uz
Feedback
Ariz SHOWBIZ

Ariz SHOWBIZ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ

Ko'proq ko'rsatish
1 327
Obunachilar
-124 soatlar
-57 kunlar
-3630 kunlar
Postlar arxiv
‘ሌንጮ ለታ ትግልና ሕይወቱ’ መጽሐፍ ለንባብ በቃ የአንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታን የግማሽ ምዕተ ዓመት የፖለቲካ ተሳትፎና የትግል ታሪክ የሚዘክረው ‘ሌንጮ ለታ፡ ትግልና ሕይወቱ’ በሚል ርዕስ
+7
‘ሌንጮ ለታ ትግልና ሕይወቱ’ መጽሐፍ ለንባብ በቃ የአንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታን የግማሽ ምዕተ ዓመት የፖለቲካ ተሳትፎና የትግል ታሪክ የሚዘክረው ‘ሌንጮ ለታ፡ ትግልና ሕይወቱ’ በሚል ርዕስ የተሰናዳው መጽሐፍ ዛሬ በይፋ ተመርቋል። በደራሲ ዙፋን ኡርጋ በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋዎች የተሰናዳው ይህ መጽሐፍ፤ የአቶ ሌንጮን የሕይወት ውጣ ውረድና ለዘመናት የዘለቀውን የፖለቲካ ተጋድሎ በስፋት ይተነትናል። የምረቃ መርሐ ግብሩ የኦሮሞን ጥንታዊ ባህልና እሴት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፣ በአባ ገዳዎችና በሃደ ሲንቄዎች ባህላዊ ምርቃት በይፋ ተከፍቷል። ከምረቃው በኋላም በአቶ ሌንጮ ለታ ረጅም የትግል ዘመን ላይ ያተኮረና ታዋቂ ግለሰቦች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በዚህ መርሐ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ደራሲያን፣ አርቲስቶች፣ የአቶ ሌንጮ ለታ የትግል አጋሮች፣ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ከአሪዝ ጋር ይዘምኑ!
ለተጨማሪው https://arizmedia.vercel.app/

"በነገራችን ላይ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተመለሰ። በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈውና በደረጀ ኃይሌ የሚዘጋጀው “በነገራችን ላይ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም፣ አዲስ ምዕራፍ ወደ ስርጭት መመለ
"በነገራችን ላይ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተመለሰ። በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈውና በደረጀ ኃይሌ የሚዘጋጀው “በነገራችን ላይ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም፣ አዲስ ምዕራፍ ወደ ስርጭት መመለሱ ተገለፀ። ፕሮግራሙ ወደ አየር ሲመለስ፣ ለአምስት አስርት ዓመታት ያህል በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ የኖሩትንና በርካታ ታሪካዊ ውጣውረዶችን ካሳለፉት ልዑል አስፋወሰን አስራተ ካሳ (ዶ/ር) ጋር እጅግ አስገራሚና ጥልቅ ቆይታ አድርጓል። በዚህ ልዩ መርሃ-ግብር፣ ልዑሉ ስለ ግል ሕይወታቸው፣ ስለ ሀገራዊ ታሪክ እንዲሁም በስደት ስላሳለፉት ረጅም ዘመን ልምዳቸውንና ትውስታቸውን እንደሚያካፍሉ ይጠበቃል። ደረጀ ኃይሌ በበሳልነት ና በጥልቀት በሚያቀርባቸው ጥያቄዎች የሚታወቅ በመሆኑ፣ ይህ ቆይታ ለተመልካቾች አዲስ መረጃና ግንዛቤን እንደሚያስጨብጥ ይታመናል። ይህ በጉጉት የሚጠበቀው ፕሮግራም፣ የፊታችን እሁድ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በአርትስ ቴሌቪዥን እና በጣቢያው ዩቲዩብ ቻናል ላይ በቀጥታ እንደሚተላለፍ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ከአሪዝ ጋር ይዘምኑ!
ለተጨማሪው https://arizmedia.vercel.app/

🌍የቴዲ አፍሮ አዲሱ አልበም "ኢቶሪካ" ለህዝብ ሊቀርብ ነው🌍 በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ደማቅ አሻራ ያሳረፈው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን አዲስ
🌍የቴዲ አፍሮ አዲሱ አልበም "ኢቶሪካ" ለህዝብ ሊቀርብ ነው🌍 በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ደማቅ አሻራ ያሳረፈው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን አዲስ አልበም ሊያበረክት መሆኑ ተሰማ። ዝነኛው ድምፃዊ የአልበሙን ዝግጅት አጠናቆ ለህዝብ ለማቅረብ በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ታውቋል። "ኢቶሪካ" – አዲሱ የጥበብ ስራ "ኢቶሪካ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ አልበም፣ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ስራዎቹ በላቀ ሁኔታ ረቂቅ የሆኑ ግጥሞችና ጥልቅ ዜማዎች የተካተቱበት እንደሆነ ተገልጿል። አልበሙ በተለይ በዘንድሮው የዳግማ ትንሳኤ በዓል ለሙዚቃ አፍቃሪዎች እንደሚደርስ ይጠበቃል። የቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ጉዞ በአጭሩ ቴዲ አፍሮ ከዚህ ቀደም ባወጣቸው ስራዎቹ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ይታወሳል። ከእነዚህም መካከል፦ ያስተሰርያል አቦጊዳ ጥቁር ሰው ኢትዮጵያ ይህ አዲስ ስራ ለረጅም ጊዜ በጉጉት ለጠበቁት አድናቂዎቹ ትልቅ የበዓል ስጦታ እንደሚሆን ተገምቷል። ከአሪዝ ጋር ይዘምኑ! ለተጨማሪው https://arizmedia.vercel.app/

🌍“ሄር ስቶሪ” የሥዕል አውደርዕይ ተከፈተ 🌍 “ሄር ስቶሪ” የተሰኘ የጋራ የሥነ-ጥበብ ዐውደርዕይ ባሳለፍነው ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ዘ ስፔስ ኢትዮጵያ” ጋለሪ ውስጥ ለተመልካቾች ክ
🌍“ሄር ስቶሪ” የሥዕል አውደርዕይ ተከፈተ 🌍 “ሄር ስቶሪ” የተሰኘ የጋራ የሥነ-ጥበብ ዐውደርዕይ ባሳለፍነው ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ዘ ስፔስ ኢትዮጵያ” ጋለሪ ውስጥ áˆˆá‰°áˆ˜áˆáŠŤá‰žá‰˝ ክፍት ሆኗል። እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስም ይቆያል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ዐውደርዕይ ላይ፤ አሌክሳንድራ ምትኩ፣ ብሌን ደረሰ፣ ፍቅርተ አያና፣ ምሕረት እሸቱ፣ ኒና ኡርጌሳ፣ ራፋኤላ ፍቃዱ፣ ሩት አስክንድር እና ሩት ጌታቸው የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ለታዳሚ አቅረበዋል። ይህ ዐውደርዕይ ለቀድሞዋ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ መታሰቢያነት የተበረከተ መሆኑ ተነግሯል።
Via :- Event Addis
Ariz Media.TG ከአሪዝ ጋር ይዘምኑ
https://t.me/ArizTellegram

🌍ድምፃዊ ቬሮኒካ አዳነ በሩዋንዳ ሁለት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አሸነፈች!🌍 አሪዝ|ተወዳጇ ድምፃዊ ቬሮኒካ አዳነ በጎረቤት ሀገር ሩዋንዳ በተካሄደ የሽልማት መርሃ-ግብር ላይ የሁለት ዘርፎች
🌍ድምፃዊ ቬሮኒካ አዳነ በሩዋንዳ ሁለት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አሸነፈች!🌍 አሪዝ|ተወዳጇ ድምፃዊ ቬሮኒካ አዳነ በጎረቤት ሀገር ሩዋንዳ በተካሄደ የሽልማት መርሃ-ግብር ላይ የሁለት ዘርፎች አሸናፊ በመሆን የሀገራችንን ስም በድጋሚ አስጠርታለች። ቬሮኒካ ሽልማቱን በአካል ተገኝታ ለመቀበል የጉዞ ትኬት ቆርጣ የነበረ ቢሆንም፣ ባልታሰበ ምክንያት መገኘት እንዳልቻለች ገልጻለች። ይሁን እንጂ ሽልማቶቹ በሁለት ቀናት ውስጥ እጇ እንደሚገቡና ለደጋፊዎቿ ልዩ የምስጋና ቪዲዮ ይዛ እንደምትመጣ ቃል ገብታለች።
Ariz Media.TG ከአሪዝ ጋር ይዘምኑ
https://t.me/AriffTellegram

እንኳን ለ120ኛው የአድዋ በዐል በሠላም አደረሠን! በዐሉ የሐገር ፍቅር እና እውቀት ሚሠፍንበት ይሆን ዘንድ አሪፍ ሚድያ ይመኛል ። Ariff Media.TG ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ https://t.me/
እንኳን ለ120ኛው የአድዋ በዐል በሠላም አደረሠን! በዐሉ የሐገር ፍቅር እና እውቀት ሚሠፍንበት ይሆን ዘንድ አሪፍ ሚድያ ይመኛል ።
Ariff Media.TG ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ
https://t.me/AriffTellegram

🌍የኢትዮጵያ ፓርላማ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር እስረኞችን እንድትቀያየር የሚፈቅድ አዋጅ ፀደቀ🌍 የኢትዮጵያ ፓርላማ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር እስረኞችን እንድትቀያየር የሚፈቅድ አዋጅ ማጽደቁን ኢትዮጵያን
🌍የኢትዮጵያ ፓርላማ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር እስረኞችን እንድትቀያየር የሚፈቅድ አዋጅ ፀደቀ🌍 የኢትዮጵያ ፓርላማ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር እስረኞችን እንድትቀያየር የሚፈቅድ አዋጅ ማጽደቁን ኢትዮጵያን ኢንሳይደር ዛሬ የፀደቀ ሲሆን በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ቻይናውያን ፍርዳቸውን በሀገራቸው እንዲጨርሱ በተመሳሳይም በቻይና የታሰሩ ኢትዮጵያውያን ፍርዳቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲጨርሱ እድል የሚሰጥ ነው፡፡ይህ አዲስ አዋጅ አደንዛዥ እጽ ይዛ ተገኝታለች ተብላ በቻይና ላለፉት አመታት የታሰረችው ናዝራዊት ወደ ሀገሯ እንድትመለስ እድል ይፈጥራልም ተብሏል፡፡
Via: Ethiopian Insider
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ  መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍የቀጥታ ስርጭት ዘገባውን በወፍ ታጅቦ ያከናወነው የፋና ሪፖርተር🌍 የፋና ቴሌቪዥን ሪፖርተር ምራዑል ከድር የቀጥታ ስርጭት ዘገባ በማቅረብ ላይ እያለ፣ አንዲት ወፍ ትከሻው ላይ አርፋ ዘገባውን አብራው ማጠናቀቋን ኖር ሬድዮ ዘግቧል። ሪፖርተሩ ለተመልካቾች መረጃ ለማድረስ ሙሉ ትኩረቱን ካሜራው ላይ አድርጎ ባለበት ቅጽበት፣ ወፏ ትከሻው ላይ አርፋ ለደቂቃዎች ቆይታለች። ምራዑል ይህንን ልዩ አጋጣሚ ሲገልጽ "ቀጥታ ዘገባዬ አልተቋረጠም፣ ድምፄም አላስደነገጣትም፤ አእምሮዬ ከወፏ ጋር እያወራ አንደበቴ ግን መረጃ ማድረሱን ቀጥሏል" ብሏል። "ሰው ጋር መግባባት በከበደበት በዚህ ጊዜ ከወፍ ጋር ተግባብቼ የቀጥታ ዘገባዬን ጨረስኩ" በማለትም በሙያው ያጋጠመውን ይህን ብርቅዬ ክስተት በደስታ ገልጾታል።
Via: Nor- Radio
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍ታዋቂዋ የውበት ባለሙያ ትርሀስ (ቴሪ) አረፈች🌍 በኢትዮጵያ የውበትና የፀጉር ስታይል ዘርፍ ስሟ በጉልህ የሚነሳውና በቅርብ ወዳጆቿ "ቴሪ" በሚል ቅጽል ስም የምትታወቀው የውበት ባለሙያ ትርሀስ
🌍ታዋቂዋ የውበት ባለሙያ ትርሀስ (ቴሪ) አረፈች🌍 በኢትዮጵያ የውበትና የፀጉር ስታይል ዘርፍ ስሟ በጉልህ የሚነሳውና በቅርብ ወዳጆቿ "ቴሪ" በሚል ቅጽል ስም የምትታወቀው የውበት ባለሙያ ትርሀስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተሰማ። ባለሙያዋ በአዲስ አበባ ደንበል ሲቲ ሴንተር "ሞሮኮ ባዝ" (Morocco Bath) የተሰኘውን ዘመናዊ የውበት መጠበቂያ ማዕከል በመክፈትና ዘመናዊ የፀጉር አሰራርና የሜካፕ ጥበብን በማስተዋወቅ ረገድ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት ባለሙያዎች መካከል አንዷ ነበረች።
Via : Event - Addis

🌍የኢትዮጵያ ሰርክስ ቡድን በፈረንሳይ ድል ቀናው🌍 በየኔነህ ተስፋዬ ማናጀርነት እና በአሰልጣኝ ክብሮም ወልደሳሙኤል የሚመራው "ትሩፕ ኮልፌ" (የቢጣ ሰርከስ ቡድን) በፈረንሳይ በተካሄደው 48ኛው
🌍የኢትዮጵያ ሰርክስ ቡድን በፈረንሳይ ድል ቀናው🌍 በየኔነህ ተስፋዬ ማናጀርነት እና በአሰልጣኝ ክብሮም ወልደሳሙኤል የሚመራው "ትሩፕ ኮልፌ" (የቢጣ ሰርከስ ቡድን) በፈረንሳይ በተካሄደው 48ኛው የሞንቴ ካርሎ ዓለም አቀፍ የሰርከስ ፌስቲቫል ላይ በመሳተፍ የብር ሜዳሊያ አሸናፊ እንደሆነ ኖር ሬድዮ ዘግቧል። የዓለማችን ታዋቂ የሰርከስ አርቲስቶች የሚሳተፉበት ተብሎ በሚታወቀው በዚህ ክብረ በዓል ላይ ቡድኑ ያስመዘገበው ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ትልቅ ኩራት ሆኗል።በዚህ ፌስቲቫል ላይ ትሩፕ ኮልፌ ያገኘው የብር ሜዳሊያ፣ የኢትዮጵያን የሰርከስ ጥበብ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ያደረገ ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
Via: EVENT - ADDIS
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ማስታወቂያ አውጥቷል 🌍 ሚዲያው ሪፖርተር ይፈልጋል! ​የኢትዮጵያ ኢንሳይደር አሳታሚ የሆነው ሀቅ ሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን፤ በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ መ
🌍ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ማስታወቂያ አውጥቷል 🌍 ሚዲያው ሪፖርተር ይፈልጋል! ​የኢትዮጵያ ኢንሳይደር አሳታሚ የሆነው ሀቅ ሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን፤ በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። በዚህም ተፈላጊ የሥራ መስኮች ፦ ​1. ሪፖርተር (አዲስ አበባ) - በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ላት። - ​አማርኛ እና ኦሮምኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፎ መናገር የሚችል/የምትችል። ​2. ሪፖርተር (ባህር ዳር) ​- በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ላት። - ​ባህር ዳር ከተማ የሚኖር/የምትኖር። ​3. ሪፖርተር (ድሬዳዋ ወይም ሀረር) ​- በጋዜጠኝነት ወይም በተመሳሳይ የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪ እና 1 ዓመት የስራ ያለው/ላት። - ​ከአማርኛ በተጨማሪ ሌሎች የአካባቢው ቋንቋዎችን መናገር መቻል ተመራጭነት አለው። ​4. ኦዲዮ ቪዥዋል ኤዲተር ​ በኢንፎግራፊክስ እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ስልጠና የወሰደ/ች እና ቢያንስ የ1 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት። በምርጫ ዘገባዎች ላይ ቀደምት ልምድ ያላቸው አመልካቾች በከፍተኛ ሁኔታ ይበረታታሉ። ​አመልካቾች የትምህርት እና የስራ ልምድ ማስረጃችሁን (CV) በ recruitment@ethiopiainsider.com ኢሜይል አድራሻ መላክ ይጠበቅባችኋል።
Via : Event - Addis

🌍ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተሸጠ🌍 ከአዲስአበባ ቀደምት ዘመናዊ ሆቴሎች መካከል አንዱ የሆነው ዋቢ ሸበሌ በዛሬው ዕለት ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ተሽጧል። ስምምነቱን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና
🌍ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተሸጠ🌍 ከአዲስአበባ ቀደምት ዘመናዊ ሆቴሎች መካከል አንዱ የሆነው ዋቢ ሸበሌ በዛሬው ዕለት ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ተሽጧል። ስምምነቱን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሾል አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድና የዋቢ ሸበሌ ሆቴል አክሲዮን ማህበር የቦርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን ተፈራርመዋል። አቶ ጀማል አሕመድ የሆቴሉን አገልግሎት በዘርፉ አለም በደረሰበት ደረጃ በማዘመን ለእንግዶች ምቹና ጥራቱን የጠበቀ የማረፊያ ቦታ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። የዋቤ ሸበሌ ሆቴል የቦርድ ፀሀፊ ልዑል በዕደማርያም መኮንን የሆቴሉን ታሪክ ጠብቆ በማዘመን ለትዉልድ ለማሻገር በመስማማቱ ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ኢትዮጵያ  32ኛውን  የዓለም  የአየር ንብረት  ለውጥ ጉባኤ ለማዘጋጀት መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ  ለተሳታፊዎች  ከሚሰራቸው ሆቴሎች አንዱ ሲሆን ዘመናዊና ቅንጡ በሆነ መልኩ የማሪዮት ደረጃን (autograph collection by Marriot ) ጠብቆ የሚታደስ መሆኑን ሚድሮክ ኢትዮጵያ አስታውቋል ። ዋቢ ሸበሌ ሆቴል በ1960 ዓም ሾል መጀመሩ ይታወሳል። ሆቴሉ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ህይወታቸው ላለፈው የልዑል መኮንን ልጆች የገቢምንጭ እንዲሆን ንጉስ ሃይለስላሴ ማስገንባታቸው ይነገራል ። ሆቴሉን ደርግ ከወረሰው በኋላ በዘመነ ኢህአዴግ ለእነ ልዑል በዕደማርያም መኮንን መመለሹ ይታወሳል ።
Via: ሁሉ አዲስ
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍የደራሲ እና ጋዜጠኛ መርዕድ እስጢፋኖስ ሁለት የልቦለድ መፅሀፍት ለአንባብያን በቁ!🌍 በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና የሎዛ ድርሳናት(2017 ዓ.ም) ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍ ኤጄንሲ(ወመዘክር) ተመርቋል። የመጻሕፍቱ ይዘት በኢትዮጵያ ሚሊኒዬም ዋዜማ ከአፍሪካ እስከ አውሮፓ የሚዘልቅ ሲሆን በገጸ ባህሪያቱ ሙግት በፍቅር፣ በባህልን እና ስነ ልቦናዊ ጉዳዮች ላይ ይፈላሰፋል ፣የስደት ገጠመኞችን ያስቃኛል እንዲሁም በቀልብ አንጠልጣይ ትረካ የገጸ ባህሪያቱን መጨረሻ ለማወቅ የሚያጓጓ መፅሀፍ መሆኑ ተገልጿል። የሎዛ ዘፀአት መፅሐፍ የገፅ ብዛት 557 እና የሎዛ ድርሳናት በ517 ገፆች የተቀነበቡ ናቸዉ። በመፅሀፍ ምርቃቱ የመጽሐፍ ዳሰሳ በጋዜጠኛና ደራሲ ታምሩ ከፈለኝ ቀርቧል። በዚህ መፅሀፍ ምርቃት ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ ደራሲት የዝና ወርቁ እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በመፅሀፉ ዙሪያ ያላቸዉን አስተያየት ሰተዋል። ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና የሎዛ ድርሳናት(2017 ዓ.ም.) መፅሐፍቶች ሲመረቁ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች ፣ ታዋቂ የኪነ-ጥበብ ሰዎች ፣ የጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ ቤተሰቦች አብሮ አደጎች አድናቂዎች ፣ወዳጆች ጥሪ የተደረገላቸው ታዳሚያን ተገኝተዋል፡፡
Via: Fast Mereja
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍በመጨረሻም ነፃነት ወርቅነህ ተቀበረ 🌍 የአርቲስት ነፃነት ወርቅነት የቀብር ስነስርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል። በድንገት ላጣነው አርቲስት ነፃነት ወርቅነት ሽኝት ከለ
🌍በመጨረሻም ነፃነት ወርቅነህ ተቀበረ 🌍 የአርቲስት ነፃነት ወርቅነት የቀብር ስነስርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል። በድንገት ላጣነው አርቲስት ነፃነት ወርቅነት ሽኝት ከለቀስተኞች ከ2000 በላይ የአበባ ጉንጉን መቅረቡን የኢቢኤሱ ተወዳጁ ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደ ተናግረዋል።

🌍የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ሽኝት 🌍 የተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የአስክሬን ሽኝት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ይገኛል። ስነስርዓቱ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በቀጥታ እ
+7
🌍የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ሽኝት 🌍 የተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የአስክሬን ሽኝት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ይገኛል። ስነስርዓቱ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በቀጥታ እየተሰራጨ ይገኛል።

🌍የጆኒ ራጋ ጀማው ኮንሰርት ተሰርዟል 🌍 የድምጻዊ ጆኒ ራጋ "ጀማው" ኮንሰርት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት እንደተሰርዘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያ
🌍የጆኒ ራጋ ጀማው ኮንሰርት ተሰርዟል  🌍 የድምጻዊ ጆኒ ራጋ "ጀማው" ኮንሰርት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት እንደተሰርዘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።የተሰረዘው ኮንሰርትም የፊታችን አርብ ጥር 15 2018 á‹“.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል። ጆኒ ራጋ ስለጉዳዩ ተከታዩን ብሏል"እስካሁን ትኬት ቆርጣችሁ በመጠበቅ ላይ ያላችሁትን ሁሉ በታላቅ ትህትና ይቅርታ እየጠየቅን በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ጀማው ኮንሰርትን ለመጪው አርብ ጥር 15 ማዘውራችንን ለሁሉም ጀማ እንድታደርሱልን በአክብሮት እንጠይቃለን"
Via : Event Addis
ስለምርጫዎ እናመሠግናለን!!  ለአዳዲስ ኤቨንት እና ሾውቢዝ መረጃዎች   https://t.me/AriffTellegram ን ተመራጭ ያድርጉ ከአሪፍ ጋር ይዘምኑ!

🌍አርቲስት ገነት ንጋቱ በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ዙሪያ ያሰራጨችውን ቪዲዮ አነሳች፤ የ"Unsubscribe" ዘመቻም ገጥሟታል🌍 አርቲስት ገነት ንጋቱ የሙያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነፃነ
🌍አርቲስት ገነት ንጋቱ በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ዙሪያ ያሰራጨችውን ቪዲዮ አነሳች፤ የ"Unsubscribe" ዘመቻም ገጥሟታል🌍 አርቲስት ገነት ንጋቱ የሙያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ላይ አሰራጭታው የነበረውን ቪዲዮ ከገጿ ላይ ማንሳቷ ታወቀ። አርቲስቷ ቪዲዮውን ለማንሳት የተገደደችው፣ ቪዲዮው የሟቹን ክብር የማይመጥንና ቤተሰቦቹን የሚጎዳ ነው በሚል ከህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ ከበረታባት በኋላ መሆኑ ተገልጿል። በተለይም በሀዘን ወቅት እንዲህ ያሉ መረጃዎችን ለዕይታ ማግኛ (Views) መጠቀም ተገቢ አይደለም በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰፊ ቁጣ ተቀስቅሷል። ከቪዲዮው መነሳት ባሻገር፣ ድርጊቱ ያስቆጣቸው በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በአርቲስት ገነት ንጋቱ የዩቲዩብ ቻናል ላይ "Unsubscribe" የማድረግ ዘመቻ መጀመራቸው ታይቷል።
Via: Event Addis

🌍 ነጻነት ወርቅነህ ዛሬ ጠዋት 🌍 ነጻነት ዛሬ ጠዋት ወደ ስራ ሊሄድ እየለባበሰ ነበረ። ህመም ሲሰማው ጓደኛውን ጠርቶት ወደ ICMC ሆስፒታል ሄዱ። መንገድ ላይ እያለም ህመሙ እየባሰበት ነበረ።
🌍 ነጻነት ወርቅነህ ዛሬ ጠዋት 🌍 ነጻነት ዛሬ ጠዋት ወደ ስራ ሊሄድ እየለባበሰ ነበረ። ህመም ሲሰማው ጓደኛውን ጠርቶት ወደ ICMC ሆስፒታል ሄዱ። መንገድ ላይ እያለም ህመሙ እየባሰበት ነበረ። ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ምሳ ሰዓት ገደማ አረፈ። ፖሊሶች በሆስፒታሉ ተገኝተው ሙያዊ የምርመራ ስራቸውን አከናውነዋል። አሌልቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅበሩኝ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በሕይወት እያለ ሲሞት አሌልቱ ጊዮርጊስ ከአያቱ አጠገብ ቀብሩ እንዲፈጸም እንደሚፈልግ ለወዳጆቹ ደጋግሞ ይናገር የነበረ ሲሆን ያለፈው ሳምንትም አሌልቱ ጊዮርጊስ በመሄድ ቤተክርስቲያኒቱን የማሳደስ ስራ ስለማከናወን ከሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቱ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሮ መመለሱ ተሰምቷል። ኑሮዋን በአሜሪካ ያደረገችው ባለቤቱ እና የልጆቹ እናት እሁድ ጠዋት ከአሜሪካ አዲስ አበባ የምትገባ ሲሆን በዚያው ሰዓት ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
Via: ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ፤ በግል የሕይወት ታሪካቸው እና በሀገሪቱ የፖለቲካ ሂደት ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ የሚያወሳ አዲስ መጽሐፍ ለህትመት ማብቃታ
የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ፤ በግል የሕይወት ታሪካቸው እና በሀገሪቱ የፖለቲካ ሂደት ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ የሚያወሳ አዲስ መጽሐፍ ለህትመት ማብቃታቸው ተሰማ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለጹት፣ የመጽሐፉ የአርትኦት ሥራዎች ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው ለአካላዊ ህትመት ወደ ማተሚያ ቤት ገብቷል። መጽሐፉ በቅርብ ቀናት ውስጥ ለአንባቢዎች ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ መጽሐፍ የወይዘሪት ብርቱካንን የሕይወት ውጣ ውረድ እና የፖለቲካ ተሳትፎ የሚዳስስ እንደሆነ ተጠቁሟል። ወይዘሪት ብርቱካን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የፍትህ ሥርዓት ውስጥ ጎልተው የወጡት በ1993 ዓ.ም. ነበር። በወቅቱ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆነው ሲያገለግሉ፣ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉትን የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃን በዋስ እንዲለቀቁ በመወሰን፣ለዳኝነት ነጻነት ያሳዩት አቋም በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አትርፎላቸው ነበር። ከዳኝነት ሙያቸው በኋላ ወደ ፖለቲካው በመግባት፣ በምርጫ 97 ወቅት የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ቅንጅት) ከፍተኛ አመራር በመሆን አገልግለዋል።ከምርጫው ጋር በተያያዘም በቃሊቲ እስር ቤት ታስረው የነበረ ሲሆን፣ ከእስር ከተፈቱ በኋላ በስደት ቆይተዋል። ከ2010 ዓ.ም. የፖለቲካ ለውጥ በኋላ ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ሀገራዊ የምርጫ ተቋሙን የመምራት ኃላፊነት ወስደው ሰርተዋል። አዲሱ መጽሐፍ በእነዚህ ኩነቶች እና በሌሎች የግል ታሪካቸው ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ያላቸውን ተሞክሮ ያካፍሉበታል ተብሎ ይጠበቃል። https://t.me/AriffTellegram

🌍ያልተኖረ አዲስ ፊልም 🌍 ታህሳስ 13 ሰኞ በታላቁ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ከ ቀኑ 11:30 ጀምሮ በቀይ ምንጣፍ ስነ-ስርዓት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ሚዲያዎች እና የኪነ - ጥበብ ባለሙያዎ
🌍ያልተኖረ  አዲስ ፊልም  đŸŒ ታህሳስ 13 ሰኞ በታላቁ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ከ ቀኑ 11:30 ጀምሮ በቀይ ምንጣፍ ስነ-ስርዓት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ሚዲያዎች እና የኪነ - ጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይመረቃል። ታህሳስ 17፣18፣19 ደግሞ በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች በታላቅ ድምቀት ይመረቃል። ፊልሙን ያቀረበው ናዲ መልቲ ሚዲያ በቅርቡ ሌሎችም ትላልቅ ፊልሞችን እንደሚያቀርብ ገልፅዋል ። https://t.me/AriffTellegram