cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qilingÂť, bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Brave Generation❤💪

Let's fall forward For any comment🤓 @Yilo15

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
211
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

#ማምሻ_ስምንት ወድጄሽ ነዉ? ወይስ ወድጄሽ ነው። ሁለት ግራ የሚየጋቡ ሀሳቦች። ሁለት ያልተረጋገጡ ዕዉነታወች። በጥያቄና መልስ፣ጠያቂዉም ተጠያቂዉም አንድ በሆነበት። በማመን እና አለማመን፣አማኙም አላማኙም አንድ ነፍስ በሆኑበት አለም ዉስጥ ተደንቅሮ የቀረ ምትሀታዊ ስሜት። @yilo15 @bravegenbyyil
Hammasini ko'rsatish...
#ማምሻ_ሰባት ቲሽ....ግጥም....ምናባቱ ቅኔ...ምናባቱ ዜማ ለኔ ካልደረሰ ዉስጤን ካላሰማ ምናባቱ ቅኔ...ምናባቱ ዜማ ዛሬም ካንቺዉ ጋር ነኝ...ዉስጤ ላንቺ ሲሆን የኋሊት መፍሰስ አይታክተዉም። ቢገባሽ ብዬ ዛሬም ከቃላት ጋር እታገላለሁ። ግጥሙን ለመግጠም እድሀለዉ፤ቅኔን ለመቀኘት እዳክራለሁ፤ዜማን ላዜምልሽ ጉሮሮዬን እስላለሁ። ግና ሁሉም አቅም ያጡብኛል። ከልቤ ወተዉ ከብዕሬ እና ከአፌ ደጃፍ መድረስ ህልም ይሆንባቸዋል። ታዲያ ቲሽ..... አያንሳቸዉም @yilo15 @bravegenbyyil
Hammasini ko'rsatish...
Watch "Intro video #yilgraphis" on YouTube https://youtu.be/Uwun-O2wkVc
Hammasini ko'rsatish...
Intro video #yilgraphis

#graphics_design #videoediting #logodesign @yilgraphics +251 921 09 92 64

yil graphics #graphics_design_banner_logo_brochure_video_editing_business_card_any_advertisement_work_furniture_interior_design 0921099264 Group link https://t.me/yilgraphics https://t.me/yilgraphics
Hammasini ko'rsatish...
yil graphics

#graphics_design_banner_logo_brochure_video_editing_business_card_any_advertisement 0921099264 0954710579 Group link

https://t.me/yilgraphics

❗#የጋዳፊ_ትንቢታዊ_ንግግር ⤵️ "እኔ ወደየትኛውም ሃገር ተሰድጄ ወይም ጥገኝነት ጠይቄ አልሄድም። የተወለድኩት እዚሁ ነው። የምሞተውም በዚሁ በሃገሬ በሊቢያ ነው። እኔ ወደ ስልጣን ስመጣ ይህ ሃገር ሙሉ በሙሉ በረሃ ነበር። እኔ ግን ሁሉም እፅዋት እንዲበቅልበት አድርጌ ወደ ልምላሜ ቀይሬዋለሁ። ይህችን ሃገር ከራሷ ዜጎች በላይ ማንም አይወዳትም። አሜሪካውያንና አውሮፓውያን እንወዳችኋለን ቢሏችሁ አትመኗቸው። ተጠንቀቁ! እነሱ የሚፈልጉት ሃብታችሁን ነው። እነሱ የሚወዱት የዚህችን ሃገር ነዳጅ እንጅ ህዝቦቿን አይደለም።ዛሬ እናንተ እኔን ትወጉ ዘንድ እያነሳሷችሁና እያገዟችሁ ነው። ነገር ግን እናንተ ከኔ ጎን ቆማችሁ እነሱን ብትዋጉ ብልህነት ነው። ምክንያቱም ምዕራባውያን አሁን እየወጉ ያሉት የወደፊት ተስፋና ራዕያችሁን ነው። ለመላው ሊቢያውያን ማስተላለፍ የምፈልገው አንድ መልእክት አለኝ። ዛሬ ምዕራባውያን እናንተ እኔን ትወጉbዘንድ እያስታጠቋችሁና እየደገፏችሁ ነው። ነገርግን እውነት እላችኋለሁ በኋላ ለዚህ ጥፋት በምትከፍሉት መራራ ዋጋ እጅግ ትጎዳላችሁ። ለእናንተ ለአሜሪካኖችና ለአውሮፓውያንም ልነግራችሁ የምፈልገው ነገር አለኝ። እናንተ ትገሉኛላችሁ። ነገር ግን እኔ ከሞትኩ በኋላ ለምትጋፈጡት ማቆሚያ የሌለው የሽብር ጦርነት ራሳችሁን አዘጋጁ። እናንተ ከድንቁርናችሁ ሰመመን ከመንቃታችሁ በፊት አሸባሪዎች ጦርነቱን እደጃችሁ ድረስ ያመጡታል።" ጋዳፊ በአሜሪካ ፊትአውራሪነትነና በምዕራባውያን ደጋፊነት በተከፈተባቸው ጦርነት ከመገደላቸውና ሊቢያም አሁን ባለችበት ሁኔታ ከመፈራረሷ በፊት ጋዳፊ የተገደሉት በሃገር ቤት ለዜጎቻቸው፣ በዓለም መድረክም ለተቀረውbዓለም አንባገነን ስለነበሩ ነበር ከተባለና የጋዳፊ መንግስትም ለውድቀት ሃገሪቱም ለመበታተን የበቃችው መንግስታቸው አንባገነን ስለነበረ ብቻ ነው ወደሚለው ከእውነታው ያፈነገጠ መደምደሚያ የምንደርስ ከሆነ "አንባገነን" እና "ዴሞክራሲያዊ" የሚሉት ቃላት ፍች በአተረጓጎም ቦታ ተቀያይረዋል ማለት ነው። እስኪ ጋዳፊ በስልጣን ላይ በነበሩበት ዘመን ሊቢያውያን ያገኙ የነበሩትን የዜግነት ጥቅም አንድ በአንድ እንይና ኮለኔል ጋዳፊ በመጨረሻው ዘመናቸው የተናገሩትን ትንቢታዊ መልዕክት፣ የአሜሪካኖች በሰው ሃገር ጣልቃ የመግባት ውጤት ከሆነችው እና ዛሬ ብትንትኗ ወጥቶ ዜጎቿ ቁራሽ ዳቦ ብርቅ እንዲሆንባቸው ከተደረገችው፣ ለአለም ህዝቦች በተለይም ለመሃከለኛው ምስራቅ ሰላም ስጋት የሆኑ ሽብርተኞች መፈልፈያ ከሆነችው ከዛሬዋ ሊቢያ ጋር እናስተያየውና የራሳችንን ፍርድ እንስጥ… 1 #በጋዳፊ ዘመን በሊቢያ የኤሌትሪክ ሃይል ከክፍያ ነፃ ነበር። የኤሌትሪክ ፍጆታ ቢል ብሎ ነገር አልነበረም። 2 #ማንኛውም ሊቢያዊ የባንክ ብድር ከፈለገ ከወለድ ነፃ በ 0% interest የፈለገውን ገንዘብ መውሰድ ይችል ነበር። 3 #በሊቢያ የመኖርያ ቤት ማግኘት ከሰብዓዊ መብቶች እንደ አንዱ ይቆጠር ነበር። 4 #በሊቢያ ህክምናና ትምህርት በነፃ ይሰጥ ነበር። ከጋዳፊ በፊት 25% የነበረው የተማረ ሰው ሃይል መጠን በእሳቸው ግዜ 83% ደርሶ ነበር። 5 በሊቢያ በግብርና ስራ ላይ መሰማራት የሚፈልግ የእርሻ መሬት፣የግብርና ግብአት ማቀነባበሪያ ቤት፣መሳርያዎችና የተለያየ ቁሳቁስ ከመንግስት በነፃ እንደ ማበረታቻ ይሰጠው ነበር። 6 በሃገር ውስጥ የከፍተኛ ትምህርትና ህክምና ማግኘት ላልቻሉ ዜጎች እነዚህን ወደውጭ ሃገር ሄደው ያሟሉ ዘንድ መንግስት ድጎማ ያደርግ ነበር። 7 ሊቢያውያን አዲስ መኪና ሲገዙ የወጭውን 50% በመንግስት ይደጎሙ ነበር። 8 በሊቢያ የነዳጅ ዋጋ 0.14 ዶላር በሊትር ነበር። 9 ሊቢያ ምንም አይነት የውጭ ብድር ያልነበረባት ሃገር ከመሆኗም በላይ የመንግስት የመጠባበቂያ ካፒታል መጠኗም 150 ቢሊየን ዶላር ነበር። 10 በሊቢያ አዲስ ተመራቂ የሆነ ዜጋ እንደተመረቀ ስራ ካላገኘ በሙያው ቢቀጠር ያገኝ የነበረውን ደሞዝ 50% ያህል ስራ እስኪቀጠር መንግስት ይከፍለው ነበር። 11 ሊቢያ ከነዳጅ ታገኘው ከነበረው ገቢ ግማሽ ያህሉ ወደ እያንዳንዱ ሊቢያዊ የባንክ ሂሳብ ፈሰስ ይደረግ ነበር። 12 በሊቢያ አዲስ ህፃን የምትወልድ ሴት ከመንግስት 5ሺህ ዶላር በሽልማት መልክ ይሰጣት ነበር። 13 በሊቢያ በቁጥር 40 የሚደርስ ሙልሙል ዳቦ ዋጋው የአንድ ዶላር 15 ሳንቲም አካባቢ ነበር። 14 ከሊቢያ ዜጎች 25% ያህሉ የዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ማግኘት ችለዋል። 15 ጋዳፊ በዘመናቸው በዓለም 1ኛ የሆነውንና ሰው ሰራሽ ወንዝ በመባል የሚታወቀውን ፕሮጀክት በመስራትና በእያንዳንዱ በረሃማ ከተሞች ውሃ በየቤቱ እንዲዳረስ ያስቻለ ስራ ሰርተዋል። እንግዲህ ጋዳፊን ለሞት፣ ሃገሪቱን ደግሞ ለማያባራ የእርስ በእርስ ጦርነትና መበታተን የዳረጋት የአንባገነንነት መገለጫ ከላይ የተገለፀው ትሩፋት ከነበረ፣ የሰው ሃገር ሉአላዊነት ምእራባዊያን በፈለጉ ሰዓት እየደፈሩ፣መንግስታትና ህዝቦችን እየከፋፈሉ፣ ህፃናትን ሴቶችንና አረጋውያንን ለማያባራ ሰቆቃ እየዳረጉ ያሉትና ራሳቸውን የዴሞክራሲ መሲሆች አድርገው የሚቆጥሩት አሜሪካውያን እና አውሮፓውያን መገለጫቸው ምን ይሆን…⁉️⁉️ እኛስ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ማድረግ አለብን❓ ሁላችንም ስለእውነት ቆም ብለን እናስብ! 🇪🇹 ፈጣሪ ለኢትዮጵያ ሰላሙን ያምጣላት 🙏🙏 በሳሙኤል ግርማ
Hammasini ko'rsatish...
ስለ ድክመትህ ካሰብክ ተራራ የሚያህል ጎዶሎ ነገር ልታወጣ ትችላለህ፤ እሱ ምን ጎደለው የምትለውም ሰው ካንተ የባሰ ሰማይ የሚነካ ጉድለት ሊኖረው ይችላል። አየህ ስለ ጥንካሬህ ብታስብ ግን ይቺ ምድር የምትፈልገውን ነገር ሁሉ ላንተ ለመስጠት ትዘጋጃች፤ በምንም አይነት ከባድ ጨለማ ውስጥ ብትሆን እንኳን ፍንጣቂ ብርሀን ማየት ከቻልክ ሁሉም ነገር ቀላል ይሆናል።!
Hammasini ko'rsatish...
እዮብ_መኮንን ደብዝዘሽ መልክን የሻረዉ አንቺ ጋር ምን ተሻለው ከሩቅ ሳትስቢ፣ አየሁ ልቤ ስትገቢ ካንቺ በላይ ቆንጆ ሞልቶ ያዉቃል ልቤም ቀርቦም አይቶ ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆዎቹን አስናቅሻቸው ካንች በላይ እዉቀታቸው ስቄም ነበር በቀልዳቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው መልክን የሻረዉ አንቺ ጋር ምን ተሻለው ከሩቅ ሳትስቢ፣ አየሁ ልቤ ስትገቢ ካንቺ በላይ ቆንጆ ሞልቶ ያዉቃል ልቤም ቀርቦም አይቶ ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆዎቹን አስናቅሻቸው ካንች በላይ እዉቀታቸው ስቄም ነበር በቀልዳቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው ለኔው ጥቅም በኔው ሰው ተመክሬ አላውቅም አብልጬ፣ ከልብ አምርሬ አሁን ለምን ገባኝ፣ ባንቺ ሲመከር ያሉግንን ብለሺኝ፣ የምፍጨረጨር ከኔ ነው፣ ወይ ካንቺ ነው ልቤን ለጅሽ፣ የሰጠነዉ ማኩረፍ የኔ ነበር አልሸፋፈንኩም ካንቺ ጀምሬ ግን አልተቀየምኩም ምንድነው ብርቅ ሆኖ የሚያስወድደኝ ሁሉሺን እንዳደንቅ የሚያስገድደኝ የት ብለው፣ የት ቢሄዱ መስፈርት የለም፣ ከወደዱ መልክን የሻረዉ አንቺ ጋር ምን ተሻለው ከሩቅ ሳትስቢ፣ አየሁ ልቤ ስትገቢ ካንቺ በላይ ቆንጆ ሞልቶ ያዉቃል ልቤም ቀርቦም አይቶ ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆዎቹን አስናቅሻቸው ካንቺ በላይ አውቀታቸው ስቄም ነበር በቀልዳቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው ተቀይሩዋል አይኔ፣ ወዷል መልክሺን ስመዝኑሽ ያደንቁዋል፣ ሲቀርቡሽ አንቺን ቆንጆም ዉብም ለኔ ያንቺ አይነት ብቻ ባይም ልቤ አያምንም፣ እንዳለሽ አቻ የት ብለው፣ የት ቢሄዱ መስፈርት የለም፣ ከወደዱ ተቀይሯል አይኔ፣ ወዷል መልክሺን ሲመዝኑሽ ያደንቋል፣ ሲቀርቡሽ አንቺን ቆንጆም ዉብም ለኔ ያንቺ አይነት ብቻ ባይም ልቤ አያምንም፣ እንዳለሽ አቻ ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆወቹን አስናቅሻቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆወቹን አስናቅሻቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው ግን በምን በለጥሻቸው ቆንጆወቹን አስናቅሻቸው ዝምታሽ በለጣቸው ደብዝዘሽ አጋለጥሻቸው ግምም=ኤልያስ መልካ ዜማ=ኤልያስ መልካ ቅንብር=ኤልያስ መልካ
Hammasini ko'rsatish...
የማለዳ ማ ስታወሻ #119 . ያ ዕለት ከአንደበትሽ የወጡት የተበታተኑና ፍቺያቸው የራቁ ቃላት የመጨረሻ ንግግርሽ መሆኑን ባውቅ ጆሮዬን ከአንደበትሽ አልነቅልም፣ በዚያች ቅጽበት ምድር ብትንቀጠቀጥ፣ሰማይ ቢደረመስ፣ከዋክብት ቢረግፉ የመጨረሻ ንግግርሽን ከመሳት የበለጠ አያ ስፈሩኝም ነበር። . ያ ዕለት ዓይኖችሽ ከሩቅ ሲከተሉኝ የስንብት ዕይታ መሆናቸው ቢገባኝ አንገትሽ ሥር ገብቼ የልብ ምቴን እስክትሰሚው አቅፌ እሰናበትሽ ነበር። በወግ የመሰናበትን ትርጉም ያስተማረኝ ያለመሰናበት ፀፀት ነው። . ያ ዕለት በሕይወታችን አንዱ አስከፊው ግን የምናልፈው ቀን መሰለኝ። አቃጥሎ የሚሰወር ክቡድ ድባብ የተጠናወተው ቀን መሰለኝ። ታገልኩ። ታተርኩ። በዚያ ትግል ውስጥ የሚወዱትን የመሰናበት ወግ አመለጠኝ። እየቆየ የሚጠዘጥዝ ጠባሳ፣ ቀን እየጠበቀ የሚያገረሽ ደዌ ተነቀስኩ። "ሕይወት ይቀጥላል" ብለው ሲያፅናኑ "መቀጠሉ ያማል" የሚል ምላሽ ፈጠርኩ። . #ፈይሠል_አሚን . @huluezih @huluezih
Hammasini ko'rsatish...
ሳልነግርሽ… (በላይ በቀለ ወያ) . . አፍቅሬ እንዳጣሁሽ… በነብያቶች አፍ፣ ፍልስፍና ሚመስል ፣ ትንቢት ተነገረ ታምር የሚሰራ… ጎትቶ ጎትቶ ፣ በመርፌ ቀዳዳ ፣ ግመል አሻገረ ግመሉ ሲሻገር ፣ መርፌው ተሰበረ፡፡ በሰባራ መርፌ…. ፍቅርሽን ከፍቅሬ ፣ ባንድነት ልሰፋ ይኸው እደክማለሁ… ክር ሆነሽ እያጠርሽ ፣ ኖራለሁ ስለፋ፡፡ …………………………………. ሳልነግርሽ… የኔ አለም ያላንቺ ፣እንደሆነ ራቁት ባንቺ እንደነበር ፤ ቀንና ሌሊቴ የሚፈራረቁት፡፡ እንደተለየሽኝ … አለም ባዶ ሆና ፣ መኖር እንዳስጠላኝ ፍቅርሽ እከክ ሆኖ… በልቤ ተተክሎ ፣ ነፍሴን እንደበላኝ፡፡ ………………………………… ሳልነግርሽ…. የነብያት ትንቢት ፣ በኔ መፈፀሙን ‹‹ታምሪያለሽ ›› እያልሁኝ ፣ ‹‹ተአምር ›› ማክተሙን የተለየሽኝ ለት… ምፅአት መምጣቱን ፣ የኔ አለም መቆሙን፡፡ ………………………………………… ሳልነግርሽ…. ካጣሁሽ በኋላ…. ባለፍኩት ጭንቅ ዓለም ፣ የስቃዬን መአት አፍቅሮ ማጣት ነው… በሰባራ መርፌ፣ እውነትን መስፋት ነው ፣ ለካንስ ምፅአት፡፡ @bravegenbyyil
Hammasini ko'rsatish...
የኦፕራ ዊንፍሬ የቢዝነስ ምክሮች መቼም ብዙዎቻችን ኦፕራ ዊንፍሬን እናውቃታለን ብዬ እገምታለሁ፡፡ ኦፕራ የቶክ ሾው አቅራቢ፤ የቢዝነስ ፈጣሪ፤ ተዋናይ፤ ፕሮዲውሰር፤ የመፅሄት ባለቤት ናት፡፡ ዛሬ የኦፕራ ሃብት ከ22 ቢሊየን ዶላር በላይ ይገመታል፡፡ ኦፕራ ዊንፍሬ ከምትሰራቸው ስራዎች ወይም ቢዝነሶች መካከል • ኦፕራ.ኮም የተባለ ዌብ ሳይት አላት፡፡ ዌብ ሳይቷ በወር ከ6 ሚሊየን በላይ ሰዎች ይጎበኙታል፡፡ • ኦ ዘ ኦፕራ ሜጋዚን ( O The Oprah Magazine) የተባለ ወርሃዊ መፅሄት ታሳትማለች። መፅሄቱ ዲጂታል ሆኖ እና ታትሞ ይሸጣል፡፡ • ኦፕራ ዌይት ዋቸርስ የተባለ የምግብ አምራች ኩባንያ ውስጥ ወደ 430 ሚሊየን ዶላር የሚገመት ሼር ያላት ሲሆን ትሩ ፉድ ኪችን የተባለ ብዙ ቅርንጫፎች ያሉት ሬስቶራንትም ላይ ኢንቨስት አድርጋለች። ኦፕራ ለስኬት ያበቋትን ሚስጥሮች እንደዚህ አካፍላለች፡፡ 1. ካልተሳሳታቸሁ አልሰራችሁም ማለት ነው ኦፕራ መውደቅ/መሳሳት ያለ ነው ስለዚህ መውደቅን አትፍሩ ትላለች፡፡ ውድቀት ወይም ኪሳራ አለ ብላ አታምንም ይልቁንስ በዛ ውስጥ የምናገኘው አዲስ እውቀት እና ጥበብ ይበልጣል ብላ ታምናለች። ያደናቅፋችሁ ድንጋይ ካለ ከወደቃችሁበት ስትነሱ ድንጋዩን ረግጣችሁ ወደ አላማችሁ ገስግሱ፡፡ 2. ክፉን ወደ መልካም ለመቀየር ሞክሩ ኦፕራ በጣም ድሃ ከሚባል ቤተሰብ የተገኘች ሴት ናት፤ በልጅነቷ የመደፈር ጥቃት ደርሶባታል፤ በ14 አመቷ ልጅ ብትወልድም ሞቶባታል። እነዚህን መጥፎ ገጠመኞቿ የሌሎች ሰዎችን ችግር እና መከራ በቀላሉ መረዳት እንድትችል እንዳደረጓት ታምናለች። ይህም ቶክ ሾው ስትሰራ በቀላሉ ከተመልካቾች እና ከእንግዶች ጋር መግባባት እንድትችል አድርጓታል፡፡ ስለዚህ ሰዎች በህይወታችው ክፉ ነገር በሚያጋጥማቸው ጊዜ በፍራቻ ከመዋጥ ወይም ከመደንገጥ ይልቅ ነገሩን ወደ መልካም ነገር ለመለወጥ እንዲጥሩ ትመክራለች፡፡ 3. ህይወት እና ቢዝነስ ከትምህርት ቤት ይለያል ትምህርት ቤት ስንማር ስኬት የሚገኘው አስተማሪዎቻችን እና ቤተሰቦቻችን የሚነግሩንን በማዳመጥ እና የነሱን መንገድ በመከተል፤ በመታዘዝ እንደሆነ ይነገረናል፡፡ ከትምህርት ቤት ስንወጣ ግን በግል ህይወታችንም ሆነ በቢዝነሱ አለም አዲስ ነገሮችን መሞከር እና መፍጠር ይጠበቅብናል፡፡ ኦፕራ የመጀመሪያ የቴሌቪዥን የዜና አንባቢነትን ስራ ስታገኝ ሌሎች አንባቢዎች እንደሚያደርጉት ኮስተር ብላ ዜናውን ማንበብ ላይ አላተኮረችም፡፡ ይልቁንም ዜናውን በስሜት ተውጣ እና የሌሎች ሰዎ ስሜትን እያሰበች ነበር የምታቀርበው፡፡ ከሌሎች አንባቢዎች ለየት ያለውን አቀራረቧን ተመልካቾች ወደዱላት፡፡ ቶክ ሾው ስትጀምርም ከነበሩት ቶክ ሾዎች በተለየ ሁኔታ ፖሎቲካ፤ ጤና፤ መንፈሳዊ ህይወ፡ እና መሰል ነገሮች የሚነሱበት ቶክ ሾው ነው የጀመረችው፡፡ 4. እድል ማለት በቂ ዝግጅት ካደረግን በዃላ የሚያጋጥሙንን እድሉ በአግባቡ መጠቀም ነው ብላ ታምናለች የቢዝነስ ሰው ብዙ ደንበኞችን በአንዴ ማፍራት ወይም ትልቅ ኮንትራ ማግኘትን ተስፋ ያደርጋል፤ ይመኛል፡ ኦፕራ እንደምትለው ግን ዝም ብለን ቁጭ ብለን የምናልም ከሆነ ጊዜያችንን ማጥፋት ነው፡፡ ይልቁንም በዚህ ጊዜ ራሳችንን ለትልቁ ቢዝነስ ማብቃት እና ማዘጋጀ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነ የሚያጋጥሙንን እድሎች ሳንጠቀምባቸው እናልፋለን፡፡ 5. አመስግኑ በህይወታችሁ ውስጥ ላሉት መልካም ነገሮች ፈጣሪን ማመስገን ያስፈልጋል ትላለች ኦፕራ፡፡ እንደሷ እምነት ባመሰግናችሁ ቁጥር መልካም ነገሮች ይጨመርላችዃል፡፡ ፈጣሪን ብቻን ሳይሆን ሰዎች መልካም ባደረጉልን ቁጥር ማመስገን ይመከራል፡፡ የምስጋና ህይወ ሲኖረን በህይወታችን ደስተኛ እንሆናልን፡፡ ኦፕራ ምስጋና በጣም አስፈላጊ ነው ብላ ስለምታምን Thank you Game የተባለ መተግበሪያ ወይም አፕ በ2012 አ.ም ፈጥራ ነበር። @yilo15 @bravegenbyyil
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.