጿሚነታቸውን ከተናገሩ) እንደሚፈርስባቸው (እንዳልጾሙ እንደሚሆኑ) ማወቅ ይኖርባቸዋል። •  በጾማቸው ወቅት በሆነ አጋጣሚ ወዳጆቻቸው አብረው ይበሉ ዘንድ የግድ ቢሏቸው፥ “ጿሚ ነኝ፤” ማለት የለባቸውም። በማያስነቃ መልኩ ማምለጥ ከቻሉ (በምክንያት) መልካም ነው። ካልቻሉ ግን ለዚያ ጊዜ (ቁርስ፣ ምሳ፣ ራት) የቀረበውን ሳይለዩ አብሮ ግጥም አድርጎ መብላትና ከዚያ በኋላ ጾሙን መቀጠል ይገባል። ምክንያቱም ይህ ጾም የሚፈርሰው በዚያ አጋጣሚ አብሮ በመብላት ሳይሆን “እኔ ጿሚ ነኝ፤” እያሉ (ይወቁልኝ ብሎ) ለአላፊ ለአግዳሚው በማወጅ ነውና። •  ይህ ጾም በግል ውሳኔና ፈቃደኝነት የሚጾሙት እንጂ ለካህናትና ለክርስቲያኖች ሁሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የታዘዘ (የዐዋጅ ጾም) ስላልሆነ በማይጾሙ ካህናትና ክርስቲያኖች ላይ ከመፍረድ በእጅጉ መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል። ይህን ካደረጉ (በማይጾመው ከፈረዱ) ጾምን ማፍረስ ብቻ ሳይሆን በማይመለከታቸው በሰው ላይ ፈርደዋልና ፈራጁ እግዚአብሔርን የሚያሳዝነውና ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ውጪ በመሆኑ ታላቅ ኀጢአትም ይሁንባቸዋል። ሆዳቸውን እያስጾሙ አንደበታቸውን የማይቆጣጠሩ (አንደበታቸው የማይጾም) ሰዎች ስለሚሆኑም “ጿሚዎች” ሊባሉ እንደማይችሉ መረዳት ይገባቸዋል። •  ጿሚዎች ይህንን ወርኃ ጽጌ ሲጾሙ የሚበሳጨው ሰይጣን ብቻ ነው። የሰው ልጆች ጠላት የሆነ ይህ ባላጋራ የዐዋጁን ጾም ፈጽመው ዳግመኛ በፈቃዳቸው ያልታወጀውን ጾም የሚጾሙ ሰዎችን ዝም ብሎ አይመለከታቸውም። ምክንያቱም ይህ ታላቅ የመንፈሳዊነት ደረጃ እንደ መሆኑ ጠላት ሥራውን ትቶ ሳይዋጋ አይተዋቸውም። ስለዚህም ርኵስ መንፈስ ሰማያዊ ዋጋቸውን ለማሳጣት ልዩ ልዩ ፈተና እንደሚያመጣባቸው አስቀድሞ መገንዘብና በትዕግሥትና በትኅትና ሆነው ለመዋጋት መዘጋጀት አለባቸው። እነርሱ በመጾማቸው ታላቅ እንደ ሆኑና የማይጾሙት ደካሞች እንደ ሆኑ አስመስሎ እያሳየ በትዕቢት ስለሚዋጋቸው በፍጹም ትኅትና ሆነው መጾም አለባቸው። “ሰይጣን እንዳያታልለን አሳቡን የምንስተው አይደለምና።” (፪ ቆሮ. ፪፥፲፩።) እንዲል። •  ይህን ወቅት ከላይ በተገለጸው መሠረት ፈቅዶ በጾም ማሰብ በእጅጉ አስደሳች ተጋድሎ ነው። በተቻለ መጠን ቅዳሴ እያስቀደሱ (በተለይ በሰንበተ ክርስቲያን) ሥጋውን መብላትና ደሙንም መጠጣት መረሳት የለበትም። በቅዱስ ቍርባን ያልታተመ ምግባርም ሆነ ትሩፋት ለዘለዓለማዊ ሕይወት አያበቃምና። ይቆየን። መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በነገሮች ሁሉ ማስተዋሉን ያድለን!!! “ተግሣጽን የሚወድድ ዐውቀትን ይወድዳል፤ ተግሣጽን የሚጠላ ግን ሰነፍ ነው።” ምሳ. ፲፪፥፩። ወርኃ ጽጌን በሰላም ለመፈጸምና እንደየአቅማችንና በጎ ፈቃዳችን በምንፈጽማቸው ምግባራት የአረጋዊው ዮሴፍን፣ የሰሎሜን፣ የእመቤታችንንና የልጇን በረከተ ስደት እንድናገኝ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን!!! አሜን ወአሜን፤ ለይኩን ለይኩን።
Hammasini ko'rsatish...
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
#Update የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ውጤት መቼ ይገለጻል? የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ውጤትን ቶሎ ለማድረስ በሙሉ አቅም እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡ ፈተናውን የማረም ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ማንጠግቦሽ አዳምጤ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡ ከመስከረም 07 እስከ 11/2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ጨምሮ ውጤት ለመግለፅ መታሰቡን ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡ "ምናልባትም እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል" ተናግረዋል፡፡ በነሐሴ መጨረሻ በሰጡት መግለጫ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል ውጤት እስከ መስከረም አጋማሽ ድረስ ይፋ ይደረጋል ብለው እንደነበር አይዘነጋም። በትግራይ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ለነበሩ ተማሪዎች ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 02/2016 ዓ.ም የመልቀቂያ ፈተናው ይሰጣል መባሉ ይታወቃል። #Share #share 🙏 ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ይቀላቀሉ ፤ https://t.me/Temhert_Minister https://t.me/Temhert_Minister
Hammasini ko'rsatish...
Hammasini ko'rsatish...
Esdros S.C

እንኳን ወደ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ/ማህበር የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ፡፡ This is Esdros S.C's official Telegram channel. For more updates please visit www.Esdros.com