cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

#መንሀጁ ሰለፍ

"አላህ መልካም የሻለትን ሠዉ ዲኑን ያስገነዝበዋል" ረሡል (ሰለላሁ አለይሂ ወሠለም) #selefoch

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
203
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ጥያቄ እና መልስ
ቁርዓን በውብ ድምፆች
ሰሂህ ሃዲስ
ግጥሞች
አጫጭር ሙሃደራ
ኢስላማዊ ፅሁፎች
ወቅታዊ መረጃ
አጫጭር ማስታወሻዋች
ከኡለማዋች አንደበት
የሰለፎችን ንግግር 👌👌
ሁሉንም በአንድ ለማግኘት
Join
ስለዚህ በእንዲህ አይነት ከባድ ጉዳይ ላይ የታማኝ ዑለማዎችን ‘ተውጂሃት’ ከመከተል ባለፈ በግል ሃሳብ አጉል መኮፈስ፣ አለፍ ሲልም የቢድዐ አንጃዎችን አቋም ማራመድ፣ ከዚህም አልፎ የሱና ዑለማዎችን በነገር መውጋት የለየለት ብልግና ነው። ስሜት ልቡን ያወረው፣ አእምሮውን ያሰከረው፣ ብልሹ አካሄዱን እንደ ንቃት የሚቆጥር ‘ሩወይቢዻ’ (رويبضة) ካልሆነ በስተቀር እዚህ ሰፈር ሚንሀጁን የሚያከብር፣ ቀድሩን የሚያውቅ ሰለፊ አይልከሰከስም።
Hammasini ko'rsatish...
አንድ እርምት ለአንድ ማምታቻ ~~~~~~~~~~~ አንድ እዚህ ላይ ስሙን ልጠቅሰው የማልፈልገው ሰው ትላንት በፃፍኩት ላይ ተቃውሞ እንደፃፈ በተሰጠኝ ኮሜንት ላይ አየሁኝ። ሃሳቡን የሚጋሩ ሊኖሩ ሰለሚችሉ በዝምታ ማለፍ አልፈለግኩም። ተቃውሞው ያለበት የፅሁፉ ክፍል ይሄውና:– “በአፍጋኒስታን ጂሃድ የነበረ ጊዜ በአለማችን የካፊሮችና የሙሥሊሞች ጦር አሠላለፍ የማን ይበልጥ ነበር? ያለምንም ጥርጥር ዛሬ ኑኩውሌር ያላቸው ሐገራት ያኔም የታጠቁ ነበር። ያኔም በጦር መሣርያ ኩፋሮቹ ይበልጡ ነበር። … በዚያ ወቅት የነበረው ጂሃድ በጦር መሣርያ ከሃዲያኑ ይበልጥ የታጠቁበት ከነበረና ረቢዕም በዚህ ሸርጡ ባላሟላ ጂሃድ ተሳትፎ ከነበር በምን መነፅር ነው? ለረቢዕ ጊዜ ፅድቅ ለሌሎች ዓሊሞች ጊዜ ‘ኸዋሪጅነት’ የሚሆነው? ምክንያቱም ያኔም አሁንም ሙሥሊሞች በኃይል ከከሃዲያኑ ያነሱ ናቸውና። መልሥ ያለው ያሥረዳኝ።” የኔ መልስ ቀጥሎ ያለው ነው:– ~~~~~~~~~~~ በቅድሚያ ይሄ ሃሳብ ሊነሳ እንደሚችል ቀድሜም አስቤ ነበር። የፅሁፌ መርዘም ነው ያስቆመኝ። እየጠቀሰ ያለው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1979 ጀምሮ ከአስር አመታት በላይ ሲካሄድ የቆየውን የአፍጋኒስታን ጦርነት ነው። እንግዲህ ከልጁ ፅሁፍ ጭብጥ እንደምትረዱት ጦርነቱ በአንድ በኩል ሙስሊሞች፤ በሌላ በኩል ደግሞ ኒኩሌር የታጠቁት ካፊሮች ሆነው ለሁለት ጎራ ተሰልፈው እንደተዋጉ አስመስሎ ነው እያቀረበ ያለው። እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም። “ኒኩሌር የታጠቀውን ፀረ ኢስላም ህብረት በዚያ መጠን ያልሆኑት ሙስሊሞች አሸንፈውታል። ስለዚህ በወንጭፍ እና ትከሻ ላይ ተደርጋ በምትተኮስ ሮኬት ብንዋጋ ምንድነው ችግሩ?” ማለቱ ነው። ለዚህ ልጅ የምሰጠው ምላሽ 1ኛ:– “ተዋጉ” አልኩኝኮ! ዑለማዎች ላይ መዝመቱን ትታችሁ ሂዱና ቁድስን ነፃ አውጡ። የፌስቡክ ነብር አትሁኑ። የእናንተ ጂሃድ ሰለባ'ኮ ከ80% በላይ ሙሰሊሙ ነው። ያውም ኢስላምን ማጠልሸታችሁ፣ ለጠላት መጠቀሚያ መሆናችሁ፣ ዑለማዎችን በማንቋሸሽ ወጣቱ ከዲኑ እንዲርቅ ማድረጋችሁ ሳይታሰብ። 2ኛ:– ተቃውሞ ከመፃፍህ በፊት በመጀመሪያ ስለምታወራው ጉዳይ ዝርዝሩ ቢቀር ቢያንስ መሰረታዊ ጭብጥ ይኑርህ። ይህን የምለው የፃፍከው ነገር በጊዜው የነበረውን አሰላለፍ እንደማታውቀው በሚገባ ስለሚያሳይ ነው። 3ኛ:– “ለረቢዕ ጊዜ ፅድቅ ለሌሎች ዓሊሞች ጊዜ ‘ኸዋሪጅነት’ የሚሆነው?” ብለህ መጠየቅህ ማምታታት ነው። እኔ በእንዲህ አይነት አቅምን ባላገናዘበ ጦርነት ስለገቡ ብቻ ሰዎችን በኸዋሪጅነት አልወነጀልኩም። ግን “ምን ያለበት ዝላይ አይችልም” ነው ነገሩ። ሃሳቤ በእንዲህ አይነት ጦርነት ውስጥ መግባትን ስለነቀፉ ዓሊሞችን በፈሪነት መወንጀል፣ ለጠላት ቅጥረኛ አድርጎ መሳልና በኢርጃእ መወንጀል፣ “የአንባገነን ቅጥረኛ” እያሉ ማጠልሸት፣ አልፎም በግልፅ በክህደት መወረፍ፣… በተደጋጋሚ እያየን ነው። “ኸዋሪጅ” ያልኩት በዚህ ቆሻሻ ባህር ውስጥ የሚንቦጫረቁ ሰዎችን ነው። ፀሃፊው ከዚህ ውስጥ የተወሰነው ድርሻ እንዳለው አውቃለሁ። 4ኛ:– የአፍጋኒስታኑን ጦርነት በተመለከተ ጦርነቱ በአሜሪካና በሶቭየት ህብረት መካከል የነበረው የቀዝቃዛው ጦርነት አካል ነበር። ብዙ ነገሩ የውክልና ጦርነት (proxy war) የሚገልፁ ፀሃፍት አሉ። በዚህ ጦርነት ከሶቭየት በተቃራኒ የተሰለፉት እሱ አስመስሎ እንዳቀረበው ሙስሊም ሃገራት ብቻ አልነበሩም። ይልቁንም በትጥቅም፣ በስልጠናም ከፍተኛ የሆነ የአሜሪካ፣ የእንግሊዝና የቻይና ድጋፍ ነበር። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሶቭየትን ጣልቃ ገብነት አውግዞ ውሳኔ አሳልፏል። ምእራቡ አለም ተደራራቢ ማእቀቦችን በሶቭየት ላይ ጥሎ አዳክሟታል። በሂደትም ሶቭየት ከአፍጋኒስታን ጠቅልላ ልትወጣ ተገዳለች። ነገሩ በዚህም ሳይቆም ሶቭየት ህብረት ፈራርሳ 15 እራሳቸውን የቻሉ ነፃ ሃገራት ተመስርተዋል። ስለዚህ ጦርነቱ የነበረው:– ① – በአንድ በኩል ያሉት ሶቭየት እና በሶቭየት የተጎለቱት የምስራቅ ጀርመንና የአፍጋኒስታን መንግስቶች ብቻ ናቸው። ሌላ ከተጠቀሰ የህንድ ሰብአዊ ድጋፍ ነው። ② – በሌላኛው ጎራ ያለው የአፍጋኑ ሶሻሊስት መንግስት ተቀናቃኝ የሆኑ በርካታ ተዋጊ ቡድኖች፣ የዐረብ ሙጃሂዶች፣ እነዚህን ቡድኖች ሲያግዙ የነበሩ የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ የፓኪስታን፣ የሳዑዲ፣ የግብፅ፣ የቻይና፣ የምእራብ ጀርመን መንግስታት፣ በኢራን የሚደገፉ ተዋጊዎች፣… ነበሩ። ይሄ ሁለተኛው ቡድን አለማቀፍ ተቋማትን ተጠቅሞ በቀላሉ ነበር ፀረ ሶቭየት ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ የነበረው። ይህም አሰላለፉ ፀሀፊው ከገመተው ፈፅሞ የተለየ ነበር። እንደ ምሳሌ ለመጥቀስ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ 104 ለ 18 በሆነ የድምፅ ልዩነት ነበር ሶቭየትን አውግዞ ውሳኔ ያሳለፈው። እንዲህ አይነቱን ጦርነት ሙስሊሞች በአንድ በኩል፣ ኒኩሌር የታጠቁ ሙስሊም ያልሆኑ መንግስታት ደግሞ በሌላ በኩል እንደተዋጉ አስመስሎ ማቅረብ ማምታታት ይሰኛል። ሙስሊም ተዋጊዎች፣ ዑለማዎች በጊዜው ያደረጉት አጋጣሚውን መጠቀም ነው። ፀረ ኢስላሙን የአፍጋን ሶሻሊት መንግስትና ግብረ አበሩ ሶቭየትን ከምእራቡ አለም ጋር ሆነው ተዋጉ። አለቀ። ይሄ ሌላ ጊዜም ሊደረግ ይችላል። ምእራቡ አለም በተለያዩ መነሻዎች ከሙስሊሞች ሆኖ ሙስሊም ያልሆኑ አካላትን ጭምር ሊዋጋ ይችላል። ልክ በ1999 አሜሪካ መራሹ ኔቶ የፀጥታው ምክር ቤትን ይሁንታ እንኳ ሳያገኝ ለሙስሊሟ ኮሶቮ ወግኖ ዩጎዝላቪያን እንዳትበላ እንዳትዘራ አድርጎ እንደቀጠቀጣት። እውነት ለመናገር በእንዲህ አይነት ርእስ ላይ መፃፍ ብዙም አያስደስተኝም። ነገር ግን የኢኽዋን ‘አካደሚሻን’ እና ከእናት ቡድኑ የተስፈነጠሩ አንጃዎች ሁሌ ከሚዘምሩለት “ፊቅሁል ዋቂዕ” የተኳረፈ ግልብ ትንታኔ እየሰጡ በዑለማዎቻችን ላይ ሲዘምቱ ማየት እጅጉን ያማል። ለዚህ ድፍረት የሚያበቃቸው ለዑለማዎች ያላቸው ንቀት ነው። እንጂ ይሄ ዘርፍ በ‘አካደሚ’ ሳይሆን በጥልቅ የሸሪዐ እውቀት የሚመዘን ነው። እኛ ያለብን የነሱን ምክር ከኋላ ሆኖ መከተል ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል:– وَإِذَا جَاءَهُمْ أَمْرٌ مِّنَ الْأَمْنِ أَوِ الْخَوْفِ أَذَاعُوا بِهِ ۖ وَلَوْ رَدُّوهُ إِلَى الرَّسُولِ وَإِلَىٰ أُولِي الْأَمْرِ مِنْهُمْ لَعَلِمَهُ الَّذِينَ يَسْتَنبِطُونَهُ مِنْهُمْ ۗ وَلَوْلَا فَضْلُ اللَّهِ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَتُهُ لَاتَّبَعْتُمُ الشَّيْطَانَ إِلَّا قَلِيلًا “ከደህንነት ወይም ከስጋት አንዳች (ወሬ) በመጣላቸውም ጊዜ እርሱን ያጋንናሉ፡፡ ወደ መልክተኛውና ከእነርሱ ወደ ትዕዛዙ ባለቤቶች (ወደ አዋቂዎቹ) በመለሱት ኖሮ እነዚያ ከእነርሱ (ነገሩን) የሚያውጣጡት ባወቁት ነበር፡፡ በእናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ ከጥቂቶች በስተቀር ሰይጣንን በተከተላችሁ ነበር፡፡” [አኒሳእ: 83]
Hammasini ko'rsatish...
ፍልስጤም - የደም ነጋዴዎች ካርድ! ~~~~~~~~~~ የፍልስጤም ወገኖቻችን ሰቆቃ ከወትሮው በጨመረ ቁጥር ይህንን አስታኮ ዑለማዎች ላይ መዝመት የተለመደ ክስተት ሆኗል። ሙስሊሞች ስሜታቸው የተነካበተን ጊዜ ጠብቀው ዑለማዎችን እንዲንቁ በፍርሃትና በሸፍጠኘነት እየወነጀሉ የጥላቻ መርዝ የሚግቱ opportunisቶች አሉ! የኢኽዋን ቫይረስ ተሸካሚዎች አብይ መታወቂያ ይሄ ነው። የሰለፊያ ዑለማዎች ናቸው በፍርሃትና ጂሃድን በመቃወም የሚወነጀሉት? እነ አልባኒ፣ ኢብኑ ባዝ፣ ዑሠይሚን፣... አይደሉ እንዴ ለአፍጋኒስታን ጦርነት ሲቀሰቅሱ የነበሩት? እነ ረቢዕ የአፍጋኒስታን ጂሃድ ላይ አልተሳተፉም ወይ?! ህይወታቸው በነዚህ የጥመት አንጃዎች አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ሐቅን በማድረስ ላይ አልተዋደቁምን? እነ ኢሕሳን ኢለሂ ዞሂር በተጠመደ ቦምብ አልተገደሉም? እነ ጀሚሉ ረሕማን ኩነር አፍጋኒስታን ውስጥ አልተገደሉም? እነ ሙቅቢል መስጂድ ውስጥ ከተጠመደ ቦምብ ለትንሽ አልተረፉም? ለህይወታቸው ቢሳሱ ነው’ንዴ ሌሎች የተሸበቡበትን ርእስ ከፍ በማድረግ ደም የጠማቸው የጥፋት አንጃዎችን የሚጋፈጡት? የኢኽዋን ቆሻሾች እንደሚወነጅሏቸው ፈሪዎች ስለሆኑ ነው በዚህ ደረጃ ህይወታቸው አደጋ እየተደቀነበት እንኳ ወደኋላ የማይሉት? እነዚህ ሳይሞቅ ፈላዎች ጀግና ከሆኑ ለምን ወደ ፍልስጤም አይዘምቱም? ፍልስጤም ብትርቃቸው እዚሁ አፍሪካ ውስጥ ሙስሊሞች የሚበደሉባቸው በርካታ ሃገራት አሉ’ኮ። ፌስቡክ ላይ ከሚፎክሩ ለምን ነፍጥ አንግበው ጫካ አይገቡም? ሁሌ ከዑለማእ ውስጥ ሰለፊዮቹ ላይ፣ ከሃገራት ውስጥ ሳዑዲ ላይ ነው የሚዘምቱት። ለእስራኤል የደህንነትና የስለላ መረጃዎችን የሚያቀብለው የኩርጂክ የራዳር ማእከል ቱርክ ውስጥ ነው የሚገኘው። ከእስራኤል ከፍተኛ የንግድ አጋሮች ውስጥ አንዷ ቱርክ ነች። ከሙስሊሙ አለም በቱርክ ደረጃ ለሷ ወዳጅ የሆነ የለም። በቅርቡ ቃጠሎ ሲገጥማት የእሳት ማጥፊያ አውሮፕላኖችን የላከች ቱርክ ነች። “የእስራኤል አባት” ተብሎ የሚጠራው ቴዎዶር ሄርዝል ቀብር ላይ የአበባ ጉንጉን ያስቀመጠው ኤርዶጋን ነው። በተለያዩ ጊዜያት የጋራ የጦር ልምምድ ሲያደርጉ እንደነበር የሚታወቅ ነበር። በዚህ ቀውጢ ጊዜ ሳይቀር በጎን ባዶ የቃላት ኳኳታ እያሰሙ ሲያደነዝዙ፣ በሌላ በኩል የንግድ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር ኢኽዋኖችና የነሱን ተውሳክ የተሸከሙ አካላት ነጋ ጠባ “ሳዑዲ፣ ሳዑዲ” እያሉ ማላዘን ነው የሚቀናቸው። ኢላማቸው መሪዎቹ አይደሉም። ወደ ዑለማዎቹ ለመሻገር ነው የነሱን ጉዳይ የሚያነሱት። እስኪ አሁን “ጂሃድ በደመ–ነፍስ የሚካሄድ ሳይሆን ዝግጅት ይፈልጋል” የሚል ምክር ምን እንከን ይወጣለታል? ሃሳቡን አይቀበሉ! ምናል በቅንነት ተመልክተው ለሌሎች የሚሰጡትን ‘ዑዝር’ ቢሰጧቸው? እንዴትስ እዝነት መቆርቆራቸው በክፋትና በፍርሃት ይተረጎማል? የቢድዐ ልክፍት ያሳበዳቸው ወፈፌዎች ካልሆኑ በስተቀር ይሄ ጤነኛ አእምሮ ላለው የሚሰወር አይደለም። ቤት ውስጥ በሚዘጋጅ የጠርሙስ ቦምብ ነው ኒኩሌር ከታጠቀ ኃይል ጋር የምትዋጋው? በወፍ ማደኛ ወስፈንጠር ነው ከታንክ ጋር የምትፋለመው? በህልም ነው በውን ክላስተር ቦምብ የሚያዘንቡ ጄቶች በወንጭፍ የሚወርዱት? ለመሆኑ ለምንድን ነበር ሙስሊሞች መካ ላይ እያሉ በጂሃድ ያልታዘዙት? ደካማ ስለነበሩ አይደለምን? መዲና ውስጥ አቅማቸው ሲጠነክር’ኮ ነቢዩን ﷺ የተሳደበ አካል እርምጃ ተወስዶበታል። መካ ሳሉስ? ከስድብ በላይ ብዙ አልደረሰባቸውም? የገማ እንግዴ ልጅ አልተጣለባቸውም? ለምን እርምጃ አልወሰዱም? ምክንያት የለውም’ንዴ? ሶሐቦች ያ ሁሉ ሲደርስባቸው፣ እነ ሱመያ እነ ያሲር ሲገደሉ፣ ሌሎች አገር ጥለው እንዲሰደዱ ያደረጋቸው ግፍ ሲያስተናግዱ የፈለገ ይሁን ብለው አሳቻ ቦታ እየጠበቁ ጥቃት ማድረስ አቅቷቸው አልነበረም’ኮ! ቢላል ክፉኛ ሲያንገላታው የነበረውን ኡመያን ለመግደል ከአመታት በኋላ የተካሄደውን የበድር ዘመቻ ሳይጠብቅ ገና ቁስሉ ሳይደርቅ መካ ውስጥ መግደል አቅቶት’ኮ አልነበረም። ሸሪዐው የጂሃድን ትእዛዝ ያዘገየው ያለ ምክንያት ነው’ንዴ? አቅም እንዲያጎለብቱ፣ ዝግጅት እንዲያደርጉ እንጂ! የላቀው አላህ ምንድነው ያለው? وَأَعِدُّواْ لَهُم مَّا ٱسۡتَطَعۡتُم مِّن قُوَّةٖ وَمِن رِّبَاطِ ٱلۡخَيۡلِ تُرۡهِبُونَ بِهِۦ عَدُوَّ ٱللَّهِ وَعَدُوَّكُمۡ “ለእነሱም ከማንኛውም ኃይል (መሳሪያ) እና ከታጀቡ ፈረሶችም የቻላችሁትን ሁሉ በእርሱ የአላህን ጠላትና ጠላታችሁን የምታሸብሩበትን አዘጋጁላቸው።" [አልአንፋል፡ 60] ሶሐቦቹ ይህንን መለኮታዊ ትእዛዝ ተከትለው ጠላትን የሚገዳደር ዝግጅት አድርገዋል። ዛሬ ወደ ጦር ሜዳ የምትጓዘው በፈረስ፣ የምትወረውረውም ቀስት አይደለም። ጠላት አእላፍ ኪሎ ሜትሮችን ርቆ አንተን ማደባየት ይችላል። ሙስሊሙ የትኛው ዝግጅት ነው ያለው? ምናልባት “የሰለጠኑ ፈረሶችን አዘጋጅተናል” ይሉ ይሆን? አይሉም አይባልም እነዚህ ማስተዋል የተሳናቸው ጉዶች? በዓለም ላይ እጅግ አውዳሚ የሆኑ ሃይድሮጂን ቦምቦች፣ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች፣ ግዙፍ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች፣ ጅምላ ጭራሽ ባዮሎጂካል መሳሪያዎች፣ ከራዳር ቁጥጥር ውጭ የሆኑ የተራቀቁ የጦር አውሮፕላኖች፣ ወዘተ የታጠቁት ሙስሊም ሃገራት አይደሉም። ወደ 16 ሺህ ከሚገመተው የዓለም ኒኩሌር 90 ከመቶ በላይ በአሜሪካና በራሺያ እጅ ነው ያለው። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በጃፓን ሂሮሽማና ናጋሳኪ ከተሞች ላይ 2 መቶ ሺህ አካባቢ ህዝብ ያለቀው በሁለት ኒኩሌር ብቻ ነው። ይህን ያክል ርቀዋል። የዛሬ ሙስሊም ሃገራት የ1945ቷን ጃፓን አያክሉም። ከመሆኑም ጋር ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ ተንኮታኩታ ነበር እጅ የሰጠችው። ጋዳፊን በቀናት ውስጥ ያሽመደመደው የፈረንሳይ አየር ኃይል እንጂ ተቃዋሚዎቹማ እዚህ ግባ የሚባል አቅም አልነበራቸውም። በርካቶች ዘንድ ተጋኖ ተስሎ የነበረው የሳዳም ጦር እንደ ቅቤ የቀለጠው ያለ ምክንያት አይደለም!! “የዐረብ ሃገራት ናቸው ጉድ የሰሩት” እያሉ ዋናውን ምስል መዘንጋት እራስን ማታለል ነው? ወደድንም ጠላንም በመሃላችን ያለው ርቀት ከምንገምተው በላይ እጅግ የሰፋ ነው።  እጅግ በርካታ “ሙፈኪሮች” ያለንበትን ተጨባጭ በውል አልተረዱም። ምነው ችግሩ በዚህ በቅቶ መከራችን በቀለለ?! በዚህ ሰመመናቸው ውስጥ ሆነው “ፊቅሁል ዋቂዕ አልገባቸውም” እያሉ ዑለማዎች ላይ መዝመታቸው ባሰ እንጂ። የነሱ የጥመት አውራዎች ሲነኩ ግን “ዑለማእ ተሰደበ” እያሉ አገር ያቃጥላሉ። ዑለማዎቻችንን ተውልን። ክፍተት ቢኖራቸው እንኳ እንደ ቀርዷዊ ካሉ የጥፋት ቁንጮዎች ጋር የሚነፃፀሩ አይደሉም። በምን ስሌት ነው እነዚያ እየታለፉ በነዚህ ላይ ሌት ከቀን የሚዘመተው?! እንዲህ አይነቱ ኸዋሪጅ ጋር እየዋለ፣ የኸዋሪጅ ፊክራ እየጠጣ፣ ኸዋሪጅኛ የሚያስነጥስ የጥጃ ቀንዳም ነገሮችን በውል መመዘን፣ ግራ ቀኝ መመልከት የሚባል አያውቅም። ሙስሊሙ ዓለም ከአሜሪካም፣ ከራሺያም፣ ከፈረንሳይም፣ ከእንግሊዝም፣ ከቻይናም፣ ከህንድም፣ ከእስራኤልም ጋር እንዲዋጋ ነው የሚሹት። ተጨባጩ ግን እንኳን ከነዚህ ሁሉ ቀርቶ አንዱንም በሚቋቋምበት ቁመና ላይ አለመሆኑ ነው። ቱርክ ጦሯን ድንበር ተሻግራ ሶሪያ ውስጥ ብታስገባም "ለሃገሬ ስጋት ናቸው" የምትላቸውን የኩርድ ታጣቂዎች ከማጥቃት ባለፈ በሻረል አሰድን ለመንካት የማትደፍረው ወዳው አይደለም፤ ራሺያን ፈርታ እንጂ። ቻይና “የግዛቴ አካል ናት” የምትላትን
Hammasini ko'rsatish...
ታይዋንን ለመጠቅለል ከሰባ አምታት በላይ አድፍጣ የምታደባው ለታይዋን የሚሆን አቅም አጥታ አይደለም። ከታይዋን ጎን ከቆምችዋ አሜሪካ በኩል የሚመጣባትን ጣጣ ሽሽት እንጂ። ሙስሊሙ ዓለም አቅሙ ከቻይና በጣም ያነሰ ነው። ቻይና ለዚህ አላማ በሁሉም ዘርፍ አቅሟን ለማጎልበት ሌት ከቀን እየተጋች ነው። እኛጋ ደግሞ መካሪ ዑለማዎቹን እያብጠለጠለ፣ ከንቱ ቀረርቶ እያሰማ ደካማ ሃገራቱን ከጠላት ቀድሞ ያፈርሳል፤ እጁን በእጁ ይቆርጣል። ይህንን የተሳከረ አካሄዱንም ጀብድ አደርጎ ይኮፈስበታል። እንደሚታወቀው የሙስሊም ዓለም መሳሪያ ሸማች እንጂ አምራች አይደለም። በገንዘቡ ለሚገዛውም ብዙ ቅድመ ሁኔታ ይቀመጥበታል። እንዲያውም ብዙዎቹ መሳሪያ መተኮስ፣ ሰራዊት ማዝመት ሳያስፈልግ ጠላት እነዚህን እንጭጮች በመጠቀም ሰላማቸውን ያናጋቸው ናቸው። እነዚህ ወፈፌዎች ግን ጉዳዩን ከሴትና ህፃናት መሃል አድፍጦ የአጭር ርቀት ሮኬቶችን በማስወንጨፍ የሚሞከር አድርገው ያስባሉ። በአጥፍቶ መጥፋትና በትንንሽ ሮኬቶች/ድሮኖች ጥቃት ጊዜያዊ ቡረቃ እንጂ ዘላቂ ድል አይመጣም። ይሄ ቅዠት ነው። ጠላትማ ምን ያድርግ? እነዚህ አሉ እንጂ ጠላት ወደ ሙስሊም ሃገራት እንዲገባ ተልእኮ ፈፃሚ የሆኑ ወልጋዶች!! “ምሳርማ ምን ያርግ * የብረቶች ልጅ ያ የኛ ወልጋዳ * አስጨረሰን እንጂ!!” ዑለማዎች “ጂሃድ የኢማንም፣ የትጥቅም፣ የሰው ሃይልም ዝግጅት ይፈልጋል” ማለታቸውን በመቃረን “እነ ሶላሑዲን,… አሽዐሪዮች ነበሩ” ይላሉ። የኢማን ዝግጅት አያስፈልግም ለማለት ነው እንግዲህ ይሄ የሚቀርበው? “ተመጣጣኝ ወይም ተቀራራቢ አቅም መኖር ሸርጥ አይደለም። ሶሐቦቹም በቁጥር ትንሽ ሆነው ነው የተዋጉት” ይላሉ፣ እነዚህ የሚዲያ ላይ ነብሮች። በመጀመሪያ የዑለማዎቹን ንግግር ለትችት በሚመቻቸው መልኩ ነው አዛንፈው የሚያቀርቡት። ደግሞ’ኮ አብዛኞቹ ከሶሻል ሚዲያ ቀረርቶ ያለፈ ሙከራም የላቸውም። በተለይ ደግሞ የኛዎቹ። እስኪ ከነዚህ በያመቱ የፍልስጤምን ጉዳይ ለቡድናዊ ፕሮፓጋንዳ ከሚጠቀሙ አካላት ውስጥ ወደ እስራኤል የሚዘምት ጥቀሱ? እዚያው ፍልስጤም ውስጥ ከሚንደፋደፉ ደካማ ቡድኖች ውጭ እራሳቸውን ወደ ሰለፊያ የሚያስጠጉ ተውሳኮችን ጨምሮ፣ አይሲስ፣ አልቃዒዳ፣ ኢኽዋን፣ ቦኮ ሀራም፣ ... በፍልስጤም ጉዳይ ይነግዳሉ እንጂ እስራኤልን አይዋጉም።  ደግሞስ የኢማን፣ እንዲሁም ከትጥቅና ከሰው ኃይል ደግሞ ምክንያታዊ የሆነ ዝግጅት ያስፈልጋል ማለት እንዴት ያስወቅሳል?! እና ጠላት ባካፋና በዶማ ነው የሚሸነፈው? ጠላት ባመረተው መሳሪያ እየተታኮስክ መሃል ላይ “አንዴ አቁሙ! ጥይት ጨርሻለሁ” ልትል ነው? ጂሃድን የህፃናት ጨዋታ አስመስሉት’ኮ! ፍልስጤሞችን ውሰዱ! ለፍልስጤማዊያን ተፈናቃዮች ከፍተኛውን እርዳታ የሚያቀርቡት እነማን ናቸው? አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት! ኤሌትሪክና የነዳጅ አቅርቦት እንኳ ከእስራኤል’ኮ ነው የሚገዙት። ከዚህ በላይ አቅመ ቢስነት አለ?! በዚህ አቅም ተሁኖ ነው ስለ ጂሃድ የሚወራው? እሱ በታንክ አንተ በድንጋይ ሆነህ ነው ድል የምትጠብቀው? እስካፍንጫው የታጠቀን ወታደር ቀይ ካርድ ስላሳየኸው የሚሟሟ ይመስለሃል? ጂሃድን በዚህ መልኩ ነው የምትረዳው? ሱብሓነ’ላ፞ህ!! መቼም የምፅፈው ለፍልስጤማውያን እንዳልሆነ ግልፅ ነው። የምፅፈው ይህን ክስተት እያስታከኩ ዑለማዎችን ስለሚያንቋሽሹ አካላት ነው። የሚገርመው ከነዚህ ዋልጌዎች ቅርሻት ስር የሚልከሰከሱ “ሰለፊ ነን” ባዮች መኖራቸው ነው። አንድ ሰው የሆነን ዓሊም አቋም ቢነቅፍ ወግ ነው፣ አቅሙ ካለው። በዚህ መልኩ ከዑለማዎች መርጦ ሰለፊዮቹን በጅምላ የሚዘረጥጥ፣ እልህን መንሃጁ ያደረገ፣ ከሰለፊዮች ጋር መፋጠጥን እንደ ጀብድ የሚቆጥር፣ ከዑለማእ ንግግር ውስጥ አቃቂር ማውጣትን፣ ‘ሰቀጧት’ መልቀምን ንቃት ያደረገ ከንቱ ፍጡር ማየት ነው የሚደንቀው። ደግሞም የሰው ኃይል ቁጥርም ቢሆን እነዚህ ስሜት ያሰከራቸው አካላት እንደሚስሉት ሳይሆን በተጭባጭ ከግምት ይገባል። ይሄው ቁርኣናዊው ማስረጃው፦ يَـٰٓأَيُّهَا ٱلنَّبِيُّ حَرِّضِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ عَلَى ٱلۡقِتَالِۚ إِن يَكُن مِّنكُمۡ عِشۡرُونَ صَٰبِرُونَ يَغۡلِبُواْ مِاْئَتَيۡنِۚ وَإِن يَكُن مِّنكُم مِّاْئَةٞ يَغۡلِبُوٓاْ أَلۡفٗا مِّنَ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ بِأَنَّهُمۡ قَوۡمٞ لَّا يَفۡقَهُونَ “አንተ ነቢዩ ሆይ! ምእምናንን በመዋጋት ላይ አነሳሳቸው፡፡ ከናንተ ውስጥ 20 ታጋሾች ቢኖሩ 200ን ያሸንፋሉ፡፡ ከናንተም 100 ቢኖሩ ከነዚያ ከካዱት እነሱ የማያውቁ ህዝቦች ስለሆኑ 1,000ን ያሸንፋሉ።” [አል አንፋል፡ 65] አስተውሉ! ንፅፅሩ አንድ ለአስር ነው። ሊያውም ተዋጊን ከተዋጊ ጋር። አሰስ ገሰሱን ሁሉ ሂሳብ እንዳታስገባ!! ቀጠለ፦ ٱلۡـَٰٔنَ خَفَّفَ ٱللَّهُ عَنكُمۡ وَعَلِمَ أَنَّ فِيكُمۡ ضَعۡفٗاۚ فَإِن يَكُن مِّنكُم مِّاْئَةٞ صَابِرَةٞ يَغۡلِبُواْ مِاْئَتَيۡنِۚ وَإِن يَكُن مِّنكُمۡ أَلۡفٞ يَغۡلِبُوٓاْ أَلۡفَيۡنِ بِإِذۡنِ ٱللَّهِۗ وَٱللَّهُ مَعَ ٱلصَّـٰبِرِينَ  “አሁን አላህ ከእናንተ ላይ አቀለለላችሁ፡፡ በናንተ ውስጥም #ድክመት መኖሩን አወቀ፡፡ ስለዚህ ከናንተ 100 ታጋሾች ቢኖሩ 200ን ያሸንፋሉ፡፡ ከናንተም 1,000 ቢኖሩ በአላህ ፈቃድ 2,000ን ያሸንፋሉ፡፡ አላህም ከታጋሾቹ ጋር ነው፡፡” [አል አንፋል፡ 66] ልብ በሉ! እዚህ ላይ ደግሞ አንድ ለሁለት ሆነ። ለማቃለሉ የቀረበው ምክንያት ሙስሊሞች ዘንድ ድክመት መኖሩ ነው። ዛሬስ ያለው ድክመት እዚህ ላይ ከተጠቀሰው የባሰ ነው ወይስ የተሻለ? እጅግ በርካታ ዓሊሞች ናቸው “የዛሬ ሙስሊሞች ከድክመታቸው አንፃር ሲታዩ የመካ ዘመን ምሳሌ ላይ ነው ያሉት” የሚሉት። የሙስሊሙ ቁጥር ከቢሊዮን በላይ መሆን ከጦርነት አንፃር ቁም ነገር ሆኖ የሚነሳ አይደለም። የጠላትን ዝግጅት በሚገዳደር መጠን ዘመኑን የዋጀ ለሌሎች የሚተርፍ የሰለጠነ ኃይል ሊሆን ቀርቶ ለራሱም መሆን አቅቶታል። በ1948ቱ የዐረብ እስራኤል ጦርነት ጊዜ ዮርዳኖስ ባይዘልቅም በጥቂት ሰራዊት ከሌሎቹ ዐረብ ሃገራት የተሻለ ድል አስመዝግባ ነበር። ለዚህም በቀዳሚነት የሚነሳው ምክንያት በእንግሊዝ የሰለጠኑ ጠንካራ ወታደሮች ስለነበሯት ነው። ከሰመመንህ ንቃ ወንድሜ! የፈለገ ብትደፈን ቴኳንዶ እንኳ ቁም ነገር ሆኖ ክትትል በሚደረግበት ሃገር እየኖርክ “በቂ የሰው ኃይል አለን” “ዋናው በቁጥር መብዛት አይደለም” እስከማለት አትጨፈን! አዎ! የቁጥር ብዛት ሸርጥ አይደለም። በአላህ ፈቃድ ስንት ትልቅ ጭፍራ ጠንካራ ኢማን ባለው ትንሽ ጭፍራ ተሸንፏል?! ከመሆኑም ጋር “የኢማንም፣ የቁስም ዝግጅት እስከምናደርግ እንታገስ። አሁን ባለንበት ሁኔታ ሙስሊሞችን መማገድ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያደላል” ማለታቸው በምን አግባብ ነው እንደ ፍርሃት የሚቀጠረው? ደግሞም መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ እየነገርኩህ እንጂ በፍርሃት ቆፈን እንድትንቀጠቀጥ እያስፈራራሁህ አይደለም!! አቅምን ማወቅ ብስለት እንጂ ፍርሃት አይደለም። አቅምህን ስታውቅ ነው ለተሻለ የምትዘጋጀው። ሰላም!!
Hammasini ko'rsatish...
👆👆👆 🔈 #ረመዳንን የጾመ ሰው ከዚያም ከሸዋል ወር 6 ቀን ያስከተለ አንድ አመት እንደጾመ ነው በሚል እና ተያያዥ ጉዳዮች ብይን 🎙 በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 🎧 ደቂቃ 23:15 https://t.me/shakirsultan
Hammasini ko'rsatish...
ሙሐደረ_ቁ·82_ረመዳንን_የጾመ_ሰው_ከዚያም_ከሸዋል_ወር_6_ቀን_ያስከተለ.mp35.57 MB
ከረመዳን በኋላ
Hammasini ko'rsatish...
ከረመዳን በኋላ.MP34.85 MB
ህይወት ህይወት እንደ ጅረት ነው። አንዴ የነካሀውን የጅረት ውሃ ደግመህ መንካት አይቻልህም። ውሃው ለማምለጥ የሚጥር እጅግ ፈጣን ስለሆነ ሳይሆን ዳግም ስለማይመለስ ነው። በእያንዳንዱ የህይወትህ ሴኮንዶች ውስጥ ስራ፤ ተደሰት፤ ተጠቀም።
Hammasini ko'rsatish...
ጀግናዬ………… #በመከራ_ማዕበል_እየተናወጥክም ቢሆን አሏህን ሁሌም አመስግን ማመስገን የፈተናዎች ሁሉ ማምለጫ ትልቅ የአዕምሮ ረፍት ነው።
Hammasini ko'rsatish...
አትጨነቅ! በህይወትህ ውስጥ በጣም ሲያስጨንቁህ ከርመው "አያልፉም" ብለህ ስታስባቸው የነበሩ ከባባድ ነገሮች አልፈዋል። ምናልባት አሁን ረስተሃቸው ይሆናል። አሁንም ቢሆን ይህ ቀን ያልፍና ትረሳዋለህ። በቃ ለየትኛውም ነገር አስብ እንጂ አትጨነቅ! ጭንቀት ውጤት አያመጣም 😊 ሰኪና የሆነች ምሽት
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.