ወንጌል ለዓለም🔈🌎
''And he said to them, Go into all the world, and preach the gospel to every creature. Mark 16:-15 እንዲህም አላቸው ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ማርቆስ 16:-15 የተመሠረተበት ቀን (ግንቦት 08/09/2012) ለአስተያየት @Geruuu ላይ inbox.
Ko'proq ko'rsatish5 306
Obunachilar
+224 soatlar
-97 kunlar
-5530 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
የእግዚአብሄር ማደርያ ምን ያህል የሚያስፈራ እና የተቀደሰ ስፍራ ነው፡፡
and that dwelling place of God that temple is your body
everybody say after reading this message
🔥🔥🔥"my body is the temple of God"🔥🔥🔥
join us we will discuss the book of Leviticus in 4 parts!!
በ 4 የተለያዩ ክፍል ከፋፍለን የቅዱሱን ማደሪያ ስርዐት እና የእግዚአብሄርን መገኘት የሚአወጋንን ኦሪት ዘሌዋዊያንን እናጠናለን፡፡
ይቀላቀሉን አንዱን መንግስት ለመውረስ በህብረት እንሰራ በህብረት እንዘጋጅ!!!!
Repost from እውነተኛ ክርስቲያን️
17:05
Video unavailableShow in Telegram
"yemikores hiwet" bedenb simut teregagtachu @truthchristiyanity
የሚቆረስ ሕይወት(360P).mp451.09 MB
ዛሬ በእድሜዉ ትንሽ ገፍ ያሉ ምናልባት ከ60ዎቹ ያለፉ አንድ አባት በአጋጣሚ አጊንቻቸዉ በጌታ እንደሆንኩኝ እንኳን ሳይጠይቁኝ፣ ስለ ጌታ ኢየሱስ መናገር ጀመሩ እኔም፣ የመስማት ፍላጎት እንዳለኝ፣ ገለፅኩላቸዉ ትኩረቴንና ጆሮዬን ሰጠዋቸዉ።በጌታ እንደሆንኩኝና እንደማገለግልም ነገርኳቸዉ። እሳቸዉም ስላገልግሎቴ ትንሽ ላጫዉትህ ምናልባት ለአንተ ሊጠቅምህ ይችላል አሉኝ። ለ40 አመታት ያህል የእግዚአብሔርን መንግስት በድካሜም በብትርታቴም አገልግያለሁ፣ነገር ግን እንዳገለገልኩት ዓመታትና፣ በዉስጤ እንዳለው አቅም ልክ ፍሬያማ ልሆን አልቻልኩኝም አሉኝ። ምክንያቱ ምን መሰለህ አሉኝ የአገልግሎት አብዛኛዉን እድሜዬን መለወጥ ከማልችለዉ ነገር ጋር ስታገል ነዉ ያሳለፍኩት ፣ያንን ነገር አሁን ላይ ሳስበዉ ይቆጨኛል፣መለወጥ የማልችለዉን ነገር ትቼ መስራት ወደምችላቸዉ ባተኩር በብዙ ፍሬያማ እሆን ነበር አሉኝ፣አሁን ላይ በህይወት ያሉትን ደግሞም ያለፉትን በምድሪቱ ላይ ታላላቅ በጎ ተፅዕኖ የፈጠሩትን የእግዚአብሔር ሰዎች ጠቀሱልኝና ፣ከእዚህ ከአብዛኛዎቹ ጋር አገልግሎት፣ በተመሳሳይ ጊዜ ነዉ የጀመርነዉ አሁን እነርሱ በአብዛኛው አማኝ ልብ ዉስጥ አሉ ምክንያቱም ለብዙዎች የመባረክና፥ የመታነፅ፥ ብሎም ለብዙ አገልጋዮች የመነሳት ምክንያት ስለሆኑ፣ ከኢትዮጵያ አልፈዉ በአለም ዙሪያ ዛሬም ቢሆን የእግዚአብሔርን ሀሳብ ያገለግላሉ እኔ ግን በዚያን ጊዜ ልለዉጠዉ ከማልችለዉ ነገር ጋር እታገል ነበር፣ በዙሪያዬ የነበሩ ሰዎች በአገልግሎቴ ብዙም ደስተኛ አልነበሩም፣ እነርሱን ለማስረዳት በአንድ ቤተክርስቲያን ቁጭ ብዬ 27 አመት ፈጀብኝ ከ27 በኃላ ነዉ ነገሩ እንደማይለወጥ የገባኝ፣ አስበከዋል የኔ ልጅ ከ27 አመት በኃላ ልክ እንዳልነበርክ ሲገባህ፣ ለካ ብዙ ስራ መስራት እችል ነበር አሉኝ። የጠቀስኩልህ በህይወት ያሉም የሌሉም አብረዉኝ አገልግሎት የጀመሩ አገልጋዮች በምድሪቱ ላይ ታላላቅ የሆነን ተፅዕኖን የፈጠሩት ሁሉም ሰዉ ስለተቀበላቸዉ አልነበረም ወደሚቀበሏቸዉ እየሄዱ እንጂ፣ በፅድቅና በእዉነት እያገለገሉ ብዙ ትችትና፥ ነቀፌታ፣ስድብ፣ድብደባም ጭምር ይደርስባቸዉ ነበር፣ እነርሱ ግን ጥሪያቸዉ ላይ ብቻ ነበር ትኩረት ያደርጉ የነበረዉ። ለዛ ነዉ ተፅእኖን መፍጠር የቻሉት። እኔ ግን ያልተቀበሉኝ እንዲቀበሉኝ ስታገልና፣ ሳስረዳ እድሜዬን አባከንኩ ወደሚሰሙኝ ብሄድ ብዙ እንደማተርፍ አሁን ገና ነዉ የገባኝ አሉኝ።የሳቸዉን ታሪክ በሀዘን ስሜት ሆኜ ብሰማዉም ደግሞ ካሳለፉት ህይወት ብዙ ነገር ተምሪያለሁ። ምናልባት ይሄ መልእክት አንድ ሰዉ ሊጠቅም ይችላል ብዬ ስላሰቡኩኝ ነዉ የፃፉኩት።
የእግዚአብሔር መንግስት አገልጋይ ብትሆንም በፅድቅና በታማኝነት ብታገለግልም ሁሉ ይቀበሉኛል ብለህ አታስብ። ሁሉ ይቀበለኝ ካልክ የማይቀበሉህ ሰዉ ሲገጥሙህ ልብህ ይጎዳል እነርሱ ደግሞ እንዲቀበሉህ ስታስረዳህ ለሚሰሙህ መልእክትህን ሳታሰማ ከጊዜህ ጋር ትተላለፍለህ። የምናመልከዉና የምንከተለዉስ ጌታ ሲያገለግል መቼ የሰሙት ሁሉ ተቀበሉት?
መለወጥ በማትችለዉ ጉዳይ ላይ እድሜህን እትጨርስ መስራት በምትችለዉ ጉዳይ ላይ አተኩር።አንተን የሚጠብቁ ብዙ ስራዎች ስላሉ።
በእየሱስ ስም ዘመናችሁ አይበላ አሜን።
#ከፀደቀ #መንፈሰ
❝ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝ የጽድቅ ፍሬ ሞልቶባችሁ፥ ለክርስቶስ ቀን ተዘጋጅታችሁ ቅኖችና አለ ነውር እንድትሆኑ የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ፥ ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ።❞
—ፊልጵስዩስ 1: 9-11
Boshqa reja tanlang
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.