uz
Feedback
አጫጭር ልብ ወለድ

አጫጭር ልብ ወለድ

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
2 886
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
Ma'lumot yo'q30 kun
Postlar arxiv
🛑Petition ለመፈረም https://keap.page/gq193/.html

ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአውሮፓ ህብረት ጋራ የፈረመችውን ስምምነት በመቃወም የተዘጋጀ የፊርማ ማሰባሰቢያ ቅጽ ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደV አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡ ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡- ሀ) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣ ለ) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣ ሐ) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣ መ) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣ ሠ) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣ በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡ በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረJ የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ (Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡ የዚህንም ስምምነት አደገኛ አንቀጾችንና በኤክስፐርቶች የተሰጠውን ትንታኔ የያዘ ዶኩመንት በአባሪነት ያቀረብን መሆናችንንም በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

Repost from Musse Solomon
‼️❌❌❌‼️ ኢትዮጵያ🇪🇹በቅርቡ ግብረሰዶማዊነት🏳️‍🌈፣የጾታ መቀየር፣ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የቀረበን ሰነድ ፈርማለች። 😭 ይህም ሰነድ በዚህ አንድ ወር ውስጥ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲፀድቅ ይጠበቃል።🤯 ለዚህም መቃወሚያ Petition በትንሹ 50,000 ፊርማዎችን ለማሰባሰብ በዚህ Link እንሳተፍ። 🇪🇹Say NO!! ታሪክ የማይረሳውንና  እስከትውልድ ጥግ  በመልካሞቹ የሚዘከረውን ይህን movement በደስታ ተቀላቀሉ!!! 🛑Petition ለመፈረም https://keap.page/gq193/.html 🛑Tiktok https://vm.tiktok.com/ZM66xSPCn/ 🛑Telegram Group join ለማድረግ https://t.me/+ZtUngZzXFUIzOTZk

Boss Men's watch 2,800 Birr only buyer negotiations Free Delivery +251920594652
+2
Boss Men's watch 2,800 Birr only buyer negotiations Free Delivery +251920594652

NEW ARRIVAL 🔥 DIESEL Mens watch New design just in🔥 2900 Birr inbox me Free delivery Any where 0920594652
+1
NEW ARRIVAL 🔥 DIESEL Mens watch New design just in🔥 2900 Birr inbox me Free delivery Any where 0920594652

the time of ethiopia
the time of ethiopia

g0አጫጭር ልብ ወለድ🔊: ሁለት ልብ ክፍል 3 በቅናት እርር እላለው ........ ባነጋገሮ ስስቅ "ምነው ሳቅሽ " አይ ምንም እንደዚ ልብሽ ውስጥ የገባው ማነው? በተቆራረጠ ድምፅ " ና....ቲ.... ነው። ሄዋንዬ "በእናትሽ እንዳትነግሪው" አለችኝ ከየት መጣየማይባል ዘበኛችን እስራችን ደርሶ ውደ ክፍላቹ አገብም በዚ ሰአት ምንድነው? እኛም ልንገባ ብላነው ወደ ዶርማችን አመራን "ክርስቲ የሸገር ልጅ ናት" ህሮብ ቀን ፈተና ተፈትነን ከጀለሶቼ ጋር የምንቀመጥበት ቦታ ሄድን ዛሬ ክርስቲን ላስተዋውቃት ነው መንገድ ላይ አሮን ና ናቲ አጠገባችን ደረሱብን ሰላም ብለውን እንደማለፍ ሲሉ "እንዴ ምንነው? አሮን "ከሰው ጋር ነሽ ብለን ነው ሚስጢር የባቄላ ......ጨርሽው አለ። እየሳቀ "በሉ ሁሌ ሶስት ለአንድ ነበር አሁን ደሞ ሁለት ለሶስት እመራለሁ" ናቲ ውድያው ገብቶታል woww welcome" እያላ ውደ ክርስቲ መጠጋት ጀመረ "ናቲ እባላለው ይሄ አሮን ያ ደሞ ሳሚ ወደ ባታው ላይ እየጠቆመ። ግን ወደኛ ስገቢ መስፈርት አለው? "እኔ አስደነገጠኝ የምን መስፈርት? "እስቲ ዝም በይ ማን ጠየቀሽ ለሷ ነው ።..... ሁሉንም ተዋውቃ ልክ እንደቆየን ጓደኛሞች መሳቅ ማውራት ጀመረች ከሰው ጋር ቶሎ ስለምትግባባ አልከበዳትም ። "አሮን ና ናቲ በፈተነው መከራከር ጀመሩ። አቤት የነሱ ክርክር እንዴት ደስ እንደሚል በዛ ሰዓት ክርስቲ "በአይኖ ሰረቅ እያደረገ ናቲን ታየዋለች" ድንገት እኔ ክርስቲ አይን ተገጣጠመ ሁለታችን ለሳቅ ቅርብ ነን። ክት በለን ስንስቅ ደንግጠው ሳሚም ገርሞት እናዛም ከሚከራከሩበት ዝምታ ሰፈነ አንዴ እኔን እሷን አይናቸው ማማተር ጀመረ ። አሮን "ምንድነው? " " እንዴ እራበኛ በማለት ወሬ አስቀየስኩ...... የተለመደው ቤት ሄደን ዛሬ ሁለት ሴት ሶስት ውንድ ሆነናል መጎራረሳችንን ጀመርን ልክ እንደጨረስን አሮን ግቢ መሄድ አለብኝ አለ። እኛ ትኩስ ነገር ለመውሰድ ውደካፊ አመራን እኔ ሳሚ ከኃላ ናቲ ክርስቲ ከፊ ሰዓቱ 10:30ስለሆነ ብዙም ፀሀይ የለም ሊዊ ካፊ ገብተን ስንጫውት ሳናስበው 11:30ሆና እኔ ልሄድ እንደሆነ ስናግራቸው ክርስቲ "ከዘ የሞቀ ጨዋታ ላይ" ሳሚን አስነስቼ እንዲሸኛኝ አደረኩ ዶርም ገብቼ ድንገት ስልኬ ጠራ "ምን ነበር "አልኩ እንደመኮሳተር ሳሚ ነበር "አብረን እንድንሄድ ነው በር ላይ እጠብቅሻለው "ከዶርም እንደውጣው እየጠበቀኝ ነበር "ዛሬ እንዴት ውደዚ መራክ " "መቼም እኛ ሰዎች ስንባል ስንቸገር ነው ውደ አምላካችን የምናዘውትረው"አለ እየተነፈሰ እኮ እንደ አንተ አይነቱ ነው እየሳኩበት ግን እንደዚ ለምን አለ? ስንመለስ የምነግርሽ ነገር አለ ብሎኝ በውንድ መግቢያ ሄደ ስንመለስ ማታ ስለናበር ወክ ማድረግ ጀመርን። እእእ በላ ንገረኝ ምንድነው? ሳሚ "ተረጋጊያ ግጥም ላነብልሽ ነው " ሳኩበት ....እንዴ ከመቼ ጀምሮ ነው ግጥም....መግጠም ... .......እእእ። እሺ ልስማዋ? #እኔ_ምን_አውቃለው እኔ ምን አውቃለው ሳይሽ ደስ ይለኛል ስላንቺ አስባለው አመመኝ ደከመኝ አጣው መድኃኒት ፍቅርሽ አስጨነቀን እንደልብ ውጋት መውደዴ ከሆነ እኔ አንቺን ማየቱ ልቤ ከተሰማው የፍቅር ግለቱ ገረመኝ እራሴን ሳየው ሁኔታዬን ውዳንቺ እያደላ እቢ አለኝ ተው ብለው ነጋ ጠባ አንቺን ነው የማስበው ልቤ ተቆልፎ ያስባል ለብቻው ግን ግን የምውዳት ልጅ ያቻትና መክፈቻው . ......""ሂዋን...ምን ሆንሽ ....አይኔ። ..።።።። ቆይ ላውጣልሽ ተጠጋኝ በጣም ተጠጋጋ.......አውጥቶልኝ ......... ይቀጥላል....... .. @achirlebwelod

🌻🌻እንኳን ወደ አጫጭር ልብ ወለድ  ቻናል በደህና መጡ!🌻🌻 ➫ የልብ ወለድ  ቻናል ለመቀላቀል ይህንን link ይጫኑ!👇 https://t.me/joinchat/AAAAAEpXJy1v7PIXSES7uw    አጫጭር ልብ ወለድ👇 ➫መጪውን 🌻አዲሱን አመት🌻ምክንያት በማድረግ እንኳን ለ2016 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ እያለ "ይህንን መልዕክት" እስከ መስከረም 25 ድረስ ለ"50" ሰዎች ለሚልኩ ደንበኞች                  ➫የ 1000 MB ነፃ ኢንተርኔት                  ➫የ 120 ደቂቃ ነፃ የአየር ሰዓት እና                  ➫የ 150 ነፃ የሚሴጅ አገልግሎት ይላክሎታል!!! 🌻🌻🌻🌻እንኳን ለ2016 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ🌻🌻🌻 👇👇👇👇 ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ ይጠቀሙ!!!

🌻🌼🌻 ሐድስ መዋዕሊነ ከመ ትካት 🌼🌻🌼    ትርጉም 🌼 አቤቱ ዘመናችን እንደቀድሞው አድስ 🌼     ሰቆ.ኤር ም ፭ ቁ ፳፩                     5     21 🌼 እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም አሻጋግረን 🌼 🌻 መልካም አዲስ አመት 🌻 🌼 ፳፻፲፮ ዓ.ም 🌼 @achirlebwlod

በጽኑ ህመም ውስጥ ከነበረች ልጃቸው ጎን ለ38 ዓመታት ያልተለዩ እናት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እናት ለልጆቿ ስትል የምትከፍለው መስዕዋትንት ከቃላት በላይ እንደሆነ እንመለከታለን፤ ከሰሞኑም በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ የሰፈረው የእናትና ልጅ ታሪክ ይህን እውነታ ያሳያል። ኤድዋርዳ ኦባራ የተባለች የስኳር ህመምተኛ አሜሪካዊት ታዳጊ በ16 ዓመቷ በፈረንጆቹ 1969 የሳንባ ምች ሰለባ ስትሆን በሽታው ተደራራቢ እና ጽኑ ስለሆነም ቤተሰብ ወደሆስፒታል ቢወስዷት ሊሻላት አልቻለችም፡፡ በዚህ ጭንቅ ውስጥ ልጅ የእናቷን አይን እያየች ‘’እናቴ ከጎኔ አትለይ’’ ስትል ትጠይቃለች፡፡ እንኳን አደራ ተብላ እንደውም የእናት አንጀት እንስፍስፍ ነውና በፍጹም ከጎንሽ አልለይም በማለት እናት ለልጃቸው ቃል ገቡ። ኤድዋርዳ ህመሟ ይጸናባትና በጽኑ ህመም (ኮማ) ውስጥ ሆና ቀናት፣ ሳምንታት፣ ወራት ተቆጠሩ፤ ዓመታትም አልፈው አደዋርዳ ከገባችበት ጽኑ ህመም ውስጥ ሳትወጣ ለ42 ዓመታት ቆይታ ህይወቷ አለፈ። በእነዚህ ዓመታት ውስጥም እናት ልጃቸውን ከተኛችበት አልጋ ሳይርቁ የሚችሉትን ሁሉ እንክብካቤ አደረጉ። እንቅልፍ ከ90 ደቂቃ በላይ ተኝተው የማያውቁት እናት ለልጃቸው ሙዚቃ በማንጎራጎር፣ መጽሃፍት በማንበብ እና ታሪኮችን በመንገር ያሳልፉ ነበር። ቤተሰቡን ይደጉም የነበረው አባትም ልጁን መንከባከብ ግድ ሲለው ስራውን ተወ፤ ለችግርም ተጋለጡ፤ በመጨረሻም ብዙም ሳይቆይ በልብ ህመም በሽታ ለህልፈት ተዳረገ፡፡ እናትም በ2008 ማለትም በ81 ዓመታቸው ከልጃቸው በፊት አለፉ፡፡ ከዚያ በኋላ እህቷ እየተንባከበቻት ለአራት ዓመታት ቆየች፡፡ ሆኖም በሽታውና ስቃዩ በርትቶባት መንቃት ባለመቻሏ እናቷ ከሞቱ ከአራት ዓመት በኋላ ከ42 ዓመታት የጽኑ ህመም ቆይታ በኋላ በ59 ዓመቷ ህይወቷ ሊያልፍ ችሏል፡፡ በዚህም የዓለም ጊነስ ሪከርድስ ኤድዋርዳን ራሷን ስታ (ኮማ) ውስጥ ለረጅም ጊዜ በመቆየት ሲል መዝግቤያታለሁ ብሏል ሰሞኑን፡፡ ዶ/ር ዌይን ዳየር ከማርሴለን ዳየር ጋር በመሆን “A Promise Is A Promise: Unbelievable Story of a Mother’s Unconditional Love and What It can Teach Us’’ በሚለው መጽሃፍ ውስጥ የኤድዋርዳን ታሪክ ከትቧል። ጸሃፊው እንዳለውም ይህ ሴራ ቀመስ የሆነ ታሪክ አይደለም፤ ወይንም በፍቅር ስለከነፉ ጥንዶች የሚያትት ልብ ወለድ መጽሃፍ አይደለም፡፡ እውነተኛ ጽናትና ፍጹም ፍቅር የታየበት እናትነት ነው፡፡ @achirlebwold

#ቡሄ ማለት ምን ማለት ነው ? #ደብረ ታቦረ ማለትስ ምንድነው @በምዕምዕናን ዘንድ ቡሄ ተብሎም ይታወቃል። #ቡሄ ማለት ብርሃኑ የደመቀ የጎላ ማለት ነው ይህም ስያሜ በደብረ ታቦር ጌታችንን ብርሃነ መለኮት ጋር መጋለጥ ጋር የተያያዘ ስያሜ ነው #ደብረ ታቦር ማለት የታቦር ታራራ ማለት ነው ተራራው ከገሊላ ባህር በስተምሥራቃዊ በደቡብ በኩል ይገኛል ፤ መሳ 4-6 14 ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ፤ ጌታችን ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ ደቀመዛሙርቱ በጠየቀችው ጊዜ አንዳንዶቹ መጥምቁ ዮሐንስ ሌሎች ኤልያስ ነው ሌሎችም ሙሴ ወይም ከነብያት አንዱ ነው ብለውት ነብር እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ ሲላቸው ቅዱስ ጰጥሮስ አንተ የህያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ መልሶለታል ይህ በሆነ በስድስተኛው ቀን ከሐዋርያት መካከል ሦስቱን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ከወጣ ብዋላ ብርሀነ መለኮቱን ገለጣቸው ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሄረ ሕያዋን ጠርቶ ያመጣቸው ሙሴ ብርሃንን አሳየኝ ብሎት ነብር (ዘጸ 33፦17-23) ስለ እርሱም ማንነት ግራ ለተጋቡ ጰጥሮስ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት እንደተናገረው የህያወ እግዚአብሔር ልጅ እንጂ ከነብያት አንዱ አለመሆኑና የዘለዓለም ሰዎች በዚህ እንዳይሰናከሉ በተግባር አስተማሯችዋል። ከዚያም ደመና ጋረዳቸው አብ ከሰማይ የምወደው ልጄ ይህ ነውና እርሱን ስሙት ሲል መሰከረ (ማቴ 17፤2) እንሆ መጣልን ቡሄ

በዚህ ግሩፕ ውስጥ ለምትሳተፉ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የ ደብረ ታቦር በአል ይሁንልን....እንኳን አደረስን💚💛❤️ ​​ቡሄ_በሉ ቡሄ በሉ (፪) - - ሆ ልጆች ሁሉ - - ሆ የኛማ ጌታ - - ሆ የዓለም ፈጣሪ - - ሆ የሰላም አምላክ - -ሆ ትሁት መሀሪ -ሆ በደብረ ታቦር - - ሆ የተገለጠው - ሆ ፊቱ እንደ ፀሐይ - ሆ በርቶ የታየው -ሆ ልብሱ እንደብርሃን -ሆ ያንፀባረቀው -ሆ ድምጽህን ሰማና በብህሩ ደመና(፪) የቡሄው ብርሃን ለኛ መጣልን(፪) ያዕቆብ ዮሐንስ-ሆ እንዲሁም ጴጥሮስ-ሆ አምላክን አዩት - - ሆ ሙሴ ኤልያስ - ሆ አባቱም አለ - - ሆ ልጄን ስሙት - - ሆ ቃሌ ነውና - - ሆ የወለድኩት - - ሆ አዝ====== ታቦር አርሞንኤም-ሆ ብርሃን ታየባቸው ሆ ከቅዱስ ተራራ ሆ ስምህ ደስ አላቸው- ሆ ሰላም ሰላም - - ሆ የታቦር ተራራ - - ሆ ብርሀነ መለኮት - ሆ ባንቺ ላይ አበራ -ሆ አዝ====== በተዋህዶ - - ሆ ወልድ የከበረው - ሆ የእግዚአብሔር አብ ልጅ - - ሆ ወልደማርያም ነው - -ሆ ቡሄ በሉ - - ሆ ቡሄ በሉ - - ሆ የአዳም ልጆች - - ሆ ብርሃንን - - ሆ ተቀበሉ - -ሆ አዝ====== አባቴ ቤት - - ሆ አለኝ ለከት - - ሆ እናቴ ቤት - - ሆ አለኝ ለከት - - ሆ ከአጎቴም ቤት - - - ሆ አለኝ ለከት - ሆ ተከምሯል - - ሆ እንደ ኩበት - - ሆ አዝ====== የዓመት ልምዳችን - - ሆ ከጥንት የመጣው - - ሆ ከተከመረው - ሆ ከመሶቡ ይውጣ - ሆ ከደብረ ታቦር - - ሆ ጌታ ሰለመጣ - ሆ የተጋገረው - ሆ ሙልሙሉ ይምጣ - ሆ አዝ====== ኢትዮጵያውያን - -ሆ ታሪክ ያላችሁ - ሆ ባህላችሁን - ሆ ያዙ አጥብቃችሁ - ሆ ችቦውን አብሩት -ሆ እንዳባቶቻችሁ -ሆ ምስጢር ስላለው -ሆ ደስ ይበላችሁ -ሆ አዝ====== አባቶቻችን - - ሆ ያወረሱን - - ሆ የቡሄን ትርጉም - - ሆ ያሳወቁን - - ሆ እንድንጠብቀው - ሆ ለእኛ የሰጡን - ሆ ይህን ነውና - - ሆ ያስረከቡን - - ሆ አዝ====== ለድንግል ማርያም ሆ አሥራት የሆንሽ ሆ ቅዱሳን ጻድቃን - - ሆ የሞሉብሽ - - ሆ በረከታቸው - - ሆ ያደረብሽ - - ሆ ሁሌም እንግዶች - ሆ የሚያርፉብሽ -ሆ ሀገረ እግዚአብሔር -ሆ ኢትዮጵያ ነሽ ሆ አዝ====== ለሐዋርያት - - ሆ የላከ መንፈስ - - ሆ ዛሬም ለኢትዮጵያ -ሆ ጸጋውን ያፍስስ ሆ በበጎ ምግባር - ሆ እንድንታነጽ - - ሆ በቅን ልቦና - ሆ በጥሩ መንፈስ - - ሆ በረከተ ቡሄ - ሆ ለሁላችን ይድረስ - ሆ = = = = = = ዓመት ዓውዳመት ድገም እና ዓመት ድገም እና በጋሽዬ ቤ ድገም እና ዓመት ድገም እና ያውርድ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና ወርቅ ይፍሰስበት ድገም እና ዓመት ድገም እና በእማምዬ ቤት ድገም እና ዓመት ድገም እና ይግባ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና ማርና ወተት ድገም እና ዓመት ድገም እና ይትረፍረፍ በእውነት ድገም እና ዓመት ድገም እና = = = = = = እንዲሁ እንዳላችሁ - -በፍቅር አይለያችሁ - - በፍቅር ላመቱ በሰላም - - በፍቅር ያድርሳችሁ - - በፍቅር ክርስቶስ በቀኙ - - በፍቅር ያቁማችሁ - - በፍቅር የመንግስቱ ወራሽ - - በፍቅር ያድርጋችሁ - - በፍቅር እንዲሁ እንዳለን - - በፍቅር አይለየን - - በፍቅር ለዓመቱ በሰላም - - በፍቅር ያድርሰን - - በፍቅር አማኑኤል በቀኙ - - በፍቅር ያቁመን - - በፍቅር የመንግስቱ ወራሽ - - በፍቅር ያድርገን - - በፍቅር = = = = = = የቅዱሳን መላክት የፃድቃን ሰማዕታት ረድኤት በረከት ይግባ በሁሉም ቤት በሁሉም ቤት(፪) ይግባ በረከት(፪) እንቁም በሃይማኖት ፀንተን በትጋት የአስራት አገር የአበው ቀደምት የቅዱሳን አባቶች ትውፊት ይገባልና ልንጠብቅ በእውነት ባህላችንን የአባቶች ትውፊት (፫) << ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል >> መዝ፹፰፥፲፪ ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

jአጫጭር ልብ ወለድ🔊: ❤️ሁለት ልብ ❤️ ክፍል 2 እረ ማሚ አስጨነቅሽኝ "ሄዋንዬ ድስ ብሎኛል አባትሽም ፀበል ገብቶል ውዶ አይደለም ልጄ እንደዛ የሆነው መቼም ዘንድሮ ሰው ለሰው ሰላም የማይመኝለት ዘመን ነው አሁንማ ያሁላ ቀርቶል እህትሽም ሁሉንም ተረድታው ብቻ ሁሉም እየተስተካከለ ነው አታስቢ ልጄ በርችልኝ ታናሽሽም ከትምርትቤቱ አንደኛ ውታ ተሸልማለች ለማንኛውም በርትተሽ ተማሪ " እሽ ማም by . . በአቅራብያዬ ካለው ቤተክርስቲያን ሄጄ የበፊቱ ሰላማችን ስለተመለሰልኝ አመስግኜ ስመለስ ዶርም ልገባ ስል ተደውለልኝ ሳሚ ነው። "ምን ፈለክ ድመቴ" አልኩ ስልኩን አንስቼ "መቼም ድመት አይጥ እንደሚፈል ታውቂዋለሽ የኔ አይጥ "ቆይ የት ሆነክ ነው እንደዚ የምታዝገኝ . "ባክሽ ሊዊ ካፊ ነኝ ለምን አትመጭም ምርጥ ለአየሩ የሚስማማ ትኩስ ነገር ልጋብዝሽ "እሺ ቆይ ነጠላዬን ላስቀምጥ መጣው ተገኝቶ ነው አልኩ እየሳኩበት" . "እንዳገቢ ባላሽበት ፊትሽን አዙረሽ ነይ ምን ታፍራለሽ እንዴ" አለ ከግቢ ወጥቼ "ሊዊ ካፊ" ጉዞ ቀጠልኩ ሳሚ ከካፊው በረንዳ ላይ ቁጭ ብሏል አጠገብ እደደረስኩ "አንቺ ከየትነው የምትመጭው ከሀገርሽ ነው እዴ ደሞ ሲያምርብሽ ነጠላሽ እማሆይ መስለሽልኛል" አለ እየሳቀ አስተናጋጁን ጠርቱት ልምዴን ስለሚያውቀው ማኪያቱ አዘዘልኝ "ሳሚዬ በቃ አታጠናም አይደል " " በትልቁ እየተነፋሰ እነሱ ላይቡሪራ ናቸው እኔ ደግሞ .....እዚ አላውቅም ምን እንደሆንኩ "ውይ አንተ ማውቅ ካልቻልክ መቼስ ፍቅር ምናምን ያዘኝ እዳትለኝ?እየሳኩበት "የሆንሽ አይጥ ነገር እኔ አሁን ፍቅር ያዘኝ አልኩ" "እውነቴነው እደዚ ስሜትክን ማወቅ እስኪያቅትክ ድረስ ትምህርት አስጠልቶክ ሰው ለፈተና እያጠና አንተ ደግሞ የሊዊ ካፌ ትኩስ ነገሮችን ታጠናለክ" በጣም እየሳቀ "ሂጂ የሆንሽ እቡዱ ነይ ትንሽ ወክ እናዱርገን እንመለሳለን" ብሎኝ ቀዱሞ ተነሳ እጄን ዘርጋ ሰአት ሳይ "አንዱ ሰአት ተኩል ሆኑል ሁሉም ጥዱጥዱ ሆነው ወክ በማዱረግ ላይ ናቸው እኔና ሳሚ በትንሽ ደቂቃ ዝምታ ሰፈነ ሳሚ አዩናቹን ሰረቅ እያደረገ "ሄዋንዬ እስቲ እነዛ ልብ የሚያጥላሉ ልብ ወለዶችሽ አንዱን ንገሪኝ" "እዴ ሠአቱን አይተከዋል ወደ ጊቢ መግባት አለብን ሌላቀን ሰፊ ጊዜ ወስደን" "እሺ አንዱ ሙዚቃ ዝፋኝልኝ "እሱ ያስማማናል ጭር ያለ ቦታ ስንደርስ "ታዲያ ከዳንስሽ ጋር ዳንስ ክበብ ትሰራ አልነበር "መዱረሱ አይቀር ደረስን ሙዚቃ ከፍቼ በማያስደንሰው መደነስ ጀመርኩ። በመሀል ስልኬ ጠራ አሮን ና ናቲ ናቸው አንስቼ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ሳደርግ "የት አባሽ ጠፍተሽ ነው ላያብረራ የለሽም ዶርምም ስንጠያቅ የለችም ውይ አለሁ እንዴ እውነታቸው ነው የለሁም እኮ አላኩ .... "ደግሞ ያአ አዝግ ጉደኛሽ የት እዳለ ታውቂያለሽ " "እእእእ ስሜቱ የተረበሸው ጓደኛችንን ያሄው እኔን እያዛገኝ ነው "የት ናቹ " "ግቢ እዛው የተለመደው " በቃ መጣን" ሳሚ የዛሬው አስተያየቱ ግራ አጋባኝ እዴ ምን አባሆነክ ነው እደዚ የምታየኝ ገራመሽኝ እኔ የተረበሸውን ስሜቴን እንዲታስተውኝ ስፈልግ ጭራሽ በማያስደንሰው ዘፋን በአስቴር ፍቅር ፍቅር ይዞኛል እያልሽ ማባባስሽ.... "ያው ስሜትህ ከዚህ አይዘልም በማለት ነው" እየተጨቃጨቅን እያለ እነ አሮን መጡ. "ሄዋንዬ ይህን ዳንስ ተያይዘሽዋል "ባክ አንዱ ድቡር ስላለ ፍታ እንዲል ነበር" ናቲ "እናንተ ነገ እኳ ፊዚክስ እፈትናለው እንዳለ ታውቃላችሁ" "እንደመደንገጥ ብዬበሉ በሉ ልግባና ትንሽ ላጥና ቻው ብዬ ልለያቸው ስል ከት ብለው ሳቁ" . "ሳቃቸውን ሳይጨርሱ ምን ያስቃል ስል" " "ናቲ አይ ከመቼ ጀምሮ ነው እኛ ዶርም ሳናደርስሽ መሄድ የጀመርሽው ያውም በማታ" በናቲ አነጋገር የደበርው ሳሚ መሳቅ ጀመር." እኔን በመሀል አድርገውኝ ጉዞ ቀጠልን እኛ የባጡን የቆጡን ስናወራ ስሚዬ ግን ዝምታ መርጧል "እጄን በጅ አሾልኬ እንዳይወጣ ጥብቅ አድርጎ ይዞኛል: " ዶርሜ አካባቢ ልንደርስ ስንል ሳሚ ስልክ ላውራ ብሎ ወደኅላ ተመለሰ አሮንና ናቲ ተሰነባብተው መሄድ ጀመሩ። ሳሚ by ሄዋንዬ ብሎ በጅ ምልክት ሰጠኝ"🤚 "ሳሚ እንደዚህ ግን ነገ ያገናኘናል ብዬ ወደ ዶርም ልገባ ስል" "ሄዋን" የሚል ድምጽ ሰማው አቤት ብዬ ዞር ስል ክርስቲ ናት "ክርስቲ ማለት አብራኝ አንድ ዶርም ና እንድ ክፍል ነው የምንማረው "ሄዋንዬ"ፍልጌሽ ነበር አሁን ማውራት እንችላለን። እሺ በሰላም ነው ከበር ላይ ተመልሰን የዶርማችንን መውጫና መውርጃ ደርጃ ላይ ቁጭ አልን. እሺ ክርስቲ ምን አጋጠመሽ "ምን መሰለሽ ሄዋንዬ አንቺ ትርጂኝ አለሽ ብዬ አስባለው" በረጅሙ እንደ መተንፍስ እያለች" . "በመጀመሪያ ጥሩ ጎደኛሞች እንድንሆን እፍልጋለው ቀጥዬ ደሞ ከጎደኛሽ ፍቅር ይዞኛል" " ደነገጥኩ የኔ መደንገጥ ፊቴ ላይ አይታ ምነው ሄዋን ያጠፍሁት ነገር አለ" . ክርስቲዬ እንደውም የሴት ጎደኛ የለኝም አገኘው ግን ከማን ነው ፍቅር የያዘሽ" " ክርስቲ ላይ ዝምታ ሰፈነ እንዴ ምን ነው አሁን እኮ ጎደኛሞች ሆነናል ንገሪኝ." "ታውቂያለሽ ሄዋንዬ ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ካላየሁት መዋል ማደር አልችልም አንዳንዴ ካንቺ ጋር ስትላፉ ሳይ ይቀጥላል..... @achachirlebwelod

አጫጭር ልቡወለድ 🔊: ሁለት ልብ ❤️+❤️=2❤️ ክፍል 1 . . ከልጅነቴ ጀምሮ ቤት ዉስጥ ሰላም ፍቅር እያየሁ ነዉ ያደግኩት። የሆነ ጊዜ ላይ ደስታና ፍቅሩ ጭቅጭቅ ወደ ፀብ ተተካ ! አባቴ መስከር ጀመረ። እናቴ ደግሞ የአባቴ ስካር ስላማረራት ትናገረው ነበር። በርግጥ እናቴ የሱ ነገር ሆኖባት እንጂ ጭቅጭቅ አትውድም በዚ የተነሳ ይደባደባሉ ሳይደበድባት ነግቶ አይመሽም። እኔና እህቴም ድብድቡን ክፍላችን መሽገን በጭላንጭል እየተመለከትን አደግን። ፀባቸዉ ገና ሲጀመር እንባዬ ከአይኖቼ ዱብ ዱብ እያለ ክፍሌ ተደብቄ አያለሁ። ሁሌም ሰላም የለኝም። አንዳንዴ የአባቴ ተግባር እኔን ራሱ በጣም ያበሳጨኝ ነበር። እንግዳ በሚመጣበት ጊዜ አመትባል በሆነበት ውቅት አባቴ ያለው መጠጥ ቤት ነው። እንደዚ ከመሆኑ በፊት የሚያስቀና ቤተሰብ ነበርን አባቴ ለእኛ ያለው ክብር ደስ ስለሚል ጓደኞቼ ይቀኑብኝ ነበር። እድሜዬ እየጨመረ ሲመጣ እና ነገሮችን ላቅ ባለ እይታ ማገናዘብ ስጀምር እናቴ የጭቅጭቁን መናሻ ምን እንደ ነበር? አባቴ ለምን እንደዚ እንደሆነ ጠየኳት የአባቴ ሁኔታ ምን ያህል መጥፎ እንደሆነ ስለተረዳሁት የእናቴ መናደድ ሲያንሳት ነዉ ወደሚል ድምዳሜ ደረስኩ። ምንም አባቴ ቢሆንም በፍፁም ለእኛ አርዐያ መሆን እንደማትችል ተረዳሁ። ።እኔ እና ታናሽ እህቴ ታዲያ እህቴ አባቴን በሚላት ነገር ለእናቴ መጥፎ አስተሳሰብ እንዲኖራት አድርጎል የሚጠጣበት ምክንያት ያልሆነውን እየነገራት ለማሚ ፍቅር እንዳይኖራት ባደረገ ቁጥር እቤት ሰላም እየራቀ መጣ አባቴን ምን ያህል አሳፋሪ ድርጊት እያደረገ "ሴት ውደ አባቷ ሆነ እንዴ ሲለኝ ይቺ አባባል የእናትሽ ቢጤ ነሽ ብትል ይቀልሀል እያልኩ። ምክሬን አልቀበልም በፍፁም አልተቀበለኝም። አባቴ ይህም አልበቃ ብሎት በየመጠጥ ቤቱ ስሟን ማጥፋት ጀመረ። ሚስጥሯን መደበቅ እና የጎደለውን መሙላት ሲገባው ያልሆነችውን የሆነችውን ማውራት ጀመረ ። እቤት ውስጥ መናናቅ ሁሉንም ነገር በየግል ውሳኔ መውሰን ተጀመረ የቤተሰቡ መሰረት ተናጋ!ከምንም በላይ የሚገርመኝ የእናቴ ትግስት ፅና ነው .... ለምን አትፈታውን? እኔ ብሆን እንደሷ ይሄን ያክል ጊዜ የምታገስ አይመስለኝም። . እድሜዬ ከፍ ብሎ የአስራሁለተኛ ክፍል ተማሪ ስሆን ቤት መግባት የሚባል ነገር አስጠላኝ። ጠዋት ከቤት እውጣለው በሰበብ አስባቡ ማታ አምሽቼ እገባለሁ ማታ ወደ ቤት ስመለስ ልክ ወደ ሀዘን ቤት የምገባ ይመስለኛል። ወደ ቤት ላለመመለስ ስል ቀኑን በተቻለኝ መጠን ራሴን በተለያዩ ነገሮች ቢዚ በማድረግ አሳልፋለሁ። ከተውሰና ጊዜ በኃላ ከቤተሰቤ የተነጠኩትን ያጣሁትን ፍቅር ከክበቦች ለማግኛት ወደ አርት ውዳለበት አቀናው ብዙዎቹ ጓደኞቼ ቤታቸዉ ዉስጥ ያላቸዉ ሰላም እና የቤተሰብ ፍቅር ምን ያህል ትልቅ ፀጋ እንደሆነ አይረዱትም። "ከሰፈር ስድብና አሽሙር ችዬ ሁሉንም በፍቅር ሳያቸው " ሲመለከቱ በጥንካሬዬ ይገረማሉ። እኔ ከእዚ የገባሁት ያንን ጭቅጭቅ አለመስማት መሸሸጊያዬ ነው። ቤተሰብ የሁሉም ነገር መሰረት ነዉ። መልካም ባልሆነ ቤተሰብ ዉስጥ ያደገ ልጅ መጥፎ ቢሆን አይገርምም። ጊዜዉ እየገፋ ሲመጣ የምሳተፍባቸው ክበቦች እና የዳንስ ምሽት ለጊዜዉ ከሀዘናን ጭንቀቴን ከማስረሳት በቀር እዚ ሙያ ውስጥ የመቀጠል ሀሳብ እንዳሌለኝ አውቃለው። . እድሜዬ 22 ሲሆን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተመድቤ ፊዚክስ ዲፓርትመንት መማር ጀመርኩ። ሀዋሳ በጣም ዉብ ከተማ ነች። መንገዶቿ በአረንጓዴ ልማት ያጌጡ እና ፅዱ ናቸዉ ። ከፊቼ ጋር ሲነፃፀር የማይገነኝ ነዉ። ሀዋሳ ከዚ በፊት እኔ አባቴ እናቴ እህቴ ሆነን ለጉብኝት መጥቼባት ነበር ግን ታይታ የማትጥገብ ነች። የላንጋኖ ሀይቅ ታይቶ አይጠገብም ... ብቻ ሁሉም ነገሮ ደስ ይላል። በአንድነት የሰፈሩባት ለምለም ምድር ናት። ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ግቢዉም እንደ ከተማዋ አረንጓዴ ነዉ። ዩኒቨርስቲ መግባት ልክ እንደኔ ባልታሰበ ሰዓት ሰላሞን ለተነጠቀ ሰላም ከሌለዉ ቤተሰብ ለመጣ ሰዉ ትልቅ እረፍት ያለዉ ቦታ ነዉ። ትምህርት ተጀምሮ ጥቂት ወራት እንደተማርን ከክፍል ተማሪዎች ጋር መግባባት ጀመርኩ። ውራቶች የፈጀብኝ እኔ ቶሎ ስለማልግባባ ነው። አይን አፋር ቢጢ ነኝ። ሲጀመር ግቢው ውስጥ ያሉ ልጆች ቅልብን ይስባሉ የሴቶች አለባበስ የውንዶች ቁመና እረ ስንቱን.........።..።."" ያንን ቤት ማስታውስ አልችልም ... ሳሚ ፣ ናቲ እና አሮን ጓደኞቼ ሆኑ እኔ ምንም አይን አፋር ነገር ብሆንም ግን ከተግባባን በኃላ ለቀቀኝ። ከእህቴ ልጅ እቤት በተፈጠረው ነገር መልካም ቅርርብ ስላልነበረኝ የወንድምነትን የህትነትን ሁለቱንም ፍቅርን ከነሱ ለማግኘት ብዬ በደንብ ቀረብኳቸዉ። ሳሚ ን ረጋ ብዙም ወሬ የማይውድ ቀይ ድሬ ልጅ ነው። ከአሮን ጋር ያንድ ሀገር ልጆች ነን ከፊቼ ነው የመጣው ። . ናቲ የሀዋሳ ልጅ ነው እድል ሆኖ ባገሩ ደረሰው ...... ቀስ እያልን እየተላመድን መጣን ከመላመድም አልፎ ምግብ አብረን እየተጎራረብን ስንበላ ፍቅራችን ያስቀና ጀመር ። ማናችንም ተነጣጥለን በልተን አናውቅም በፆታ እኔ ብቻ ሴት ነበርኩ። አመሻሽ ላይ ከጓደኞቼ ተለይቼ ውደ ላይብረሪ ለመግባት ስል ማሚ ደውለችልኝ ሰላምታ ከተለዋውጥን በኃላ አባቴ እንዴት ነው ስላት ድምፆ እራቀብኝ ዝምታ ሰፈነ..... . #ይቀጥላል......

(((ካነበብኩት ነገር እስኪ እናንተም ተማሩበት))) አንዲት ወጣት ሴት በአንድ ወቅት አንድ ከባድ ወንጀል ፈጸመች፡፡ ይህም ወንጀል በፍርድ ፊት አቆማት፡፡ ወንጀሉ ሙሉ በሙሉ የእድሜ ልክ እስራት የሚያስፈርድ ነበር፡፡ የፍርድ ሂደቱ በሚከናወንበት ወቅት ፊቷ በእንባ እየታጠበ ለይቅርታ ብትማጸንም ሰሚ ግን አላገኘችም፡፡ ቤተሰቦቿ እና ወዳጅ ጓደኞቿ በእንባ ከመራስ ውጭ ምንም አማራጭ አልነበራቸውም፡፡ ነገር ግን በዚህ አስጨናቂ ወቅት እንድ ሰው ምስክሮች በሚቆሙበት ሳጥን ውስጥ ገብቶ ፍርድ ቤቱን በመማጸን ፍርዱ ከመወሰኑ በፊት ስለዚች ወጣት ሴት ዳኞቹን ይለምንና ይማልድ ጀመር፡፡ ጉዳዩ ከባድ ቢሆንም እርሱ ግን ያለ የሌለ ኃይሉን ተጠቅሞ በዚህች ሴት ምትክ ይሟገት ጀመር፡፡ ከብዙ ውጣውረድ እና ልፋት በኋላ ድካሙ ፍሬ አፍርቶ ልጅቱ በነጻ ተለቀቀች፡፡ ልጅቱም ሰውየው ባደረገላት ነገር ተደንቃ በፊቱ ወደቀች፡፡ ከልቧም አመሰገነችው፡፡ ብዙም ሳይቆይ ይቺው ወጣት በሌላ ተመሳሳይ ወንጀል ውስጥ ተገኘች፡፡ ልክ የፍርድ ቤቱን በር አልፋ አይኖቿን ወደ ዳኞቹ ስታቀና ባለፈው እርሷን ከፍርድ ለማዳን ሲማጸን እና ሲማልድ የነበረው ሰው ዳኛ ሆኖ አገኘችው፡፡ ለካስ ያኔ ጠበቃ ሆኖ ሲሟገትላት የነበረው ሰው አሁን ዳኛ ሆኗል፡፡ ወጣቷ ይህ ሰው ዳኛ ሆኖ ስላገኘችው ደስ አላት፡፡ እንደገና መጣሁ በሚል መንፈስ ይመስላል፡፡ ሰውየው እጆቹን ወደላይ አነሳና ይህውልሽ ትናንት ጠበቃ ነበርኩ ለዚህ ነው አንቺን ለማዳን የተከራከርኩልሽ አሁን ግን ዳኛ ነኝ፡፡ እንደ ዳኛ ደግሞ ትክክለኛውን ፍርድ መፈጸም አለብኝ አላት፡፡ ልጅቱም አይኗ በእንባ እየራሰ ለመሆኑ አንተ ማን ነህ አለችው፡፡ እርሱም፡ የትናንቱ ጠበቃ የአሁኑ ዳኛ ነኝ አላት፡፡ ወዳጄ ዛሬ ኢየሱስ ጠበቃ ነው፡፡ ለጥፋትህ ሁሉ እየማለደ ወደ ሕይወት መንገድ ትገባ ዘንድ ስለአንተ ይማልዳል፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ጠበቃ እንደሆነ አይቀጥልም ዳኛ ሆኖ የሚገለጥበት ወቅት ይመጣል፡፡ ቀኑም ቀርቧል፡፡ አምናለሁ አንተም ተዘጋጅተሃል፡፡👍👍👍