እንደ ንስር ሁኑ‼
===========
✍ ንስር አሞራን ለማጥቃት የሚደፍረው ብቸኛ ወፍ "ቁራ" ነው።
The only bird that dares to attack an eagle is the crow.
ከታች በፎቶው ላይ እንደምትመለከቱት ከጀርባዋ ላይ ይሆንና አንገቷን በመንከስ ያጠቃታል።
It sits on its back and bites into the eagles neck.
ነገር ግን ንስሯ ለቁራው አጸፋ አትመልስም፣ አትታገለውም። አቅም አጥታ እንዳይመስላችሁ። ይልቁንም ለእርሱ ምላሽ በመስጠት ጊዜዋንና ጉልበቷን አታባክንም።
However, the eagle does not respond nor fight with the crow;it spends no time or energy on the crow.
እና ምን ታደርጋለች?!
ክንፏን ትከፍትና ወደ ሰማይ ከፍታ መብረር ትጀምራለች።
It just opens it wings and starts to soar higher into the heavens.
ከዚያስ? ከዚያማ የንስሯ የከፍታ ጉዞ በጨመረ ቁጥር፤ ቁራው የመተንፈስ አቅሙ እየቀነሰ ይመጣል።
በመጨረሻም ኦክስጂን ስለሚያንሰው ኃይል ያጣና ይወድቃል።
The higher the flight, the tougher it is for the crow to breathe and then the crow falls down from lack of energy.
ታዲያ ምን ለማለት ነው? ወደ ግብህ በተጠጋህ ቁጥር፤ መሰናክሎችና ተግዳሮቶች ይበዙብሀል። ነገር ግን ተቋቁመህ ጉዞህን ወደፊት ከገፋኸው፤ አላስፈላጊ የሆኑ መሰናክሎች ሁሉ ሳትዋጋቸው በራሳቸው ጊዜ ይከስማሉ።
It simply means that once you move closer to your goals, you'll be faced with obstacles and challenges but when you keep pushing yourself forward every other unnecessary obstacle will fall by itself.
አንዳንድ ሰው አጋጣሚዎችን እየጠበቀ ሊያጠቃህ ይሞክራል! የርሱ ስኬት በአንተ መቃብር ላይ ይመስለዋል። የርሱ እድገት አንተ ካልወደቅክ የሚሳካ አይመስለውም። የሚገርመው እኮ አንተ ያለህን ነገር እርሱ ቢይዘው አጠቃቀሙን እንኳ ላያውቅበት ይችላል። ታዲያ ካልተጠቀመበት ምን አለበት ቢተውህ?
ነገሩ McGowan እንደሚለው ነው።
"This would be kind of like a dog chasing a car and jumping up on it, Dogs always want to catch the car, but they never know what they'd do if they get it."
«ውሾች መኪና ሲያልፍ ይጮኻሉ። አንዳዶች ከላዩም ላይ ዘለው ይወጣሉ። ነገር ግን መኪናውን ቢያገኙት እንኳ ምን መሥራት እንዳለባቸው አያውቁም።»
አንዳንዱ ሰው ለምን እንደሚተችህ እንኳ አያውቅም‼
እናማ ወንድሜ!
You don't have to respond to all fights. You don't have to respond to all arguments or critics.
ለሁሉም ትግል፣ ክርክርና ትችት መልስ መስጠት የለብህም። በሚሰነዘርብህ ትችትና አሉባልታም ልታዝንና ልትከፋ አይገባም።
Raise a standard, they'll fall‼
መርህ ይኑርህ፣ ዝም ብለህ ወደላይ ከፍታህን ቀጥል!፤ አልቻል ስትላቸው እነርሱ የሆነ ቀን ተስፋ ቆርጠው ይወድቃሉ።
Stop wasting time with the 'crow'!
ከ"ቁራዎች" ጋር ጊዜህን አታባክን‼
እንደ ንስር ሁን! ከፍ በል‼
(ደግሞ «አላህ የሰው ልጅ አድርጎ ፈጥሮን፣ የሰውን ልጅ በእርግጥም አክብሬዋለሁ! ብሎን፤ እንደት "እንደ ንስር አሞራ ሁኑ!" ይለናል⁉️ ብላችሁ ረድ እንዳትሰጡብኝ።
እኔ እንደ ንስር ሁኑ ማለቴ ከቁራ ጋር ላላት ትግል የተጠቀመችውን ስልት ተጠቀሙ ለማለት እንጅ ሰውነታችሁን ትታችሁ እንደ እርሷ ክንፍና እግር ያላችሁ ሁኑ ማለቴ አይደለም¡)
ለማንኛውም ይመቻችሁ‼
ሃሳቡን ከአንድ የእንግሊዝኛ ጽሑፍ የወሰድኩት ነው!
||
ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ
=========
ጥር 29, 2013 E.C
February 06, 2021 G.C
||
t.me/MuradTadesse