cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

አባወራ

አባወራ፦አባትነት፣ ባልነት፣ ወንድነት፣ ራስነት +251-9-11-67-46-87

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 304
Obunachilar
+324 soatlar
+77 kunlar
+2430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ትውልድን ማለጫ መቁረጫ ማቀንጨሪያም ===================================== ሳተናው! አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር! ☀️ "ለተከበራችሁ የኪነ-ጥበብ፣ የሥነ-ጥበብ፣ የጥበብ አፍቃሪያን..." ሲባል ምን ለማለት ተፈልጎ ነው? ☀️ "ኪነ-ጥበብ እና ሥነ-ጥበብስ የሚወክሉት ምንን ነው? ☀️ "ከያኒ፣ ደራሲ፣ ሰዓሊ፣ 'አርቲስት'... የሚባሉትስ እነማን ናቸው? ቋንቋ የተፈጠረው ለሰው ልጅ መግባቢያ እንዲኾነን ነው። ነገር ግን በዚያ እንግባባበታለን ባልነው ቋንቋ ቃላቱንም ተጠቅመን የምናስተላልፈው መልዕክት አለመግባባታችንን ሳያሳውቅ ነገር ግን በሚቃረኑ መንገዶች ወስዶን የተግባባን ካስመሰለን ወደ እውቀትና ወደ ድኅነት ከመሄድ ይልቅ ወደ መሃይምነትና ወደ ጥፋት በጅምላ የሚያደርሰን የጥፋት ሠረገላ ይኾናል። እስኪ ምን ያክሎቻችን ነን "ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ" የሚባሉ ቃላትን ትክክለኛ ፍቺ የምናውቅ? ምን ያክሎቻችን ነን "አርት(Art) ነው" ስለምንለው ነገር ጠንቅቀን የምውናቀው? እነዚህን ቃላት በዛሬው ጦማር ላይ አላብራራም። ለእናንተ የቤት ሥራ እሰጣለሁ እንጂ። ለምን? ብትሉ ምክንያቱም በኪነ-ጥበብና በሥነ-ጥበብ ስም ወገኔ ተጠርንጎ ለባርነት ለሞትም ተላልፎ እየተሰጠ ነውና። እነዚህ ሁለቱ የዘመኔን ትውልድ ጨርሶ አልጫ እንዲኾን ከፍተኛውን ድርሻ እያበረከቱ፣ ኹነኛውንም ሚና እየተጫወቱ ነውና የትርጉምና የአጠቃቀም ጉድለቱን ክፍተቱንም እናንተ እንድትደርሱበት እፈልጋለሁ፤ ከተሳሳትኩም እታረምበታለሁ። ከቅርብ ጊዜያትም ወዲህ በእነዚሁ "ዘርፎች" ከፍተኛ ተዋናይ(ተሳታፊ) የኾኑ ደረስያን፣ ተዋንያን፣ ሰዓሊያን ትውልዱን "ኪነ-ጥበብ ነው፣ ሥነ-ጥበብ ነው" እያሉ ከራሱም ኾነ ከፈጣሪው እያራቁ እያጣሉትም እንደኾነ እረዳለሁ። እስኪ ልጠይቃችሁ ኪነ-ጥበብ ሥነ-ጥበብስ ማለት ለእናንተ ምን ማለት ናቸው? መጀመሪያ ጉግል ከማድረጋችሁ መዝገበ ቃላት ከማገላበጣችሁም በፊት በራሳችሁ እስከዛሬ በደረሳችሁበት እውቀት መልሱ፤ ሲቀጥል ግን ባቅራቢያትሁ ልታገኟቸው የምትችሏቸውን የአማርኛ መዝገበ ቃላቶች በሙሉ ተጠቅማችሁ የቃላቱን መገኛ ዘር ጭምር በመመርመር ተረዱ። ከዚያም አሁን በኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ስም እንኳን በፈጣሪ ላይ ቀርቶ በእርሱ አምሳል በተፈጠረው ፍጥረት ላይ የማላገጥ መብት ሳይኖረው ፌዝና ቧልት ክህደትም የሚፈጽመውን አርቲስት፣ ደራሲ፣ ዘፋኝ፣ ዘማሪ፣ ሰዓሊ፣ የልብስ ሰፊ(ዲዛይነር) ገምግሙ። እውነት ስለ ሁለቱ ቃላት ያገኛችኋቸው ትርጉሞች እና በእነርሱ ስም የሚሠራው ሥራ ምን ያክል እንደሚቀራረብ ታዘቡ። በአባወራ ገጽ ውስጥ አንባቢው እንቶኔ በጻፈው፣ በተናገረው፣ በፈሳውና ባገሳው ሁሉ አስተያየትና የመከላከያ ሃሳብ በመሰንዘር የስብቅና ሥራ መሥራት ሳይኾን የገጹን ተከታይ እውነት የኾነ ተፈጥሮኣዊ እውቀት አስታጥቆ ግለሰቡ በገባውና ባመነበት መጠን እንዲመዝን እና እንዲወስን ይሠለጥናል። እኔም እጠይቃለሁ፦ 👉 "ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ" ትውልድን ማለጫና መቁረጫ መቀሶች ኾነው ያገለግሉት ዘንድ ጠላት እንዴት ቀጠራቸው? 👉 "በኪነጥበብና ሥነጥበብ" የሚያልፉ ወንድም እህቶቻችን ጠንካራና ጤናማ ትውልድ እንዲወጣን የሚያግዥ ለአርኣያነትም የማይበቃ ሕይወትስ እንዴት ኖራቸው? 👉 "ኪነ-ጥበቡንና ሥነ-ጥበቡን" ተክኖበታል የተባለው ግለሰብስ እንኳ ከፈጣሪ ኾነ ከተፈጥሮውም ርቆ ተለይቶ ወድቆበት የሚያይ የሚመሰክር ትውልድስ እንዴት ቢያልጭ(demoralized ቢኾን ነው) "ለእኔ ይበጀኛል" ብሎ እስኪከተለው እስኪያመልከውም ድረስ የታወረበት? ሰሞኑን ብዙዎች "አንጋፋ ደራሲ ነው" ብለው ብዙዎች የሚያደንቁት አንድ ሰው ካደረገው ቃለ መጠይቅ ወስጥ ትውልድን የሚጠቅም አንዳች ነገር አለማግኘቴ ሳይኾን በተቃራኒው እንደውም ፍጹም የሚጎዱት፣ የሚያልጩት ሃሳቦችን በማድመጤ የእርሱ "አድናቂ" የኾነው ትውልዴ አሳዝኖኛል። ባለማወቅ በዚህ "ሙያ" ተሰማርተው ያሉ እህት ወንድሞቼም እንዲሁ ያሳዝኑኛል። በእውነት ነው የምላችሁ ይህ "ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ" የሚባሉ የኾኑ ሙያዎች በአገልግሎት በቤተክርስትያናችን ውስጥ ከሰንበት ትምህርት ቤት ጋር ከገባ ከተጋባም ሃምሳ ዓመት በቅጡ አልዘለለም። ነገር ግን በገባ በጥቂት ዓመታት ውስጥ (በሶሻሊስዝ ዘመን መግባት መጋባቱንን ልብ ይሏል) እውነትና ሕይወት የኾነውን የእግዚአብሄር ቃል መሸቀጫ፣ ስሜት ማብረጂያ፣ ማራገቢያ ካደረገው አስተውሉ (እርሱን ደግሞ ሌላ ጊዜ)። እንደው እውነቱን እንነጋገር ከተባለ እኛ አሁን "ኪነ-ጥበብ ነው፣ ሥነ-ጥበብ ነው" እያልን በምንፎልልለት ሙያ የተገነባች ሀገርም ኾነች ቤተክርስትያን፣ የታነጸ የተገነባም ትውልድ የለም! አንድም የለም! በእርግጥ የፈረሱ፣ የተበተኑ፣ የወረዱ፣ የተዋረዱ፣ ክብራችውን በነውር የለወጡ፣ ከአባታቸው ቃል ከአባቶቻቸውም ትውፊት የተጣሉ የተፋቱት ግን ኁልቁ መሳፍርት የላቸውም። ጀግኖች! ሁሉን አዋቂና ጥበበኛ በኾነው አምላክ ስም ይዣችኋለሁ፦ ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብን ፈልጋችሁ ድረሱባቸውና እንዲህ ያሉ የትውልድ ማፈሪያዎችን፤ እንዲሁም ጠላት ትውልዱን ለማለጫ፣ ለመቁረጫና ለማቀንጨሪያ የሚጠቀምባቸውን መሣሪያዎቹን እንድረስባቸው። አለበለዚያ ግን ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው እንዲል ያገሬ ሰው ነገ ተፈጥሮውንና ፈጣሪውን የሚጠላ ትውልድ እናተርፋለን! አንድም ደግሞ ትውልዳችን እነዚህን መንታ መቀሶች በተሳሳተ መንገድ በመረዳት ከራሱም ኾነ ካምላኩ እየተቆራረጠ አእምሮውን እያጣ መምጣቱ አይቀርም። ወዲህም ደግሞ ይህንን ስናገር ከእኛ ቀድመው በዚህ መንገድ ሄደው ትውልዳቸውን መረን ያወጡ፣ እጃቸውን በእጃቸው የነሱ(የቆረጡ)፣ ተፈጥሮኣቸውንና ፈጣሪያቸውን የካዱ፣ የጠሉም ምዕራባውያንን ምስክር ጠርቼ ነውና እንፍጠን! ታናሼ! ወደ ፊት ትውልዱን በማለጩ ረገድ "ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ" የሚባሉቱ ምንያክል ከፍተኛ ሚና እንደተጫወቱ፣ ይበልጡንም በሰንበት ትምህርት ቤት በኩል ያደረሱትንና አሁንም እያደረሱ ያሉትን፣ ወደ ፊትም የሚያደርሱት ጉዳት እናወጋለን፤ ወደፊት ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር። ብዙ የቤት ሥራ አለብን እኮን! ታዲያ እነዚህን ሁሉ የቤት ሥራዎች ተሸክመን እውን ለዋዛና ለፈዛዛ የሚኾን ጊዜ አለን? እነሆ መኸሩ በዝቷል ደርሷልም፤ ሠራተኞች ግን ትንሽ እጅግም ጥቂት ናቸውና ሚናህን ለይ! ማሳሰቢያ ለእህቶቻችን፦ ሀገርን፣ ትውልድን፣ ትውፊትንም አባቶቻችን ቀድመው ገነውበት ወደነበረበት ከፍታ ልናነሳቸው፣ እኛም እነርሱ ወደ ደረሱበት ከፍታ ወደ አባታችን ልንነሳ ታጥቀናልና እናንተም ኾናችሁ ልጆቻችሁ በ"ኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ" ስም ዓለም በዝናና ገንዘብ እንድትደልላችሁ፣ ንጹሕና ቅዱስ ገላችሁን ልባችሁንም በቆሻሻዋ እንድትበክል አትፍቀዱ! እንወዳችኋለን እንፈልጋችኋለንምና! (ከታች የለጠፍኩት ምስል በአንዲት ሕዝቦቿን አልጫ፣ ትውልዷንም በምታጠፋ ሀገር የሚደጎም ተቋም ውስጥ ሥልጠና ወስደው የፈጠራ ውጤታቸውን ሲያሳዩ በማትገጽ የተጋራውን ነው። ኪነ-ጥበብ ሥነ-ጥበብ ወይንስ የአእምሮ መጥበብ...) ...ይቆየን
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ሴቶቻችንን ከጥፋት ስለመታደግ ==================== አሰስና አልጫ በበዙባት ዓለም ውስጥ ሴቶቻችንን በራሳቸው ተፈጥሮም ኾነ በፈጣሪያቸው ላይ እንዲያምጹ የሚያደርጋቸው ከምስኪንና ሴታውል የከፋ ማንም ጠላት የለም። እነዚህ ግለሰቦች ምስኪንኑና ሴታውሉ በተፈጥሮኣቸው ለማደግ ከእነርሱ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ያቃታቸው አልጫ፣ ሰነፍ፣ ሰበበኛና ስሜታዊ ኾነዋልና የሚናገሩትና የሚኖሩት ሁሉ ፈልገውና መርጠው ከአሰስነታቸው ጋር የሚስማማውን የተስማማውንም ነው። ስለኾነም እነርሱ በሚገቡባቸው በየትኛውም የአገልግሎት ዘርፎች በተለይም፦ በመንፈሳዊ አገልግሎቱ፤ ትውልዱን በጽድቅ ስም ማለጭ(demoralize ማድረግ)፦ ወንዱን ወኔቢስ አልጫ፣ ሴቷን ከተፈጥሮኣዊ ጸጋዋ የተፋታች አመጸኛ ያደርጓቸዋል። አሁን በተግባር በዓይናችን እያየን ያለነው በተለይም በክርስትያኑ ማህበረሰብ ውስጥ እየታዘብን ያለነው ነገር ይህንኑ ነው። ትዳሩን ለመምራት ብቁ የኾነ ወንድ ቀርቶ ራሱን፣ ፍላጎቱን የማያውቅ ልጅ "አዋቂ" ተብሎ እየተጠራ መምጣቱን እንመሰክራለን። በተለይም በከተማው ደፋር፣ ጠንካራና ሥልጡን፦ አባወራ ከመኾን ይልቅ ገንዘብና ዝና፣ ቁስና ሥልጣን ማሳደድ ከዚህችና ከዚያችም መጓተትን ወግ ያደረገ ወንድ "ስኬታማ" ይባላል። ድንቄም ስኬታማ! ረዳቱ የኾነች ሴቷንም፦ 👉 በሥራና ትምህርት ጊዜዋ ባክኖ፣ 👉 ትዕግስቷ ተሟጦ፣ 👉 ለምለም ሰውነቷ ተመጦ፣ ጠውልጎ፣ ደርቆ፣ አርጦ፣ 👉 ትውልድ ማፍሪያ ማሕጸኗ የማንም ስሜት ማራገፊያ ኾኖ፣ 👉 ባትዳራም እንኳ የድንግል-ማሕጸን ልቧ ትኅትና ርቆት ለሙግትና አመጽ ቀርቦ፣ ከረፈደ ትዳርና ልጆችን ፍለጋ እንድትባክን ያደርጓታል። በዚያም ጊዜ ሚስትም እናት መኾን ያቅታታል። ወንድምዓለም! የነገይቷን ኢትዮጲያ፣ የልጆቻችንንም መጪ ጊዜ፣ የትውልዳችንንም ቀጣይነት የሚያሳስብህ ከኾነ ይህንን ጉዳይ ቸል ሳንል ልንወያይበት ይገባል። እህቶቻችንንና ሴቶች ልጆቻችንን ትውልዱን በማለጩ ረገድ ፊታውራሪ ከኾኑት ተቋማት በተለይም እነርሱ ውስጥ ከተሰገሰጉ ሆዳደሮ፣ ሴሰኞች አልጮችም ልንታደጋቸው እነሆ ጊዜው አሁን ኾኗል። የምንታደጋቸው እኛ ነን እንጂ እነርሱ አይደሉም! የሴቶችን ተፈጥሮኣዊ ባሕርይ፣ ታሪክንና የማህበረሰብን ጠባይ ብትመረምር የምታገኘው ይህንኑ ሐቅ ነው። ይህን ስልህ ደግሞ እንደ ንክር ምስኪን ዘለህ ሴቶችን እንድትወቅስ ሳይኾን ይልቁንስ ምንም እንኳ በዚህ ጥፋት እጃቸው ቢኖርበትም ኃላፊነት የነበረበትና ተጠያቂውም እኔና አንተ ነን ለማለት ነው። ችግሩ ዛሬ ዛሬ ወንዱ እንኳን በሀገሩ ያሉ ዘሩን የሚያስቀጥሉ ዘሮች ሴቶች መጠበቅ እንዳለበት አይደለም የራሱን ሚስት እንኳ መጠበቅ እንዳለበት አያውቅም፤ አንድም ተፈጥሮኣዊ ወንድነቱ ገፋፍቶት መጠበቅ ቢፈልግ እንኳ ከምን ሊጠብቃት እንዳለው አያውቅም። ሳተናው! ሴቶቻችንን የምንታደጋቸው እኛው ነን! እኛ አባወራዎቹ! አልጫና ምስኪናኑ የሴቶቹን ደካማ ጎን፣ ምቾት ፈላጊነት በማየት የራሳቸውን ስንፍና በዚያ ይጋርዱበታል። ስለኾነም ስብከቱ፣ ድሰቱ፣ ትምህርቱ፣ ዘፈኑ፣ መዝሙሩ፣ መዝናኛው፣ ፊልሙ፣ ተረቱ፣ መጽሐፉ ሁሉ የእነርሱን ፍላጎት መግዣ ገበያውም ላይ ያነጣጠረ ባይኾን እንኳ የራሳቸውን ንክር-ምስኪንነት ያንጸባረቀ ነው። ይህ ከፍተኛ የትውልድ ክፍተት በክርስትያኑ ማህበረሰብ ላይ፣ በተለይም ደግሞ ከአባቶቻችን በተለየ አሁን አሁን እየተሰበከ በመጣው በነጠላ-ክርስትና(የታይታ) ባለጨው የተዋሕዶ ወገኔ ላይ ይበረታል። ሴቶቻችን ምን መንፈሳዊ ትምህርት ቢማሩ በአብዛኛው የቤቱ "አባወራ" ሚስቱ የኾነችበት የምስኪን አባት ውጤት ይኾኑና ከትኅትና አርቀዋቸው በገና ደርዳሪ አድርገዋቸው፣ ቀለሙን ጠጥተው እስከማስተማር አድርሰዋቸው ሚስትነትን ሲቀጥልም እናትነትን አርቀውባቸዋል። በዚህም ትዳር ቢመሠርቱ ዘግይተው፣ ጸንተው ለመቆየት አገር ተይዞ ለስንት ታቦት ስዕለት ተልኮ፣ አባወራ ባል ቢያገኙ ለመታዘዝ ጎርብጧቸው ፣ ዙሪያቸው ካሉት መረኖች የተነሳ ለፍቺ የሚፋጠኑ፣ ልጆች ቢወልዱ እንዳህያ ጡት ሁለት እነርሱንም ሰማይ ምድሩ ተይዞ ስንት ጭንቅ ጥብ ኾኖ... ወንድምዓለም! ሴቶቻችንን የምንታደግበት ጊዜ አሁን ነው! የምንታደጋቸውም እኛ ነን! እኛ ደግሞ ወንዶች ብቻ ሳንኾን በድፍረት፣ በጥንካሬ፣ በሥልጣኔም የታጠቅን አባወራዎች እንጂ! ከእነርሱም ደግሞ ሀገርን የሚረከቡ ቢነግሡ እንደ ነገሥታቶቻችን እግዚአብሄርን ታዘው ሕዝቡን የሚጠብቁ፣ ቆርበው ቢያቆርቡም እንደ ካህኖቻችን የእርሱ ዐይኑ የሚኾኑ ብዙ ልጆችን እንወልዳለን! የእኔ ሴት ልጆች ማስሬትና ዶክትሬትን መሥራት እንዳለባቸውን አንድ ቀንም አላወራንም፣ ወደ ፊትም አናወራም! እነርሱ ጊዜ የማይሰጥ ጀግናና ጻድቅ የኾነ ትውልድ አባወራ ከሚኾን ባለቸው ጋር የማነጽ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸውና! ታናሼ! ሴቶቻችንን የምንታደጋቸው እኛው ነን! እኛ አባወራዎቹ! ሴሰኛ ትልውድ ሴቶቹን፦ እናቱን፣ እህቱን፣ ሚስቱንና ልጆቹን ቢያሸረሙጥ፣ ቢያበረታታቸውም እንጂ ለአባታቸው ልጆች እንዲኾኑ አያስተምራቸውም! አንድንም ምስኪን የመኾነ ትውልድ፦ እንዲሁ ለስንፍናው እነዲመቸው ሴቶቹን በጽድቅ፣ በእኩልነት እያሳበበ ልባቸውን በማደንደን ለአባወራቸው እንዳይታዘዙ ይገትራቸውል። ☀️ ይገትራቸዋል አልኩኝ፦ የማይታዘዙ ደንዳና ያደርጋቸዋል፤ አንድም ደግሞ ጨርሰው ወንድ እስኪመስሉ በሥራና በትምህርቱ ከትኅትና መራቃቸውን ጥቅስና ኃይለቃል እየመዘዘ ያጸድቅላቸዋልና ቆሞ ቀር ያደርጋቸዋል ስል ነው። በዚህ ደግሞ እርሱም የእነርሱን ውዳሴ እነርሱም የእርሱን ይኹንታ ይመጋገቡ ዘንድ ይፈላለጋሉ) አልጨረስኩም ነገር ሲበዛ ትሰላችብኛለህ! ነገር ግን አስታውስ፣ አትርሳ፣ አትዘናጋም ሴቶቻችንን እኔና አንተ ካልታደግናቸው ፈዘንም ከተቀመጥን ምናችንም ስቧቸው ከእኛ ጋር ቤተሰብ ለመመስረት ትውልድ ለማስቀጠል አይመጡም የለባቸውምም። ለሌላ ደፋር፣ ጠንካራና ሥልጡን ትውልድ ተላለፈው ዐዲስ ማህበረሰብ(demography) ሠርተው "ነበሩ" ተብለን እንቀራለን እንጂ። ትውልዳችንን ማቆየት፣ ትውፊታችንን ማስቀጠል የእኔና ያንተ የአባወራዎቹ ድርሻ ነው! ካለበለዚያ ግን ዐይንህ ዕያየ... ...ይቆየን
Hammasini ko'rsatish...
👍 1 1🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
የትውልድ አልጫ ይሉኝታን ያጸድቃል ====================== ሳተናው! አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር! ይድረስ፦ ይሉኝታ ይጠቅማል እያላችሁ፦ 👉 ትውልዴን ለምትደልሉ፣ 👉 ወገኔን ለምታልጩ፣ 👉 ወኔውን ለምትሰልቡ፣ 👉 ኃይሉን ለምታደክሙ፣ 👉 ድፍረቱን ለምትቀሙ፣ 👉 ፈጣሪነቱን ለምታጠራጥሩ፣ 👉 ጸጋውን ለምታስጥሉ፣ demoralize ለምታደርጉት ሁሉ፡ ወደ ተጠራበት ልሕቀቱ፣ ወደ ጠራውም አባቱ መውጣትን የዘነጋ ትውልድ፦ ሥራው ሰው አየኝ አላኝ፣ ምግባሩ ሰው አለኝ አላለኝ፣ ሚዛኑም የእርሱ ቢጤ ደካማ ሰው፦ ዐይኑ መኾኑ አባቶቹ ከኖሩለት ከኖሩበት ጀግንነትም ኾነ ቅድስና ያርቀዋል። ይሉኝታን "ጠቃሚ ነው" የሚሉ ሕጻናትን "ዋ አባትህ እንዳያይህ" እያሉ የቀጪ የተቆጪያቸውን ዐይን ማስፈራሪያ አድርገው ሥርዓት ሊያሲዙ እንደሚሞክሩት ያሉ ናቸው። ይሉኝታ በልቡ የተጻፈን ሕግ፣ ማህበረሰቡ የተቀበለውን እሴት፣ በመጽሐፍ የተደነገገውን ሥርዓት፣ በአዋጅ የታወጀውን ደንብ ተላልፎ ለሚኖር ትውልድ ምንም አይበጅም። ሰው አምላኩ አባቱም ቢሉ ባፍም ኾነ በመጣፍ ያስተማረውን ሕግ ጠብቆ፤ አልተማረም ቢባል ደግሞ በልቡናው ጽላት ያስቀመጠለትን የሕሊና ሚዛን ተጠቅሞ በእነርሱም ያመነበትን ሲያደርግ ብቻ ጀግና ጻድቅም ይኾናል እንጂ ሰው ዐየኝ አላየኝ ብሎ ቢሠራው ዋጋውን ከሰው ቢቀበል እንጂ ከአባቱ ዘንድ አያገኝም። አንድም ደግሞ በቁርጥ ሕሊና አምነው፣ ቃልን ጠብቀው፣ እግዚአብሄርን አንድ ብለው ሰማይና ምድርንም ደግመውና ሠልሰው ምስክር አቁመውም መልካምን ይሠሯል እንጂ፤ አንድም ደግሞ የትም ብሄድ እንዲህ በሦስት ከሚመሰክሩብኝ ይልቁንም ሁሉን የሚያውቅ፣ የሚያይ፣ የሚሰማም፣ ኩላሊት ያጤሰውን ሳይቀር የሚመረምር ላስቀይመው የማልፈልግ አባት አለኝ፤ ብለው ከክፉ ይሰበሰባሉ እንጂ ዐይቶ አላየሁም፣ ሰምቶ አልሰማሁም፤ ሳያይ ዐይቻለሁ፣ ሳይሰማም ሰምቻለሁ የሚል ዋሾ ሰውን ምን ይለኛል ብለው አይሰማሩም! አንድም ደግሞ ሰው ዐየኝ አላየኝ ብለው በሚሠሩት ሥራ ከራስ ሕሊና ጋር ታርቆ፣ ራስን ኾኖ፣ ከሌሎች በልዩነት ቆሞ፣ ጸጋን ታጥቆ ወደ ተፈጠሩለት ልዕልና መቼም አያደርስም! በዚህ ጉዳይ ላይ በዝጉ የአባወራ ማህበረሰብ ችሎታችን መክረን፣ ተመካክረን፣ አልፈናል። በዚያ ካነሳናቸው በርካታ ጥናቄዎች መካከል አንዱን ልጠይቃችሁ፦ ☀️ ይሉኝታ በከተማ ወይንስ በገጠር ሰው ላይ ይጸናል? ☀️ ለምን? ታናሼ! ትውልዴን ወደ ጽድቅ የሚመሩት እየመሰላቸው ነፃ የምታወጣ እውነት የኾነች እውቀትን ማውራት እንጂ ኖሮ ማሳየት ያልቻሉት እነርሱ የሰውን ፊት ዓይቶ "ከመጥፎ ሥራ መቆጠብ" ጥሩ ነው ይሉታል። ከዚያ ደግሞ "ምን ችግር አለው፣ ምናለበት፣ ምን ይኾናል..." የሚሉ የአሰሶች የስሜት ለቅሶ ይከተላል። ጥያቄው አመክንዮኣዊ መልስ ሽቶ የመጣ ሳይኾን" አስተዛዝኖ ለማጽደቅ" የሚወርድ ሙሾ መኾኑን ያስተውሏል! ወንድምዓለም! ይሉኝታ፦ በአርኣያው የፈጠረክን አምላክን፣ ቁርጥ እርሱን መስለክ የተፈጠርከውን ራስክን፦ እንዳታይ፣ እንዳታዳምጥ፣ እንዳታምን፣ እንዳትተማመንም ጭምር በዘመናዊነት ሰበብ የገባ አረም ነው! ይሉኝታ የሚያስጨንቃቸው፣ ይኹንታ ግድ የሚኾንባቸው ገና ራሳቸውን ያላወቁ፣ ያልገለጡ፣ ያልተረዱ፣ ያልቻሉ ሕጻናት፤ እነርሱም እንኳ በተለይ እንደዚያ ራሳቸውን እንዲችሉና እንዲበቁ ተደርገው ያላደጉ ምናልባትም ከእናታቸው ጋር ብቻ አልያም በንክር-ምስኪን አባት ያደጉቱ ናቸው! ማስታወሻ፦ ሴቶች ካወቁት፣ ከተረዱት ካረጋገጡት እውነት ይልቅ የማህበረሰቡ ይኹንታ ያሳስባቸዋልና በይሉኝታ እንዲጠቁ አስተውል! አንድም ምስኪን ካወቀው፣ ካረጋገጠው፣ ካመነበት ጉዳይ ይልቅ ተቀባይነት የሚያገኝበትን አጥብቆ ይሻልና(በተለይ ከሚስቱ) የይሉኝታ ሰለባ እንዲኾን በሥልጠናችን መዳሰሱን አስታውስ! አባወራ ግን ሰው "ምን አለኝ፣ ምን ይለኛል፣ ምን ይለኝ ይኾናል፣ ምንስ ብሎኝ ይኾን፣ ምንስ ሊለኝ ይችል ይኾን፣ አንዳች ነገር ብሎኝስ ኾኖ ይኾን ባይኾንስ ቢኾንስ..." ሳይል የመጣው፣ የተጠራው፣ የተፈጠረው፣ የተወለደው የአባቱን ፈቃድ ሊፈጽም እንደኾነ ብቻ ዘወትር እያስታወሰ ጥሪውን ይፈጽማል! የሚመጣውንም በጸጋ በደስታ ይቀበላል! ይህን ሲያደርግም እንኳን የሰውን ይሉኝታ የራሱንም ስሜት ንቆ፣ ሽሮም ነው! እንኳንስ ለሌላ ሰው ለራሱም ጣፈጠኝ መረረኝ ሳይል ተልዕኮ፣ ግዳጅም ነውና ይፈጽማል! አልጫ(ፈሪ)፣ ሰነፍ፣ ሰበበኛና ስሜታዊ (አሰስ)፤ አልጫም (ስልብ፣ ወኔቢስ፣ demoralized person) ብቻ ነው፦ ድካሙ ይሉኝታን ወግ መስሎት የሚያጸድቀው! እኛስ ይሉኝታ እንደማይጠቅም አይደለም፤ ይልቁንም እንደሚጎዳ፣ ከጀግንነትም ኾነ ከቅድስና እንደሚያርቅ ያወቅነውን፣ ያየነውን፣ የሰማነውንና የምንኖረውንም እንመሰክራለን! ትውልዱ አምላኩንና አባቱን ቃሉንም አውቆና ጠንቅቆ ጠብቆም እንዲኖር ከማሳወቅና በተለይ ደግሞ ኖሮ "ኑር!" ከማለት ይልቅ ዛሬ የሰውን ፊት ዐይቶ እንዲኖር ማለማመድ፤ ነገ የጌቶቹን ፊት እያየ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲኖር ለባርነት ማለጭ (demoralize ማድረግ) ነው። ወንድምዓለም! ቃሉን ሰምቶ፣ ቃሉን ጠብቆ በቃሉ እንደቃሉ የሚኖር ሰው ወንድ አባወራም አጣን እኮን! ሰው ምን ይለኛል፣ ሰው ይቀየመኛል፣ ሰው ይርቀኛል፣ ሰው...ሰው...ሰው... እያለ ሁሉ አውርቶ አደር፣ ቧልተኛም ኾነብን እኮን! እኔስ ይሉኝታ ይጠቅምሃል አልልም አልልህምም! ባትፈልግ አታንብበኝ! ካላሻህም አትከተለኝ! ጉዳዬ ነው እንዴ! ብታነብ ባታነብ ለሄኖክ መሰለህ? ለደንታህ ነው! ድገመው እስቲ አዎ! ብታነብ ባታነብ ለደንታህ ነው! እኔም የምጽፈው ለደንታዬ፣ ግዴታዬ፣ ምርጫዬም ጥሪዬም ኾኖ እንቅልፍ ቢነሳኝ እንጂ አንተን ካልጣመህ ካልመሰለህ መሄድ ትችላለህ! እርሱ፦ "ዋ! እንቀርብሃለን፣ አንከተለህም...." እኔ፦ ጀግናው መድኃኔዓለምን ተከተል! ተከታይና አድናቂ ጭብጨባ፣ like, share ፈልጌ አልመጣሁም! አንተስ?....ይቆየና!
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ጌድዮንን ፍለጋ ========== ሳተናው! አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር! ትውልድ አልጫ(demoralized) እንዲኾን፦ እየተሰበከ፣ እየተገጠመ፣ እየተዘመረ፣ እየተዘፈነ፣ እየተማረ፣ እየተደረሰ ያለበት የባርነቱ ዋዜማ ላይ እንገኛለን። ዛሬ ነቅተን፣ ታጥቀን፣ ቸኩለን ካልወጣን ነገ፦ የባርነቱ ነጋሪት ይጎሰማል፣ ልጆቻችንም ኾነ ሀገራችን ለባርነት ሲተላለፉ እኛ ደግሞ ታሪክ የሚወቅሰን፣ ልጆቻችን የሚከሱን፣ ሲጠሩን እንኳ የሚሸማቀቁብን ማፈሪያዎቻቸው እንኾናለን። እጅግ በሚያሳዝን ኹኔታ የእግዚአብሄር ሕዝቡ ነፃ ይወጣበት ዘንድ የተሰጠው እውነት፣ እውቀት፣ ሕይወት እንኳ ሳይቀር ትውልዱን ለባርነት የተመቸ እንዲኾን በሆዳደሮች ተጠልፏል። "እነዚህና እነዚያ" ብዬ ብዘረዝራቸው አታምኑኝም የእስከዛሬውም እየጎረበጣችሁ እንደኾነ አውቃለሁና። ትውልዱ ፍዝ፣ ድንዝዝ እንዲኾን መብላት፣ መጠጣት፣ መዳራት፣ ወግ እንዲመስለው ከተሠራበት መሠሪ ሥራ መውጣት ዳገት ኾኖበት ለስሜቱ፣ ለሆዱ፣ ለዝናው፣ ለታይታው፣ ለይኹንታው ባርያ ኾኖ ይበዘበዛል። ከዚህ መውጣትም የሚቻል እስካይመስለው ድረስ እንደ አንበጣ በበዙት አሰሶች፣ እንደ በረሮ በየተቋማቱ በተሰገሰጉ ሆዳደሮች (በተለይም ደግሞ በአባታችን ቤት የመብዛታቸውና የመፍላታቸው ነገር ዘግናኝ ኾኖ) በቁጥር የመበለጡ ነገር ሲያስበው ገና ይረታል። እኛን የአባታችንን የአባቶቻችንንም ልጆች ሊያጠፋን ጥፍሩን ስሎ፣ ጥርሱን አግጥጦ ከመጣው ጠላት ይልቅ ለሆዳቸው አድልተው፣ ባፍጢማቸው ወድቀው አሳልፈው የሚሰጡን የራሳችን ሆዳደር ወንድሞቻችን እንዲበዙ እናውቃለን። ስለ ትውልዱ ግድ የሚለው አጣን! ስለ እግዚአብሄር ልጆች የሚገደው ቸገረን! ሰለ ተረካቢ ትውልድ የሚያሳስበው ናፈቀን! ጀግኖቻችንን የሚተካ ዘር የሚዘራ ሰው አጠረን! ጀግኖቻችንን የምትተካ ወላድ የኾነች እናትም ራቀችን! ወዮ! ወዮታ አለብን! ትውልዱን በጽድቅ ስም የሚያልጭ ቀድሞ ባለጨ አልጫ ብቻ ተከበብን! ወንድምዓለም! በእንዲህ ያለ የመከራ ወቅት፣ በእንዲህ ያለ የጭንቅ ሰሞን በጠላት ቁጥር መበለጣችንን ሳይኾን ታምነንበት የምንሰማራውን አባታችንን አምኖ ከልጆቹ ፊት የሚቀድም ጌድዮንን ሀገሬ ትፈልጋለች። የተፈጠርነው ለዚህ ለአባታችንም ልጆቹ የምንኾነው በእንዲህ ነውና! ወገኔ በአባቶቹ ዘንድ ያልነበሩ ነገር ግን ዛሬ እርሱን እንዲያልጭ የሚያደርጉ በርካታ ሕጎች፣ ሥርዓቶች፣ ፖሊሲዎች፣ ልምዶች ሲዘረጉለት አንድም ጠቃሚ እንዲመስሉት ተደልሎ ወዲህም አስገዳጅም እንዲኾኑ ተሰውሮ ነው። ከትውልዱ ግን ማን አስተዋለ? እኛን ደግሞ ከውጭ ኾኖ ለሚያስተውለን ሁሉን ቻይ፣ አሸናፊ፣ ተዋጊ፣ የማይተወን፣ የማይጥለን፣ እረፍታችንም የኾነ አባት እንዳለን እርሱንም እንደምናመልክ እንኳ ምናችንም አይመስልም። ይልቁንስ አምላካችን የረሳን፣ አባታችን የጠፋን ተቅበዝባዥ አላዛኞች፣ ጠዋትና ማታ ማልቀስ "ጸሎታችን"፣ መነፋረቅም ወጋችን የኾነ ከንቱዎች እንመስላለን እንጂ! ታናሼ! አባታችን የዘመናችን ጌድዮንን ይፈልጋል! መብላትና መጠጣት፣ መጋባትና መዳራት፣ መውለድና መሞትን የተፈጠረለት ዓላማ ያላደረገ፤ ይልቁንስ ለሌላ ከፍ ላለ ዓላማ፣ ለአባቱም መሣሪያ ሊኾን መፈጠሩን የጠነቀቀ፣ የፈቀደና የወደደ ትውልድ ያስፈልገናል። ጌድዮን አባቱን አምላኩንም ያውቀዋል ያምነዋልም! እርሱ በሰው ዘንድ የማይቻል፣ ከሰው አእምሮም በላይ የኾነ ግዳጅን ሰጥቶ የሚሠራ እንደኾነ። በእርሱ ዘንድ የማይቻለው "አይቻለኝም" ብቻ እንደኾነ። እናም ጌድዮን ሆይ ወዴት ነህ? 👉 አሰስነት፣ 👉 አልጫነት፣ 👉 ሆዳደርነት፣ 👉 ፍቺ፣ 👉 አመንዝራነት፣ ዘማዊነት፣ 👉 ድህነት፣ 👉 ሙስና፣ 👉 ዘረኝነት፣ 👉 ሴታቆርቋዥነት (feminism)... የመሳሰሉት እንደ አንበጣ ሕዝቤን ወረውታል። አንድ ሺህ ሦስት መቶ የቴሌግራም፤ ወደ ስድስት ሺህ የፌስቡክ የአባወራ ተከታይ እንዳለ ባውቅም የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት ግን ይህ ቁጥር እጅግ ብዙ ነው። አባታችን ጥቂት ሰዎችን ብቻ ይፈልጋል ወደ አባወራነት ልዕልና በድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔ የሚመጡ፤ በእነርሱም አማካኝነት ሕግና ሥርዓትን ከራሳቸው ጀምረው ሚስትና ልጆቻቸውን በማስተማር ትውልዱን ከላይ ከዘረዘርኳቸው ጠላቶች መንጋጋ ማትረፍን የመረጡ፣ የቆረጡ፣ የጨከኑ! አንተን ነው እኮ! ትሰማለህ አይደል? መበሳጨትን፣ ማማረርን፣ ማለዘን፣ መነፋረቅን አባታችንም ኾነ አባቶቻችን አላስተማሩንም አላወረሱንም! እኔ ምን አቅም አለኝ፦ ወዲህ የወጣልኝ የነጣሁኝም ደሃ፣ ወዲህም ታግዬ የማልጥል ደካማ፣ አንድም ደግሞ ሥልጣን የለኝ ተራ፣ አንድም ያልተማርኩ ጨዋ.... እያልክ ሰበብ አትደርድር መጽ መሣ 6÷15 ጌታ ሆይ፥ እስራኤልን በምን አድናለሁ? ወገኔ ከምናሴ ነገድ ከሁሉ ይልቅ የተጠቃ ነው፤ እኔም በአባቴ ቤት የሁሉ ታናሽ ነኝ አለው ጡቷን ያጠባቻቸው እናታችን ከመነከሳ ይልቅ የሚነክሷት ልጆቿ መኾናቸው ሕመሟን አክፍቶታልና አንተን ጌድዮን ልጇን ከተሸሸግክበት የወይን መጥመቂያው ጉድጓድ ትጠራሃለች። ወንድምዓለም! እስካገኝህ ድረስ ...ይቆየን! (ከታች ያለው 300 የተሰኘው ፊልም ከጌድዮን ታሪክ ጋር ተወራራሽ ነው። ካላያችሁ እዩት ወኔ ቀስቃሽ የጀግኖች ፊልም ነው። ምንም እንኳ ፊልሙ ላይ ስፓርታዎቹ ለስማቸው፣ ለሀገራቸው፣ ለልጆቻቸው፣ ለሚስቶቻቸው ሲሉ በመስዋዕትነት ቢሰዉም ጌድዮንና 300ቶው ሠራዊቱ ግን በሕይወት ድል አድርገዋል)
Hammasini ko'rsatish...
🔥 2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ጾታልባ አውራልባም የሚያደርገን የኤልዛቤል መንፈስ ============================ ሳተናው! አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር! (አውራልባ አውራምባ ላይ የማደርገው ምርመራ፣ ክትትል፣ ጥንቅርም አላበቃም አያበቃምም፤ መለጠፍ ለጀመርነው ጦማር ግን የመጨረሻው ክፍል) እኛ ለጊዜውም ቢኾን ወደን ፈቅደን እንስጣቸው እንጂ ኋላ ላይ በትምህርት ሥርዓቱ በፖሊሲውም አስገድደው እጃችንንም ጠምዝዘው ቢኾን፦ 👉 አርኣያ የሚነሳቸውን፣ 👉 አስታዋሽ የሚያሳጣቸውን፣ 👉 መሪ የማያወጣላቸውን፣ 👉 አንድ የማያደርጋቸውን፣ 👉 በፉክክር የሚያናንቃቸውን፣ 👉 በጠላት የሚያስበላቸውን፣ 👉 ራሳቸውን የሚያስጠላቸውን ትርክት በጾታ እኩልነት ስም ይጋታሉ። ምዕራባውያን ልጆቻቸውን ከስራቸው የተነጠቁት፣ መቀልበስ በማይችሉት ሴራ የተጠለፉት እንዲህ እንደ ማር እንደ ወተት የምትጣፍጥ በውስጧ ግን ትውልድ ገዳይ መርዝ የተበከለች የጾታ እኩልነትን ግተዋቸው ነው። ወንድምዓለም! እኩልነት፣ በተለይም ደግሞ የጾታ እኩልነት ትውልድን ለባርነት ለመማገድ የተፈጠረ፣ የተመቸ፣ የተረጋገጠ፣ ተስተካካይም የሌለው ኹነኛ ወጥመድ እንጂ እውነትም በሴቶችና በወንዶች መካከል "አለ" የተባለውን መበላለጥ ለማስተካከል የመጣ አይደለም። ይህን ወንዱን ለመጣል፣ እንድታግዘው በተሰጠችውና በእርሱ መካከል ያለውን ተግባቦት፣ አንድነት፣ ውሕደትም በጥርጣሬ ሞልቶ ሁለቱን ለመለያየት በዐለም መጀመሪያ ሰይጣን የተጠቀመበት ዘዴ ግልባጭ ነው። ልጆች ይህንን ከልጅነታቸው ጀምሮ እንዲማሩት፣ እንዲያውቁትና በልቦናቸውም ተስሎ እንዲቀመጥ በዕድሜያቸው መጀመሪያ "ሕጻናት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት የማግኘት መብት አላቸው" በሚል ስላቅ ልጆችን በግድ በሚግተው የአስኳላ ትምህርት በኩል ይሰጣቸዋል፤ ይነገራቸዋልም። ይህ ብቻ አይደለም! የግበረ ገብ ልዕልና፣ የሥነ-ምግባር መነሻ፣ የመልካምነት ምንጩ፣ የፍቅርም ነቁ እግዚአብሄር ኾኖ ሳለ እርሱን ገለል አድርገው፣ ከእርሱ ወስደው እሱን ግን አስቀርተው ያስተምሯቸዋል። የትኛውም ሥነ-ምግባርም ኾነ የኑሮ ሥርዓት መነሻውንና መድረሻውን ፈጣሪውን ካላደረገ ከንቱ መኾኑን ሕጻናቱ አያውቁምና ይህንኑ ከንቱ የከንቱ ከንቱ የኾነ ትርክት ይማራሉ። በእርግጥ "ፈጣሪ አለ" ማለታቸው "በፈጣሪ ያምናሉ" እንዲያስብላቸው ቢኾንም እርሱን በተረዳችሁት መጠን ግለጡት፣ ስሙን ጥሩት፣ አደራረጉን አስረዱት ቢባሉ ምንም ዓይነት መተንተኛ መግለጫም የላቸውም። ስለኾነም ልጆቻቸውን በርካቶች አምነው የሚከተሉት ፈጣሪ ባለበት ሀገር ውስጥ ኾነው ሃይማኖት አልባ ለማድረግ ከራሳቸው ምኞትና አለማወቅ የተነሳ ያጠፏቸዋል፤ ሌሎችነሰም እንዲሁ "እምነታችን ሥራ ነው" በሚል ማርክሲስታዊ መፈክር ይጣራሉ። ልጆች በተፈጥሮ ወንድና ሴት ተደርገው ቢሰጡንም ቅሉ ወንዶቹ አባወራውን አባታቸውን ሴቶቹ ደግሞ ትኁት እናታቸውን በመከተል ጾታቸውን(ጸጋቸውን)፣ በተለየላቸው ሚና ለተፈጠሩለት ዓላማ ያበለጽጉታል። በአውራልባ ማህበረሰብ ግን ልጆች በጾታ እኩልነት ሰበብ ፈጣሪ ባልሰጣቸው ጸጋ፣ በማይወጡት ሚና ያልተጠሩበትን ዓላማ እንዲፈጽሙ ይሠለጥናሉ፤ ይገደዳሉም። ይህም ደግሞ በጊዜ ሂደት ለሚፈጠር የጾታ ግራ ገብነት፣ "ወንድ ነኝ ወይስ ሴት፣ ወይንስ እንዲያ የሚባል የለም፣ ..." ለሚል ሙግት ይዳርጋቸዋል፤ ከአእምሮኣዊ ቀውስም ያደርሳቸዋል። ወንድምዓለም! እንኳን ዘንቦብሽ እንዲያውም ጤዛ ነሽ እንዲሉ፤ እንኳንስ በጾታ እኩልነት ሰበብ ወንዱን ሰልበውት አይደለ፤ እንደውም ወንዱ ወንድነቱን እያጣ አላዛኝ፣ ነፍራቃ፣ አባብሉኝ አወድሱኝ ባይ ሴሰኛም እየኾነ መምጣቱን መታዘብ ትችላለህ። ያንተን አላውቅም እኔ ግን ወንዶችም ሴቶችም ልጆች አሉኝ! ወንዱ ወንድ ነው ሴቷም ሴት! እኩልነት የሚባለውን የጠላት ሴራ እንኳን በቁም ነገሩ በተረቱም አይሰሙትም፣ እንዲሰሙትም አልፈቅድላቸውም፣ ከሰሙትም አርባ ክንድ እንዲርቁት አስጠነቅቃቸዋለሁ እንጂ! ጀግኖች! ይህ በሰው ልጅ ላይ የተቃጣ ሴራ፣ መልካም በሚመስል ስምም የተሰወረ ሸፍጥ ነው። ሰውን ከፈጣሪውና ከፍጥረቱ ለመለየት ታቅዶ ከመጣ ማርክሲስታዊ እሳቤ "ነፃ ነኝ፣ ገለልተኛ ነኝ፣ የለሁበትም፣ አይመለከተኝም" ማለት አንድም አልጫነት፤ አንድም ደግሞ ለብታ(ትኩስ ወይንም በራድ አለመኾን) ነውና አስተውል! ጦርነቱ መልካም ከክፉ፤ ዘለዓለማዊ ሕይወት ከዘለዓለማዊ ሞት ጋር ነውና አይርፈድብን! "የሴቶችን እኩልነት ያረጋገጠ..." የሚባለውን ሐረግ ደጋግማችሁ ስትሰሙ የኤልዛቤልን መንፈስ አስታውሱ! የኤልዛቤል መንፈስ፦ ✨ ስትታገስ ባንተና በትውልድ ላይ ይነግሥ፤ ✨ አባወራ መኾን ካልቻልክ እማወራ ትኾንብሃለች፤ ✨ ወደ ጽድቅ ከፍታ ካልወጣህ ወደ ኃጢአት አዘቅት ታወርድሃለች፣ ✨ እኩልነት ትላለች ባርነትን፣ ጣዖት አምልኮንም ታመጣብሃለች!.... 💪 ሕይወታችንን፣ ስብከታችንን፣ አገልግሎታችንን፣ ሚናችንን፣ ልጆቻችንን፣ ወንዶቻችንን፣ ትዳራችንን ሁሉ ልትቆጣጠር የምትሻውን የኤልዛቤል መንፈስ ደግሞ አንድ ቀን እንመጣባታለን...ይቆየን። እመኑኝ! አንድም በስሙ ሁሉን ማድረግ የሚቻለንን ክርስቶስን አምነን መሠማራታችንን እመኑኝ! በደም የተጨማለቀች፣ በጥላቻ የጨቀየች፣ በፍቺ የፈረሰች፣ መረን በወጡ ልጆቿ የደከመች፣ በሆዳደር የአብራኳ ክፋዮች ጡቷን የታኘከች እናታችንን እንክሳታለን!💪 ምንም እንኳ ጠላት በትውልዱ መካከል እንክርዳድ ቢዘራ፣ ኤልዛቤልም ትውልዱን ወደ ጥፋት ብትነዳም እኛ ግን ታምነንበት ከዘራነው አምላካችን ዘንድ ሠላሳ፣ ስድሳና መቶ መሰብሰባችን እርግጥ ነው! እመኑኝ ቀና እንላለን! ነገር ግን መስዋዕትነት የሚከፍሉ፣ በራሳቸው ላይ የጨከኑ፣ እውነትንየሚሹ፣ ስለእውነት የሚሰዉ ትውልዶች አባወራዎችንም እንሻለን እንጂ! 👉 ከታች በስተግራ የምታዩዋቸው ወንድነታቸውን ከሴቷ ያስተካከሉ፣ ወንድነት ስጦታቸውን(መክሊታቸውን) ቀብረው ሚስታቸውን ለእነርሱ ባልተሰጣቸው ጸጋ በሚናዋ ገብተው "የሚያግዙ" ሲኾኑ፤ 👉 በቀኝ በኩል የምታዩት አባት ደግሞ "ከሴቷ በተለየ፣ የተለየ የማይስተካከልም ስጦታ አለኝ፣ በዚያም በተለየልኝ ሚና ልጆቼን አንጻለሁ" ያለ አባወራ (እኔ ከልጄ ጋር ከአራት ዓመት በፊት) ነው። ወንድምዓለም! የወደድከውን ተከተል! በወደድከውም ኑር! እኔ ግን ውርድ ከራሴ!
Hammasini ko'rsatish...