Addis Ababa City Manager Office
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 474
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kun
-2130 kun
Postlar arxiv
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐጅ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸዋል፡፡
በአባታችን ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት እጅግ አዝኛለዉ !!
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እጅግ ትሁት ፣ የሀገር ወዳድ ምልክት ፣ በሁሉም ዘንድ የሚወደዱ ፣ የሚደመጡ እና የሚከበሩ አባታችን ነበሩ ።
ለቤተሰቦቻቸዉ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ ፣ እንዲሁም ለመላዉ የኢትዮዽያ ሕዝብ በከተማ አስተዳደራችን ስም ልባዊ መፅናናትን እመኛለዉ ።
ፈጣሪ አምላክ ነብሳቸዉን በአፀደ ገነት ያኑርልን ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስናካሄድ የነበረዉ የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረካችን ተጠናቅቋል ።
በግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ በሩብ ዓመቱ እና በ90 ቀናት ስራዎቻችን በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የትኩረት መስኮች የተገኙ በርካታ አበረታች ዉጤቶችን ይበልጡን አጠናክሮ ለማስቀጠል ፣ የታዩ ጉድለቶችን ፣ ብልሹ አሰራሮችን በፍጥነት ለማረም እና ዉጤታማነትን በወጥነት አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጠናል ።
በበጀት አመቱ ቀሪ ጊዜያት ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባሮቻችን ተጠናክረዉ የሚቀጥሉ ይሆናል ፣ በዚህም የኑሮ ጫናን ለመቀነስ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርት አቅርቦት መሻሻሎችን ማስቀጠል ፣ የከተማዉን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ፣ የገቢ አሰባሰባችንን ማሳደግ ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር የታየዉን ተስፋ ሰጪ ለዉጥ ይበልጡን ማስፋት፣ የስራ ዕድል ፈጠራን በማሳደግ የህዝባችንን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ይበልጡን አጠናክረን የምናስቀጥል ይሆናል ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በኃብት ስጦታ አንፃር ስንመለከት ኢትዮጵያ ለሁሉም የሚበቃ ኃብት እንዳላት እናውቃለን። በባሌ ዞን ከተለያዩ አመራሮች ጋር ያደረግነው ጉብኝት የመጨረሻ መዳረሻ አስደማሚው የፊንጫ ሀበራ ፏፏቴ ሆኗል። በግርማ የሚወርደው ፏፏቴ ወደ ሶፍኡመር የዋሻ ሥርዓት የሚደመረውን የወይብ ወንዝ የሚቀላቀል ነው። የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ የሚገኝበት ይኽ አስደናቂ ከባቢ ድንቅ የአዕዋፍ መገኛና በቅርቡ የዋሻ መስህብ የተገኘበት እንዲሁም የራፉ ውብ የዐለት ደን አቅራብያ የሚገኝ ነው። በቅርቡ በአካባቢው የሚገነባው ማረፊያ ሲጠናቀቅም ለጎብኝዎች የበለጠ ሳቢ እና ምቹ ይሆናል።
ባለፉት ሶስት ቀናት በጉብኝቱ የተሳተፉ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ያሉ ኃላፊዎች በጉብኝቱ የተመለከቱት የተፈጥሮ፣ የባሕል እና የሰው ኃብት ከፍ ያለ መነሳሳትን ፈጥሮላቸዋል። የጋራ ሥራችን እነዚህን ኃብቶቻችንን መግለጥ፣ ማሳደግ፣ በኃብቶቹ ላይ በመጨመር ቀጣዩ ትውልድ ችቦውን ተረክቦ እንዲቀጥል መሠረት መጣል ነው። ኢትዮጵያ በርግጥም የተትረፈረፈ ኃብት ምድር ናት። እንሰባሰብ። ለማለም እንድፈር። የጋራ ነጋችንን በጋራ እንገንባ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት የልማት ስራዎች ግምገማ መድረክ በቡድን ውይይት ተጠናክሮ ቀጥሏል!
የግምገማው መድረክ በበጀት ዓመቱ የሩብ ዓመት ስራዎች አፈፃፀም፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥና ማሳለጥ፣ የከተማውን ሰላም ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ማሳለጥ፣ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ፣ በባለፉት ሶስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ የተካሄዱ ዓለም አቀፍ፣ አህጉር አቀፍ;ሀገር አቀፍና ከተማ አቀፍ ኩነቶች አፈፃፀም፣ ወንድማማችነት እና የእህትማማችነት ዕሴትን በማጎልበት ፣ በጋራ ተግባቦት የነበሩ ስኬቶችን በሚያስቀጥል እና ጉለቶችን በማረም ለሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬቱ አስተዋፅዖ ማድረግ በሚያስችል ደረጃ ውይይት እየተደረገ ሲሆን ፤ የአመራሩን አቅም የሚያጎለብት የግንባታ መድረክ እንደሆነም ተመላክቷል።
የባሌ ድንቅ የተፈጥሮ ዉበት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ስራ ይበልጥ ተገልጦ ደምቆ ወጥቷል።… See more
በባሌ ዞን በነበረን የሁለተኛ ቀን ቆይታ የወልመል ወንዝ የመስኖ ልማት እና ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ጉብኝት ባሻገር ወደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሀረና ክላስተር በመገኘት ምልከታ አድርገናል። … See more
