2 813
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+530 kunlar
Postlar arxiv
+1
ለጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዳዲስ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተመደቡ።
ነሐሴ 9/2017ዓ.ም
ጂንካ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ዶ/ር ተስፋዬ አለሙን የአካዳሚክ፣ ምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠባባቂ ም/ፕሬዚዳንት እንዲሁም ዶ/ር መልካሙ ዘሮን የአስተዳደር እና ልማት ተጠባባቂ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ መድቧል።
ለአዲዲስ ምክትል ፕሬዚዳንቶች መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን።
+2
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረትና የሠላም ፎረም ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ከ2015 ዓ.ም - 2017 ዓ.ም ሲያገለግሉ ለነበሩ ሥራ አስፈጻሚዎች የትምህርት ጊዜያቸውንና የአገልግሎት ዘመናቸውን በማጠናቀቃቸው የሽኝት ፕሮግራም ተካሄደ።
የዩኒቨርሲቲው 3ኛ ዙር የተማሪዎች ህብረትና የሠላም ፎረም ተመራጭ የነበሩ ሥራ አስፈጻሚዎች የትምህርት ጊዜያቸውንና የአገልግሎት ዘመናቸውን ማጠናቀቃቸውን አስመልክቶ የሽኝት ፕሮግራም ተካሄደ። በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ይትባረክ የአስተዳደር ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ አይላቴ እና ለሎችም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆ በፕሮግራሙ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ይትባረክ ለሚሸኙ ሥራ አስፈጻሚዎች በተማሪዎች አደረጃጀት ውስጥ ሆነው በትጋት ዩኒቨርሲቲውን በማገልገላቸው ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይሄንን ትጋታቸውን ወደፊት በሚሰማሩበት የሥራ መስክ ሁሉ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን አያይዘውም መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ አይላቴ ለሚሸኙ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በሥራ ዘመናቸው ተቋሙን ደከመን ሰለቸን ሳይሉ በማገልገላቸው በማመስገን በቀጣይ መልካም ሁሉ እንድገጥሟቸው መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
+4
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ ዙር የተማሪዎች የምረቃ ፕሮግራም በታላቅ ድምቀት አካሄደ።
ሰኔ 14/2017ዓ.ም
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸው የመጀመሪያ ዲግሪና የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ደማቅ የምረቃ ፕሮግራም አካሂዷል።
በቅድመ ምረቃና በድህረምረቃ ፕሮግራሞች ከ850 በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 71 የሚሆኑት የድህረ-ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በምረቃ መርሃግብሩ ላይ በርካታ የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ ይትባረክ ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ዶ/ር ዮሐንስ ዩኒቨርሲቲው ከተልእኮው አንፃር በመማር ማስተማር፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ያከናወናቸውን አንኳር ተግባራት ጥቅል መረጃ ያቀረቡ ሲሆን ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ ም/ሰብሳቢና የዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩት ፕሮፌሰር አሰፋ አስማረ ተመራቂ ተማሪዎች በተማሩበት የሙያ መስክ ሀገርንና ህዝብን በታማኝነትና በቅንነት እንዲያገለግሉ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ለውጥ ጠንክረው እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ቡና ኢንሹራንስ አ.ማ ስድስት እንዲሁም ጊፍት ሪልስቴት ደግሞ አስር ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች በቋሚነት የስራ ዕድል ለመፍጠር በስራ አመራር በቦርድ አባላት አማካኝነት ቃል በመግባት ሌላኛው የምርቃቱ ድምቀት ሆነዋል።
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተመራቂ ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ ማለትም ሰኔ 14/2017ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል።
በመጀመሪያ ዲግሪና በሁለተኛ(በማስተርስ) ዲግሪ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸው ተማሪዎችን አዲስ ባስገነባው ዘመናዊ የመመረቂያ አዳራሽ ሰኔ 14 ቀን 2017ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ መሆኑን እየገለፅን ለተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦች ከወዲሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!!
ለ4ኛ ና 5ኛ ዓመት የተመራቂ ተማሪ ተወካዮች( የክፍል ተወካዮች)፦
የመመረቂያ ባይንደርና ሪባን ስለመጣ በቀን 07/10/2017 ከጠዋቱ 2:00 ላይ የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት ተገኝታቹ እንድትረከቡ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
+1
ማስታወቂያ
ለተመራቂ ተማሪዎች
ከዚህ በፊት ለመመረቂያ ባይንደርና ሪባን በክፍል ተወካዮቻቹ አማካኝነት ያልተመዘገባቹና ገንዘብ ያልከፈላቹ ጥቂት ባይንደሮችና ሪባኖች ስላሉ ከቀን 04/09/2017 - 06/09/2017 ዓ.ም ድረስ የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት ተገኝታቹቹ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ፦ 0992688916
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
ለሁሉም የExist exam ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ፈተና እንዲሆንላቹ የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት ይመኛል።
መልካም ፈተና!!
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
Repost from Jinka University's Official Channel
ማስታወቂያ
==========
ለመውጫ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
....................
ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በሚሰጠዉ የመውጫ ፈተናዎች የምትቀመጡ ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍሎች በምትመጡበት ጊዜ ማንኛውም ዓይነት ሞባይል ስልክ ይዞ መምጣት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን። ይህንኑ በመተላለፍ ይዞ የተገኘ ተፈታኝ ከፈተና የሚሰናበትና የዲሲፕሊን ቅጣት የሚጠብቀው/ቃት መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
ዩኒቨርሲቲው
+8
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ 1446ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በድምቀት ተከበረ!
==========================
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የ1446ኛው ዓመት ሂጅራ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ይትባረክ የአስተዳደር ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ አይላቴ እና የአካ/ቴ/ሽ/ማ/አ/ም/ፕሬዚዳንት ተወካይ መ/ር ኢብራሂም ጀማልና ለሎች የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በበዓሉ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ተማሪዎች በዓላትን ስያከብሩ በአንድነትና በአብሮነት በኢትዮጵያነት ስሜት ያለምንም ልዩነት እንዲያከብሩ እንዲሁም በትምህርታቸውም ብርቱና ጠንካራ እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
🌙ኢድ ሙባረክ! 🌙
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው ዓ.ሂ የኢድ አል-አድሃ አረፋ በዐል በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ በተለይም ለዩኒቨርሲቲያችን ሰራተኞችና ተማሪዎቻችን በራሴና በዩኒቨርስቲው ስም እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ።
መልካም በዓል ይሁንላችሁ ዒድ ሙባረክ!!
ዮሐንስ ይትባረክ (ዶ/ር)
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት
ማስታወቂያ
ለ4ኛ ዓመት ለስፖርት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች በሙሉ፦
የመመረቂያ ባይንደርና ሪባን ፈላጊ ተማሪዎች ስም ዝርዝራቹና ገንዘቡ በተወካዮቻችሁ በኩል ለተማሪዎች ህብረት እንዲቀርብ በተደጋጋሚ መልዕክት ብናስተላልፍም መቅረብ አለመቻሉ ይታወቃል። በዚህም ምክንያት ለሚፈጠረው ክፍተት የማንጠየቅ መሆኑን አስቀድመን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
+2
ከግንቦት 01/2017 ዓ.ም ጀምሮ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመደቡት ዶ/ር ዮሐንስ ይትባረክ ጋር የተማሪዎች ህብረት ሥራ አስፈፃሚዎች የትውውቅና የእንኳን ደህና መጡ ፕሮግራም አካሄዱ። በትውውቅ ፕሮግራሙ ላይ ለአዲሱ ፕሬዚዳንት የተማሪዎች ህብረት አደረጃጀት ስጦታ ያበረከቱ ሲሆን የአገልግሎት ዘመናቸውም የስኬት እንዲሆንላቸው ልባዊ መኞታቸውን ገልፀዋል።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
