FBC (Fana Broadcasting Corporate)
This is FBC's official Telegram channel. For more updates please visit www.fanabc.com
Ko'proq ko'rsatish183 268Obunachilar
+3824 soatlar
+4247 kunlar
+3 16530 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Обуначиларнинг ўсиш даражаси
Ma'lumot yuklanmoqda...
የግላኮማ ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው?
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ግላኮማ የአይን ህመም በአይን ነርቭ ላይ ችግር የሚያስከትል ሲሆን በአይን ውስጥ የሚገኘው ግፊት በመጨመሩ ምክንያት የሚከሰት ነው። የዚህ ግፊት መጨመር በአይናችን የምናያቸውን ምስሎች ወደ አንጎል የሚውስደውን የአይናችንን ነርቭ ይጎዳል፡፡ ይህም በቀጣይነት ቋሚ ለሆነ የአይን ብርሃን እጦት ይዳርጋል። ግላኮማ በሚጀምርበት ጊዜ የሚያሳየው ቀዳሚ ምልክት ወይም የህመም…
https://www.fanabc.com/archives/244104
👍 6
ማንቸስተር ሲቲ ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቸስተር ሲቲ ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 አሸንፏል።
12:30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ከሜዳው ውጪ የተጫወተው ሲቲ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
በዚህም አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት አንድ አድርጓል።
👍 43❤ 12😱 4👏 2🤔 1🤬 1
አርሰናል ቶተንሃምን በማሸነፍ የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናክሯል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠባቂው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰሜን ለንደን ደርቢ አርሰናል ቶተንሃምን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ሳካ፣ ሀቨርተስ እና ሆይቤር (በራሱ ግብ ላይ) አስቆጥረዋል፡፡
ቶተንሃምን ከሽንፈት ያላዳኑትን ግቦች ደግሞ ሮሜሮ እና ሰን አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እስከመጨረሻው የዋንጫ ተፎካካሪ የመሆን እድሉን ማጠናከር ችሏል፡፡
አርሰናል 80 ነጥቦችን በመያዝ በፕሪሚየር ሊጉ ደረጃ ሰንጠረዡ 1ኛ ላይ ሲቀመጥ ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በ76 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል፡፡
የከሸፈው ሴራ - ነገ ምሽት ይጠብቁን
👏 27😁 23❤ 3💩 3👍 1
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መስተዳድር ም/ቤት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 29ኛ መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በመጀመሪያ የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ አስመልክቶ የቀረበውን ሪፖርት ተመልክቷል፡፡ ምክር ቤቱ ባደረገው ግምገማ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በርካታ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን በጠንካራ ጎን ገምግሟል። ከለውጥ በኃላ…
https://www.fanabc.com/archives/244093
👍 34😱 2❤ 1
የሸዋል ዒድ በዓል የህዝቦችን አብሮነትና ወንድማማችነት እያጠናከረ ይገኛል- አቶ ኦርዲን በድሪ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ቅርስ የሆነው የሸዋል ዒድ በዓል የህዝቦችን አብሮነት እያጠናከረ መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ፡፡ የሸዋል ዒድ በዓል በአዲስ አበባ በተለያዩ ኩነቶች በድምቀት ተከብሮ ውሏል። በዓሉ አብሮነት እንዲጠናከርና ወንድማማችነት እንዲጎለብት ጉልህ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል።…
https://www.fanabc.com/archives/244088
👍 9❤ 5💩 3🥰 1😱 1
በኦሮሚያ ክልል 6 ነጥብ 2 ሚሊየን ተማሪዎች የት/ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሆነዋል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል 6 ነጥብ 2 ሚሊየን ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ መርሐ ግብር ተጠቃሚ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ “የህዝባችን ህልም ልጆቹን በነባሩና በመጪው የዓለም ሥርዓት ውስጥ ተፎካካሪ ሆነው ማየት ነው” ብለዋል። ለዚህም ልጆቹን ወደ…
https://www.fanabc.com/archives/244085
👍 17❤ 4💩 3👏 1🤔 1
"ዛሬ የ”ፅዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” የዲጂታል ቴሌቶን ተሳትፎ ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ። ለጋራ ጥቅም በጋራ ስንቆም ድንቅ እንሆናለን። እስከአሁን በ #ጽዱኢትዮጵያ ቴሌቶኑ ያልተሳተፋችሁ ዛሬ በቀሪዎቹ ሰዓታት፣ በመጪዎቹ ቀናት እና ሳምንታትም እንድትቀላቀሉ አበረታታችኋለሁ። በጋራ ትርጉም ያለው በጎ ተፅዕኖ መፍጠር እንችላለን።" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍 40❤ 10😁 7👏 2🤔 2
ማስታወቂያ
በ EthioDirect
ሀገር ቤት እጅግ ቅርብ ሆኗል!
**
በኢትዮ-ዳይሬክት መተግበሪያ
ከ5 - 1000 ዶላር በብርሀን ፍጥነት
ሀገር ቤት ላሉ ወዳጅ ዘመዶችዎ
በነፃ ይላኩ!
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
#CBE #ethiodirect #visa #mastercard #money #transfer #ethiopia
*****
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም App Store በማውረድ አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
👍 11
የደሴ ከተማ የልማት ሥራዎች በችግር ውስጥ ሆኖ አመርቂ ሥራ መሥራት እንደሚቻል ያሳያሉ – አቶ አደም ፋራህ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደሴ ከተማ የልማት ሥራዎች በችግር ውስጥ ሆኖ አመርቂ ሥራ መሥራት እንደሚቻል ያሳያሉ ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማእከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን የተመራ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ቡድን በደሴ ከተማ የተከናወኑ የልማት…
https://www.fanabc.com/archives/244079
👍 24❤ 5😁 4