2 813
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
+530 kun
Postlar arxiv
Repost from Jinka University's Official Channel
የቀድሞው የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኩሴ ጉዲሼ(ዶ/ር) እና አዲሱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ ይትባረክ(ዶ/ር) የስራ ርክክብ አደረጉ።
**ግንቦት 8/2017ዓ.ም**
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ ይትባረክ(ዶ/ር) ወደ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ መግባታቸውን ተከትሎ ዛሬ ግንቦት 8/2017ዓ.ም የስራ ርክክብ መርሃግብር ተካሂዷል።
ወደ ጂንካ ከተማ ሲገቡ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም በአሪ ዞንና በጂንካ ከተማ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ቀደም ሲል በለቀቅነው ልጥፋችን መዘገባችን ይታወሳል።
ከሰአት በኋላ በነበረው ፕሮግራም ደግሞ በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር ዴስክ ሀላፊ በሆኑት በአቶ አብዶ ናስር መሪነት የስራ ርክክብ ተካሂዷል።
የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት "ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከ2013-2017" በሚል ሰፋ ያለ ሪፖርት አቅርበው የዩኒቨርሲቲው አሁናዊ ሁኔታዎችና "በቀጣይ ትኩረት ቢደረግባቸው" ያሏቸውን ነጥቦች በማብራራት ለአዲሱ ፕሬዚዳንት አስረክበዋል።
የት/ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና የዩኒቨርስቲው የስራ አመራር ቦርድ አባል የሆኑት የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ፤ ዶ/ር ኩሴ በነበራቸው ቆይታ ዩኒቨርስቲውን ወደፊት ያራመዱ በርካታ የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን በመስራታቸው እንዲሁም ግልፅና ፍፁም ቅንነት የታየበት የርክክብ ሪፖርት አዘጋጅተው በማቅረባቸው ልባዊ ምስጋናቸውን የገለፁ ሲሆን ዶ/ር ዮሃንስም በበኩላቸው ከተደረገላቸው የአቀባበል ስነስርዓት ጀምሮ በርክክብ ሂደቱ እጅግ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ዮሃንስ ከሁሉም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት ብሎም ከአካባቢው የስራ ሀላፊዎች ጋር በመተባበር የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ ሊያሳኩ በሚችሉ ተግባራት ላይ ተግተው እንደሚሰሩ በመግለፅ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት ለመወጣት ያላሰለሰ ጥረት እንደሚያደርጉም አብራርተዋል።
በርክክቡ የታደሙት የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት አባላትም ከዶ/ር ኩሴ ጋር ለነበራቸው ቆይታ እንዲሁም ላደረጉት አስተዋጽኦ ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀው በቀጣይም ከአዲሱ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ጎን በመሆን በዩኒቨርሲቲው የትኩረት አቅጣጫዎችና በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጡ በቁልፍ የአፈፃፀም አመላካቾች (Key Performance Indicators) ላይ ጠንክረው እንደሚሰሩ ቃል በመግባት የስራ በርክክብ መርሃግብሩ ተጠናቋል።
Repost from Jinka University's Official Channel
የቀድሞው የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኩሴ ጉዲሼ(ዶ/ር) እና አዲሱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ ይትባረክ(ዶ/ር) የስራ ርክክብ አደረጉ።
**ግንቦት 8/2017ዓ.ም**
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ ይትባረክ(ዶ/ር) ወደ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ መግባታቸውን ተከትሎ ዛሬ ግንቦት 8/2017ዓ.ም የስራ ርክክብ መርሃግብር ተካሂዷል።
ወደ ጂንካ ከተማ ሲገቡ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም በአሪ ዞንና በጂንካ ከተማ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ቀደም ሲል በለቀቅነው ልጥፋችን መዘገባችን ይታወሳል።
ከሰአት በኋላ በነበረው ፕሮግራም ደግሞ በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር ዴስክ ሀላፊ በሆኑት በአቶ አብዶ ናስር መሪነት የስራ ርክክብ ተካሂዷል።
የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት "ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከ2013-2017" በሚል ሰፋ ያለ ሪፖርት አቅርበው የዩኒቨርሲቲው አሁናዊ ሁኔታዎችና "በቀጣይ ትኩረት ቢደረግባቸው" ያሏቸውን ነጥቦች በማብራራት ለአዲሱ ፕሬዚዳንት አስረክበዋል።
የት/ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና የዩኒቨርስቲው የስራ አመራር ቦርድ አባል የሆኑት የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ፤ ዶ/ር ኩሴ በነበራቸው ቆይታ ዩኒቨርስቲውን ወደፊት ያራመዱ በርካታ የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን በመስራታቸው እንዲሁም ግልፅና ፍፁም ቅንነት የታየበት የርክክብ ሪፖርት አዘጋጅተው በማቅረባቸው ልባዊ ምስጋናቸውን የገለፁ ሲሆን ዶ/ር ዮሃንስም በበኩላቸው ከተደረገላቸው የአቀባበል ስነስርዓት ጀምሮ በርክክብ ሂደቱ እጅግ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ዮሃንስ ከሁሉም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት ብሎም ከአካባቢው የስራ ሀላፊዎች ጋር በመተባበር የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ ሊያሳኩ በሚችሉ ተግባራት ላይ ተግተው እንደሚሰሩ በመግለፅ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት ለመወጣት ያላሰለሰ ጥረት እንደሚያደርጉም አብራርተዋል።
በርክክቡ የታደሙት የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት አባላትም ከዶ/ር ኩሴ ጋር ለነበራቸው ቆይታ እንዲሁም ላደረጉት አስተዋጽኦ ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀው በቀጣይም ከአዲሱ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ጎን በመሆን በዩኒቨርሲቲው የትኩረት አቅጣጫዎችና በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጡ በቁልፍ የአፈፃፀም አመላካቾች (Key Performance Indicators) ላይ ጠንክረው እንደሚሰሩ ቃል በመግባት የስራ በርክክብ መርሃግብሩ ተጠናቋል።
Repost from Jinka University's Official Channel
+9
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመደቡት ዮሐንስ ይትባረክ(ዶ/ር) ወደ ጂንካ ገቡ።
*****ግንቦት 8/2017ዓ.ም******
በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ለጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንትነት የተመደቡት ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር) ወደ ጂንካ ከተማ ገብተዋል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባል በሆኑት በአቶ አብረሃም አታና በሌሎች በአሪ ዞንና በጂንካ ከተማ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የቀድሞው የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ኩሴ ጉዲሼ(ዶ/ር)ን ጨምሮ በተቋሙ ማኔጅመንት አባላት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ከቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የስራ ርክክብ የሚያደርጉ ሲሆን ከርክክቡ በኋላ መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል።
+2
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሚያዚያ 30/08/2017 ዓ.ም ማለትም ነገ ሐሙስ ለሚካሄደው ታላቅ የኪነጥበብ ምሽት ዕውቅና ተወዳጅ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ጂንካ አየር ማረፍያ ስደርሱ አቀባበል ተደረገላቸው። ነገ በሚኖረው የኪነጥበብ ምሽት ላይ ከ11:00 ጀምሮ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም የአከባቢው ማህበረሰብ እንድገኙ በክብር ተጋብዘዋል።
ማስታወቂያ
ከዚህ በታች በስም የተጠቀሳችሁ የትምህርት ክፍል ተማሪ ተወካዮች(Gc committee) የተመራቂ ተማሪዎች ባይንደር፣ መፅሔትና ሪባን ማሰርያ ቅፅ ያልወሰዳቹና የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ ያልጀመራቹ ስለሆነ በአስቸኳይ የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት በመምጣት ቅፁን ወስዳቹ የትምህርት ክፍላቹን ተማሪዎች እንድታስተባብሩ መልዕክታችንን እያስተላለፍን ይህን ሳታደርጉ ብትቀሩና በኋላ ለሚፈጠረው መጓተት ተጠያቅ አለመሆናችንን በቅድሚያ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።
1. Economic Department
2.Tourism Department
3.Biology Department
4. Chemistry Department
5. Physics Department
6. Mathematics Department
7. Sport science Department
8.Computer science Department
9.Statistics Department
10.Geography Department
11. History Department
12. Psychology Department
13. Civics Department
14. Plant science Department
15.Agroeconomics Department
16. Agribusiness Department
17.Animal Health Department
ለበለጠ መረጃ፦ 0938692583
ለሁሉም የክበባትና ማህበራት አባላት ተማሪዎች በሙሉ፦
በቀን 27/08/2017 ዓ.ም በተማሪዎች ህብረት በኩል ዕውቅና የተሰጠውና የተዘጋጀ ምንም የፅዳትምና የደም ልገሳ ፕሮግራም አለመኖሩን እያሳወቅን እንዲህ ዓይነት ሀሰተኛ መረጃ ከሚያናፍሱ ራሳቹን እንድትጠብቁ እያሳወቅናቹ ማንኛውም ተማሪ ሀሰተኛ መረጃን ስያሰራጭ ብገኝ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑን በአፅንኦት ልንገልጽላችሁ እንወዳለን።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
ለሁሉም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ፦
የ50 days left ፕሮግራም በቀን 19/08/2017 ዓ.ም ማለትም እሁድ ዕለት እንደሚከበር ይታወቃል። በመሆኑም የፕሮግራሙን T-shirt የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት የሚገኝ ሲሆን ሳያልቅ በጊዜ እንድትወስዱ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።
የአንዱ T-shirt ዋጋ 250 ብር
ለበለጠ መረጃ፦ 0938692583.
+5
የ2017 ዓ.ም የትንሳኤ በዓል በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የትንሳኤ በዓል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉዲሼ እንዲሁም የአስተዳደር ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ አይላቴና ለሎች የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት በተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉዲሼ ለተማሪዎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ተማሪዎች በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሆነው በዓላት ስያከብሩ እርስ በርሳቸው በመተሳሰብ በመረዳዳትና በአብሮነት በመከባበር በዓላትን እንድያሳልፉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
