cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

፮ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

ይህ የ፮ ኪሎ ግቢ ጉባኤ ህጋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው። This is the official Channel of 6 kilo Gibi Gubae. በግቢ ጉባኤው ላይ ያለዎትን አስተያየት ወይም ጥያቄ በ @fesehatsion12 ወይም @Hoping7 ላይ ይላኩልን።

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
2 108
Obunachilar
+124 soatlar
+227 kunlar
+11430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል እና የማኅበረ ቅዱሳን ፴፪ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሰላም አደረሰን! "ግቢ ጉባኤያት የአገልግሎት መሠረት" በሚል መሪ ቃል እሑድ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከ7፡00 ሰዓት ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በመገኘት የማኅበራችንን የምሥረታ በዓል በጋራ እናክብር።
Hammasini ko'rsatish...
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል እና የማኅበረ ቅዱሳን ፴፪ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሰላም አደረሰን! "ግቢ ጉባኤያት የአገልግሎት መሠረት" በሚል መሪ ቃል እሑድ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከ7፡00 ሰዓት ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በመገኘት የማኅበራችንን የምሥረታ በዓል በጋራ እናክብር።
Hammasini ko'rsatish...
"ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም"            ቅ/ያሬድ እንኳን አደረሳችሁ? ዓመታዊ የእመቤታችንን ልደት በደመቀ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅታችንን አጠናቀናል። ስለሆነም ሁላችሁም ማግሰኞ ግንቦት 6 ቀን ምሽት 11፡00 ላይ በቅ/ሥላሴ ካቴደራል ትልቁ አዳራሽ እንድትገኙ ስንል አደራ እንላለን!! ቀኑን ግንቦት 6 ያደረግነው ክፍለ ሃገር በዓል ለማክበር የሄዳችሁ ሰዎች ተመልሳችሁ በዓሉ ላይ እንድትገኙ ብለን ስለሆነ ሁላችሁም በዕለቱ እንድትገኙ ስንል አደራ እንላለን!! ፬ ኪሎ ጊቢ ጉባኤ
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም የ6ኪሎ ግቢ ጉባዔ ተማሪዎች እንደሚታወቀው ይህ ጥንታዊ የሆነ ግቢ ጉባዔ የራሱ የሆነ የ YouTube channel መክፈቱን በይፋ ገልጿል። ስለሆነም ለጓደኞቻችሁ ፣ ለምታቁት ሰው ሊንኩን በመላክ #SUBSCRIBE እንዲያደርጉ ንገሯቸው። ይህንንም በማረግ ያሳደገችንን ግቢ ጉባዔ እናግዛት።
📌ኦርቶዶክሳዊ ትምህርተ ወንጌሎችን፣
📌የበዓላት ወረቦችን፣ 
📌ዝማሬዎችን፣ 
📌ምክረ አበውን እንዲሁም ሌሎች በስድስት ኪሎ ግቢ ጉባኤ የሚዘጋጁ ምስል ወ ድምፆችን ያገኙበታል።
ስለዚህ YouTube ላይ ገብታችሁ @6kilogbigubae ብላችሁ Search ማድረግ ወይም ደሞ ይህንን https://youtube.com/@6Kilogbigubae?si=JPyZjTwMFI-i2HxR መጠቀም ትችላላችሁ። ፮ ኪሎ ግቢ ጉባኤ                     @SidistKiloGibiGubae                    
Hammasini ko'rsatish...
"ዘወትር በንፁሕ ሕሊና እየሆናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ።" መ.ቀሌሜንጦስ 12:25 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ዘወትር ዓርብ በጋራ ተሰብስበን የአንድነት ጸሎት የምናደርስበት መርሐግብራችን ነገም እንደተጠበቀ ነው‼️ ስለዚህም ሁላችንም ከጓደኞቻችን ጋር ተቀሳቀሰን በመገኘት የጸሎት መርሐግብሩ ተሳታፊሆች እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መልካም ፈቃዱ ይሁንልን! 👥ቦታ: ቅዱስ ማርቆስ ወሚካኤል ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ⏰ሰዓት: ጠዋት 11:50 ፮ ኪሎ ጊቢ ጉባኤ
Hammasini ko'rsatish...
የእመቤታችንን ልደት  ከግቢ ጉባኤያችን ጋር    ልደተ እግዝእትነ ማርያም መዝ. 86፥1 “መሠረታቲሃ ውስተ አድባር  ቅዱሳን" መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ  ለማርያም   |በእመቤታችን ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ| ውድ የግቢ ጉባኤያችን ተማሪዎች በመጀመሪያ ​​እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን  የእናታችንን በዓለ ልደት በማሰብ ነገ በዕለተ ሐሙስ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በመንበረ ልዑል ቅዱሰ ማርቆሰ ወሚካኤል ቤተክርሰቲያን አውደምህረት እናት ግቢ ጉባኤያችን  መርሐ ግብር አዘጋጅታ ልጆቸ ኑ  እያለች መልዕክቷን ታሰተላልፋች። ልደትሽ ልደታችን ነው! ሰዓት ፡ 11:00 ጀምሮ ቦታ : መንበረ ልዑል ቅዱሰ ማርቆሰ ወሚካኤል  አውደምህረት የ፮ ኪሎ ግቢ ጉባዔ
Hammasini ko'rsatish...
ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡- #ሰኞ #ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ #ማክሰኞ #ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 #ረቡዕ #አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ #ሐሙስ #አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ #አርብ #ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ #ቅዳሜ ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ #እሁድ #ዳግም_ትንሳኤ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፡ በዓቢይ ኃይል ወስልጣን ። አሰሮ ለሰይጣን፡ አግዓዞ ለአዳም ። ሰላም፡ እምይእዜሰ ። ኮነ ፡ፍስሐ ወሰላም፡፡ እነሆ ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩር ሆኖ ከሙታን ተነስቷል፡1ኛ ቆሮ 15÷20። እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤዉ በሰላም አደረሳችሁ እያልን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የትንሳኤ ሎተሪ ትናንት ምሽት በይፋ መውጣቱ የታወሳል። በስፍራው ተገኝተው መካታተል ላልቻሉ አባላትም እድለኛ ቁጥሮችን እነሆ ብለናል። 1ኛ እጣ 1143 በገና 2ኛ እጣ 0265 Smart phone 3ኛ እጣ 3565 Air pode 4ኛ እጣ 1303 ድርሳነ ሚካኤል 5ኛ እጣ 0112 ንጥል የማስተዛዘኛ እጣዎቸ 6ኛ እጣ 0697 7ኛ እጣ 4026 8ኛ እጣ 0141 9ኛ እጣ 2286 10ኛ እጣ 0650 ከ6-10 ያሉት ሁሉም የወርሃዊ የድምጽ ጥቅል እድለኞች ናቸው። እድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ። በ @Mi121919 ላይ በማሳወቅ ሽልማቱን መቀበል ትችላላችሁ። ትኬቱን በመሸጥና እና በመግዛት ለመርኃ ግብሩ መሳካት ላበረከታችሁች ተሳትፎ በግቢ ጉባኤው ስም ከልብ እናመሰግናለን። የ2016 ዓ.ም የትንሳኤ በዓል እዘጋጅ ኮሚቴ
Hammasini ko'rsatish...
✥✥✥ መቃብሩን አትክፈቱ❗️❗️❗️❗️ ✥✥✥ 👉 በብዛት የክርስቶስን ትንሣኤ ለመግለጽ የሚሣሉ ሥዕላት መቃብሩን ከፍቶ(ፈንቅሎ) ሲነሣ ወይም መላእክት የመቃብሩን ደጃፍ ከፍተውለት ሲነሣ ኣድርገው ነው የሚሣሉት ይህ በመጽሓፍ ቅዱስ ከተገለጸው ጋር የሚጋጭ ነው። 👉 ጌታችን የተነሣው መግነዝ ፍቱልኝ፥ መቃብሩን ክፈቱልኝ ሳይል ነው። ➛ ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንደገለጸልን እሑድ በማለዳ ወደ ጌታ መቃብር ሽቱ ለመቀባት የሄዱት ሴቶች «ድንጋዩን ከመቃብሩ ደጃፍ ማን ያንከባልልልናል?» የሚል ጥያቄ ኣሳስቧቸው እንደነበር ይገልጽልናል። ➛ ይህን ጥያቄ ያቀረቡት “ ድንጋዩ እጅግ ትልቅ ነበርና ” በማለት የጥያቄያቸው መነሻ የሆነውን ምክንያት ያስረዳናል። {ማር ፲፮÷፩-፮፡፡} ➛ የእነዚህ ቅዱሳን ኣንስት (ሴቶች) ላሳሰባቸውን ጥያቄ መፍትሔ እንዴት እንዳገኘ ሌላኛው ወንጌላዊ ማቴዎስ በወንጌሉ እንዲህ ባለ መልኩ ይገልጽልናል፦ ➛ «በሰንበትም መጨረሻ ( ሰንበት ያለው ቅዳሜን ነው) የመጀመሪያው ቀን (የመጀመሪያ ቀን ያለው የሥነፍጥረት መጀመሪያ የሆነች እሁድ ነው) ሲነጋ፥ መግደላዊት ማርያምና ሁለተኛይቱ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ፡፡ እነሆም የጌታ መልአክ ከሰማይ ስለወረደ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ ቀርቦም ድንጋዩን ኣንከባሎ በላዩ ተቀመጠ፡፡ መልኩም እንደ መብረቅ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበረ፡፡ ጠባቆቹም እርሱን ከመፍራት የተነሣ ተናወጡ፡፡ እንደ ሞቱም ሆኑ፡፡ መልኣኩም መልሶ ሴቶቹን ኣላቸው፥ እናንተስ አኣትፍሩ፤ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንደምትሹ ኣውቃለሁና፤ እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ። » {ማቴ ፳፰÷፩-፮፡፡} ➛ ጌታችን መቃብሩ ከፍቶ ተነስቶ ቢሆንስ ኖሮ መልኣኩ ሴቶቹ ወደ መቃብሩ ውስጥ እንዲመለከቱ መቃብሩን ከፈተው ባልተባለ ነበር። ጌታችን በዝግ መቃብር ከተነሣ በኋላ ባዶ የነበረውን መቃብር የከፈተው ይህ የጌታ መልአክ ነው፡፡ ➛ መልኣኩ መቃብሩን ለምን ከፈተው ቢሉ፦ የመጡ እነዚህ ሴቶች የጌታችንን መነሣት እንዲያውቁ እና ትንሣኤውን እንዳይጠራጠሩ ነው፡፡ ኋላም ደቀ መዛሙርቱ ትንሣኤውን ያመኑት መልኣኩ ወደ ከፈተው መቃብር ገብተው መግነዙን ካዩ በኋላ ነው። ዮሐ ፳፥፯። ➛ ጌታችን መቃብሩን ክፈቱልኝ ሳይል ለምን ተነሣ ቢሉ፦ ሞቱ በፈቃዱ እንደሆነ ትንሣኤውም በሥልጣኑ መሆንን ለማስረዳት ነው። ኣንድም፦ ሥግው ቃልን በርቀቱ ቢያጸናው ነው። ይኸውም በኅቱም ድንግልና መወለዱ፣ በባህር ላይ መራመዱ፣ በተዘጋ ደጃፍ ሳይከፈት መግባቱ፣ መቃብርም ክፈቱልኝ ሳይል መነሣቱ ጌታ ምንም እንኳን ግዝፍ የሆነ ሥጋን ቢነሣም በመለኮትነቱ ግን ረቂቅ ነው በተዋሕዶ የቃል ርቀቱ ለሥጋ ገንዘቡ በመሆኑ (ሥግው ቃልን በርቀቱ ቢያጸናው ) በድንግልና ለመወለድ የማይከልክለው፣ ባህር የማያሰጥመው፣ ደጃፍ ለመግባት የማይከለክለው፣ ለትንሣኤውም መቃብር መክፈት የማያስፈልገው መሆኑን ኣስረዳ። 👉 ስለዚህ ቅዱሳን ሥዕላት በመሣል ቤተክርስቲያንን የምታገለግሉ ይህንን መጽሓፍ ቅዱሳዊ ትምህርትን መሠረት ኣድጋች ብትሥሉ (መቃብሩን ኣትክፈቱ)፤ ምዕመናንም ይህን በመረዳት በቤታችንም ሆነ ወደ ቤተክርስቲያን የምናመጣቸውን ሥዕላትን ትክክለኛ መልእክት የሚያስተላልፍ ከቤተክርስቲያን ትምህርት ጋር የማይጋጭ መሆኑን በማገናዘብ ቢሆን ፤ እንዲሁም በሶሻል ሚዲያ የምናቀርባቸው ሥዕላትንም ይህን ያማከለ ሊሆን ይገባል። ይቆየን መልካም በዓል ይሁንላችሁ ❗️❗️❗️
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም ለኩልክሙ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ። በመስቀሉ ሰላምን አደረገ ትኩረት የሚሻ መልዕክት እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው ዋይዜማ  በሰላም አደረሳችሁ እግዚአብሔር ቢፈቅድ የትንሣኤው መርሐግብራችን ለማክበር አጭር  ሰዓታት ቀሩን።  የዘንድሮው መርሐግብራች ከሌላው ዓመት በተለየ ቀደም ተብሎ  ከቀኑ 10:30 ላይ የሚጀመር ! ይህም የሆነበት ምክንያት መርሐግብራችንን ቶሎ ጨርሰን ወደ አገልግሎት  ለመግባት እና ቅዳሴ ለማስቀደስ በሚል እሳቤ ነው። ቦታ:መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ አዳራሽ ሰዓት:10:30  ( አደራ ሰዓት ይከበር  የሚጀመረው ontime ነው።) ለሚመለከተው ሁሉ share አድርጉ! እና ተቀሳቅሳችሁ ተገኙ! ፮  ኪሎ ግቢ ጉባኤ
Hammasini ko'rsatish...