Addis Ababa City Manager Office
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 474
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kun
-2130 kun
Postlar arxiv
የሲንጋፖር ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግን በክብር ተቀብያለው።
ውይይታችን በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለንን ግንኙነት ለጋራ ነጋችን ወሳኝ በሆኑ መስኮች በጋራ ለመሥራት በምናደርገው ጥረት ውስጥ አንድ ጠቃሚ ርምጃ ነው። በተለይም በክሂሎት ልማት እና የካርበን ብድር ትብብር ላይ ያደረግናቸው የመግባቢያ ስምምነቶች ጽኑ እና ለነገው ገበያ ዝግጁ የሆኑ ሠራተኞችን ለማፍራት ብሎም በአየር ንብረት ጥበቃ ረገድ ዘላቂ፣ ዝቅተኛ ካርበን የሚያወጣ እድገት ለማረጋገጥ ያለንን የጋራ አቋም የሚያንፀባርቅ ነው።
ከሲንጋፖር ጋር ይኽን የወዳጅነት እና የትብብር ጉዞ በጋራ በመቀጠላችንም ክብር ይሰማናል። በላቀ ተግባራዊ ትብብር ንግድ እና ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት፣ ዘመናዊ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስን በማልማት፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በገንዘብ ልውውጥ ቴክኖሎጂ፣ ሳይበር ደኅንነት እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለንን ትብብር ለመጠቀም እጅግ ሰፊ አቅም አለን።
I have the distinct honor of welcoming His Excellency Lawrence Wong, Prime Minister of the Republic of Singapore.
Our meeting marks an important milestone in the relationship between our two countries as we continue to deepen cooperation in areas critical to our shared future. In particular, the signing of two Memoranda of Understanding on Skills Development and Carbon Credits Collaboration reflects our joint commitment to building resilient, future-ready workforces and advancing sustainable, low-carbon growth.
We are honored to continue this journey of friendship and collaboration with Singapore. There is tremendous potential to harness the strengths of our partnership through further practical cooperation, expanding trade and investment, developing smart transport and logistics, and strengthening collaboration in digital infrastructure, fintech, cybersecurity, and artificial intelligence.
ዛሬ ክቡር የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግን በክብር ተቀብለን፣ የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ አስጎብኝተናቸዋል።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት፣ ለጥቁር ሕዝቦች ነፃነት ትግል ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች መታሰቢያ ሐውልት ሥር የአበባ ጉንጉን አኑረዋል።
ክቡር የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ሎውረንስ ዎንግ በምድረ ቀደሞቷ ኢትዮጵያ እንዲሁም በውቧ ከተማችን አዲስ አበባ የሚኖርዎት ቆይታ ፍሬያማ እንዲሆን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረው የፀረ-ሙስና ቀን "ትዉልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር ‶ በሚል መሪ ቃል ተከበረ።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት የፀረ ሙስና ቀንን አስመልክት በአለም ለ22ኛ ጊዜ በሀገራችንን ለ21ኛ ጊዜ አስመልክቶ ከፅ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር በዛሬዉ እለት ተከብሮ ዉሏል።
በዚሁ መድረክ የሰነ-ምግባር እና የፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክተር አቶ ምህረቴ ሙሉሰዉ በዚሁ መድረክ እንደተናገሩት ሙስና ደረጃው ይለያይ እንጂ በሁሉም የዓለማችን ሀገራት የሚገኝና የሁሉም ሀገራት ተግዳሮት መሆኑ ገልፀው እንደ ሀገር የሙስና ሂደቱን ለመቀነስ በጋራ እንዲሁም የተጠናከረ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ተናግረው እንደ ከተማ ትውልድን በፀረ ሙስና ትግል ግንባታና በስነ ምግባር የታነፀ እና ሙስናናን የሚፀየፍ ትዉልድ ለመፍጠር እንደ ተቋም ሰፊ ሰራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃና በከተማችን የፀረ ሙስና ትግል የእስካሁን እንቅስቃሴ ጥሩ የሚባል ጅማሮ ሲሆን በተለይም አዲስ አበባ ከተማ የሙስና ወንጀልን ለመከላከል በልዮ ትኩረት የሰነ-ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ተቋማት፣የሲቪክ ማህበራት፣የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል እና መዋቅሮችን በመዘርጋት ሙስናን መከላከያ ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።
አክለዉም በተቋማት የስነ-ምግባር እና የፀረ ሙስና ትግል ላይ እየተከናወኑ የሚገኙ ሰራዎች ወደ ተግባር በመቀየርና ተቋማትም የሚሰጡ አገልግሎቶች ከብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግ ሁሉም አካላት በሙስናን በመታገልና በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በዚሁ መድረክ የስነምግባር ምንነት፣ብልሹ አሰራርን የመቀነስ መንገድ፣የስነምግባር መርሆች፣የስነምግባር ምንጮች፣ሙስና የሚያስከትለው ጉዳት፣የሙስና የመከላከያ ስልቶች፣የፀረ ሙስና ትግል ሁኔታዎች በእነዚህና በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች የፅ/ቤት የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል ከፍተኛ ባለሙያ በሆኑት በአቶ አለማየሁ ሙላት ሰነድ ቀርቦ ዉይይት ተካሂዶበት መድረኩ ተጠናቋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ሳምንታችንን አጨልመን አንጀምርም!
የሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ ለእኛ ፍካትና ተስፋ የሚሰጠን ቀን ነው!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
‘ወርቃማ ሰኞ’ የሚል መጠሪያ የተሰጠውና በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ዘወትር ማለዳ የሚካሄደው የመማማሪያ መርሃ-ግብር ሁለተኛ ዓመት ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተከብሯል። ይህ ከሁለት ዓመት በፊት በክብርት ከንቲባ ሃሳብ አመንጭነትና መሪነት የተጀመረው መርሃ-ግብር ‘ጥቁር ሰኞ’ን ወደ ‘ወርቃማ ሰኞ’ የቀየረ ሆኗል። የከንቲባ ጽ/ቤት፣ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና የኮሙኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የሚሳተፉበት ‘ወርቃማ ሰኞ’ ሦስት ግቦችን (ከተማችንን የብልጽግና ተምሳሌት እናደርጋለን፣ ስንተባበር ለውጥ እናመጣለን እና እዚህ ያለነው ለማገልገል ነው) በማነገብ የተጀመረ ነው።
በሁለተኛ ዓመት ክብረ በዓል አከባበር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሳምንቱን መጀመሪያ ሰኞን በፍካትና በተስፋ እንጂ አጨልመን አንጀምረውም ብለዋል። ይህ ለራስ እድገት አስፈላጊ የሆነው መርሃ-ግብር በአሁኑ ሰዓት ወደ ሁሉም የከተማዋ መዋቅሮች እንደተስፋፋ እና እየተተገበረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
በዕለቱ ከክብርት ከንቲባ መልዕክት ባሻገር ‘ወርቃማ ሰኞ’ በሚል ርዕስ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቲያትርና ባህል አዳራሽ ተውኔት ያቀረበ ሲሆን የሁለተኛ ዓመት የመርሀ-ግብሩ ጉዞም ለታዳሚው በገለጻ መልክ ቀርቧል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ዛሬ ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 8፡30 በመርካቶ፣ አብነት ሆቴል፣ ሞላ ማሩ፣ ተ/ኃይማኖት ፔፕሲ ፋበሪካ ፣ሰባተኛ በከፊል፣አማኑኤል ሆስፒታል፣ ሻወል ደማ ት/ቤት፣ በመሳለሚያ፣ አማኑኤል ቤተክርስትያን እስከ ኮካ፣
👉 2፡30 እስከ 10፡00 በሰበታ ከተማ ፣ አቀበና ውሃ ማምረቻ ፣ ዲማ ሆስፒታል፣አኔ ዲማ፣ ወጣቢቻ፣ ጉዱ፣ ሙሎ፣ ከሚሴ፣ድሬ ከአስፋልት በላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ ፣ከሰብስቴሽን ፣ ባቡር ሐዲድ፣ ሲዳሞ አዋሽ፣ ገንደ ቆሬ፣ ገላን መኖሪያ ቤቶች፣ ገመዳ ማህበር፣በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ፣ ካፍ ማደያ አካባቢ፣ ብርጭቆ፣ አስኮ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ዓለም ባንክ
👉ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 9፡30 በሰሜን ማዘጋጃ፣ ሸገር መናፈሻ፣ መስቀሉ ሥጋ ቤት፣ ዳዊት ፋርማሲ፣ ዕንቁላል ፋብሪካ አካባቢ፣ አባዲና ፣ ሩፋኤል ቤ/ክ አካባቢ እና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
ስለሆነም አገልግሎቱ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ብሏል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በደማቅ ሁኔታ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ በተሳተፉበት በተካሄደው "ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ" ላይ በደረቅ ቆሻሻ መልሶ መጠቀምና ዑደት ስራ ላይ የተሰማሩ ማህበራት ቆሻሻን በመሰብሰብ ባሳዩት ትጋት ከፍተኛ ገቢ ማግኘት ችለዋል።
የማህበራቱ ጥረት ለከተማው ጽዳት ጥረት ትልቅ ድጋፍ ሲሆን፣ የስፖርቱን ደስታ ከአካባቢ ንጽህና እና ከገቢ ማስገኛነት ጋር ባገናኘ መልኩ ትልቅ ትምህርት ሰጥቷል።
"ብዙ የሰበሰበ ብዙ አገኝ" የሚለው መርህ በደማቅ ሁኔታ ሩጫው በተካሄደበት ወቅት ታዳሚዎች የተጠቀሙባቸውን ያገለገሉ የፕላስቲክ ጠርሙሶች ወዲያውኑ በመሰብሰብ ረገድ የማህበራቱ ሚና እጅግ የጎላ ነበር።
በተለይም የ'ሀይላንድ' ውሃ ጠርሙሶችን ለመሰብሰብ ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ቆሻሻ ወደ መልሶ ማምረቻ ግብዓትነት እንዲለወጥ አድርገዋል።
ህጋዊ ባጆችን በመጠቀም በስርዓት ሲሰሩ የዋሉት እነዚህ ማህበራት፤ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት ለራሳቸው ብልጽግና መሰረት ከመጣልም በተጨማሪ የከተማዋ ጽዳት እንዳይጓደል እና የአካባቢ ብክለት እንዳይፈጠር በመከላከል ለአካባቢ ፅዳት ትልቅ ድርሻ ተወጥተዋል።
ይህ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ትልቅ የኢኮኖሚ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የደረቅ ቆሻሻን ችግር ወደ "ብልፅግና ዕድል" መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ስኬታማ ምሳሌ ሆኗል።
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በአንድ ላይ የሚያሰባስብበት መድረክ መሆኑ ለፕላስቲክ መልሶ መጠቀም ስራውም ታላቅ ሽፋን በመስጠት፣ የአካባቢ ንቃተ-ህሊናን ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ አድርጓል።
ህዳር 4/2018 አ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ተወዳጁን፣ ተናፋቂውን እንዲሁም ባለፉት 25 ዓመታት የከተማችን አንዱ ድምቀት እና ዓለም አቀፍ መገለጫ የሆነውን ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን በልዩ ድምቀት አስጀምረናል።
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የዓለም ኮከብ አትሌቶች መለማመጃ እና መኖሪያ በሆነችው መዲናችን አዲስ አበባ ከልጅ እስከ አዋቂ፣ ከፕሮፌሽናል አትሌት እስከ ጤና ቡድኖች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እየተሳተፉበት፣ እየተዝናኑበት፣ ጤናቸውን እየጠበቁበት፤ ወንድማማችነትን፣ እህትማማችነትንና አብሮነትን እያጠናከሩበት 25 የድምቀት ዓመታትን አሳልፏል።
የዚህ ታላቅ ውድድር መስራች የሆነውን ጀግናው አትሌታችንን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴን፣ እንዲሁም አጠቃላይ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አመራሮችን፣ ባለሙያዎችን እና አስተባባሪዎችን ለዘመን ተሻጋሪ ሥራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ።
አስተዳደራችን በቀጣይም ይህ ውድድር እንደ ሌሎች ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ይበልጥ ተጠቃሽ እና ተተኪዎችን ጭምር የምናፈራበት እንዲሆን ይበልጡኑ አበክሮ ይሠራል።
ተሳታፊዎች፣ የፀጥታ አካላት፣ በጎ ፈቃደኞች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ለውድድሩ ስኬት ለነበራችሁ በጎ አስተዋፅኦ ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ
Jaalatamaa, hawwamaa akkasumas waggoota 25 dabraniif miidhagina magaalaa keenyaa keessaa tokko fi ibsituu idil-addunyaa kan ta'e Fiigicha Guddaa Itoophiyaatti miidhagina addaatiin eegalchiisneerra.
Fiigichi guddaan Itoophiyaa bakka shaakalaa fi jireenya atileetota urjii idil-addunyaa kan taate madiinaa teenya Finfinneetti ijoollee hammaa ga'eessaatti, atileetota piroofeeshinaalaa hammaa gareelee fayyaatti, namoota beekamoo fi hawaasni diploomaatii irratti hirmaachuun; itti bashannanaa, fayyasaanii itti eeggataa; obbolummaa, obboleettummaa fi walooma itti cimsaa waggoota miidhaginaa 25 dabarseera.
Hundeessaa dorgommii guddaa kanaa kan ta'e gooticha atileetii keenya ajajaa kumaa Haylee G/Sillaasee, akkasumas hooggantoota waliigalaa, ogeessotaa fi haala mijeessota fiigicha guddaa Itoophiyaa hojii keessan bara cehaa ta’een baga gammaddan jechuun barbaada.
Bulchiinsi keenya fuuldurattis dorgommiin kuni akka dorgommiiwwaan daandii gubbaa idil-addunyaa biroo caalatti kan yaamamuu fi bakka buutotas kan itti oomishnu akka tahu daran cimsee ni hojjeta.
Hirmaattonni, qaamoleen nageenyaa, tola ooltonni, ogeessonni miidiyaa fi qaamoleen qooda fudhattootaa biroo milkaa'ina dorgommichaaf gumaacha gaarii qabaattaniif onneerraa isin galateeffadha.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu
We have successfully launched the Great Ethiopian Run, a beloved event and one of a key international emblem of our city for 25 years.
Held in Addis Ababa, home to world-class athletes, the race has just completed 25 special years of promoting health, unity, and participation across all segments of society, from children to the diplomatic community.
We congratulate our iconic Major @Haile Gebrselassie, the founder and pillar of this event, along with all the leaders and organizers of the Great Ethiopian Run, for their historic work.
Our administration commits to ensuring this race becomes as globally recognized as New York and Tokyo marathons, and continues to be a crucial platform for nurturing future athletes.
A heartfelt thank you to all participants, security personnel, volunteers, media, and stakeholders for contributing to the success of the race.
ውድ ተመራቂ መኮንኖች ፤ ወደ ሥራ ስትሰማሩ ሙያችሁን በታማኝነት፣ በቅንነት፣ ለእውነት በመወገንና በአርቆ አሳቢነት በመመራት ሐቀኛ የሕዝብ አገልጋይነትን በብቃት እንድትወጡ አደራ እላለሁ።
የከተማ አስተዳደሩ ኮሌጁ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ለመሆን ለሰነቀው ራዕይ እንደ ሁልጊዜውም ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ!"
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
