cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ሳምንትአዊ ኢስላሚክ ዜና እነ መዝናኛ

በአላህ ተማመን!!!! መቻቻል መርሐችን ማድረግ አለብን!!! አስታያት ካሎት..

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
827
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ሰሜን ኮሪያ ኒውክሌር ለማምረት የሚያስችላትን ኬሚካል ማበልጸግ ሳትጀምር አልቀረችም ተባለ ፕሉቶኒዬም ልክ እንደ ዩራኒዬም ሁሉ ኒውክሌርን ለማምረት ከሚያስችሉ ወሳኝ ሁለት ግብዓቶች መካከል አንዱ ነው ፒዮንግያንግ ዮንግባዮን በተሰኘው ዋና ኒውክሌር ማብለያ ጣቢያዋ ፕሉቶኒዬም የተሰኘ ኬሚካልን እያበለጸገች ነው ተብሏል ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለማምረት የሚያስችላትን ፕሉቶኒዬም የተሰኘ ኬሚካል ማበልጸግ ሳትጀምር አልቀረችም ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ፡፡ ፕሉቶኒዬም ልክ እንደ ዩራኒዬም ሁሉ ኒውክሌርን ለማምረት ከሚያስችሉ ወሳኝ ሁለት ግብዓቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ የድርጅቱ የአቶሚክ ኃይል ተቆጣጣሪ አካል (IAEA) የ5 ሜጋ ዋት አቅም ያለውና ዮንግባዮን የሚገኘው ዋና ኒውክሌር ማብለያ ጣቢያ ስራ ጀምሯል ሲል በዓመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡ ከ2018 ታህሳስ እስካሳለፍነው ሃምሌ ድረስ ፒዮንግያንግ ኬሚካል ማበልጸጓን አቁማ ነበር ያለው ተቆጣጣሪው አሁን ግን ስራ መጀመሯን የሚያሳዩ ምልክቶችን ተመለክቻለሁ ሲል ገልጿል፡፡ ዮንግባዮን፤ ለሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር መርሃ ግብር “የደም ስር ነው” የሚባልለት የጥናትና ምርምር ቦታ ነው፡፡ IAEA ባለሙያዎቹ ከፒዮንግያንግ ከተባረሩበት እ.ኤ.አ ከ2009 ጀምሮ በሰሜን ኮሪያ ተደራሽነት የለውም፡፡ ሂደቶችን በሳታላይት ከመከታተል እና ምስሎችን ከመተንተን ያለፈ ገብቶ ሊያረጋግጥ የሚችልበት መንገድም የለም፡፡ ሆኖም አሁናዊ ለኒውክሌር ጦር መሳሪያ ምርት ግብዓት የሚሆኑ ኬሚካሎችን ማበልጸግ መጀመሯ፤ ልክ ከአሁን ቀደም ታደርግ እንደነበረው ሁሉ “ወደ ጦር መሳሪያዎች ሙከራዋ ትመለስ ይሆን?” የሚል ስጋትን በተቋሙ ባለሙያዎች ዘንድ አጭሯል፡፡ ፒዮንግያንግ ለመጨረሻ ጊዜ በ2017 ነበር የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሙከራ ያረገችው፡፡ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፤ ሃገራቸው የማዕቀብ እፎይታ የምታገኝ ከሆነ ፕሮግራሙን ለማቆም ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በ2019 ተነጋግረው እንደነበር ይታወሳል፡፡
Hammasini ko'rsatish...
በዛሬው እለት ከሰንበቴ ወደ ጋቸኒ ሊዘዋወር የነበረ ጩቤና የኦነግ ሸኔ ባንድራ ያለበት የጥይት ካርታ መያዣና ሌሎች ህገወጥ እቃዎች በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ፡፡ እንደ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽቤት ገለጻ ከሆነ ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰአት ተኩል አካባቢ 20 ህገ ወጥ ጩቤ ፣ 6 የኦነግ ሸኔ ባንድራ ያለበት የጥይት መያዣ ካርታ ፣ 5 እንግብ ፣ 5 የትጥቅ መያዣ ቀበቶ እንዲሁም አንጋዳ ከሰንበቴ ተነስቶ አፋር ክልል ጋቸኒ ሊዘዋወር ሲል በ08 ቀበሌ ፖሊስ ኦፊሰርና ማህበረሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል፡፡ ዝውውሩ ለማካሄድ ወደ ደብረ ብርሀን የሚያስኬደውን ኬላ በባጃጅ ማለፍ እንደ ቴክኒክ ተጠቅመው እንደነበርና ሲያዘዋውር የነበረው ግለሰብም በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት መሆኑ ጽ/ቤቱ አያይዞ ገልጿል፡፡ በህገ ወጥ መንገድ አካባቢው የሁከት ቀጠና ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ አካላት ማስቆም ወይም መግታት የተወሰነ አካል ድርሻ ብቻ አድርገን ባለመውሰድ ሁላችንም የድርሻችን ልንወጣ ይገባል። በተለይ የባጃጅ አገልግሎት የምትሰጡ አሽከርካሪዎች የሸዋሮቢትንና የአካባቢዋን ሰላም ለማምጣት የናንተም ድርሻ ከመቼውን ጊዜ በላይ አሁን ያስፈልገናል እናም አገልግሎት የምትሰጡትን አካል በደንም ማወቅና መለየት ያስፈልጋል፤ አጠራጣሪ ነገርም ስትመለከቱ ለሚመለከተው የጸጥታ አካል ጥቆማ ማድረግ ይገባል እንላለን ፡፡ የሸዋሮቢት ከንቲባ ፅህፈት ቤት
Hammasini ko'rsatish...
የደሴ ከተማ አስተዳደር ለተፈናቃዮች ድጋፍ ለማድረግ መቸገሩን ገለጸ ሀሩን ሚድያ ነሐሴ 22፣ 2013 አድስ አበባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ወደ ከተማው የሚገቡ የተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ የሰብዓዊ ድጋፎች ለማድረግ ተችግሬያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የደሴ ከተማ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ምሳዬ ከድር እንደገለጹት፣ የቀይ መስቀል፣ የአደጋ መከላከያ እና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት የተለያዩ አካላት ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም፣ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ለመጣው የተፈናቃዮች ቁጥር የተሰጡ የሰብዓዊ ድጋፎች አነስተኛ ናቸው ብለዋል። አያይዘውም በየቀኑ የሚገቡትን ተፈናቃዮች ለማስተናገድ ተከታታይ የሆነ ድጋፍ ያስፈልጋል ሲሉ ነው የገለጹት። ጉዳዩ በመንግሥት በኩል ለጥቂት ጊዜ ብቻ ትኩረት ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ሰዓት እየተረሳ በመምጣቱ የሚሰጡ ድጋፎች መቀነሳቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም ተፈናቃዮችን ለማስተናገድ ከፍተኛ ችግር ገጥሞናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የከተማው ማኅበረሰብ ከሚያደርገው ድጋፍ ውጭ በመንግሥት በኩል ተከታታይ ዕርዳታዎች ባለመምጣታቸው ችግር ላይ እንገኛለን ብለዋል። ይህ መረጃ እስከተጠናከረበት ቀን ድረስ ወደ ከተማዋ የሚገቡ ተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን፣ በቀን እስከ 200 ሰዎች ከተለያዩ አካባቢዎች እየገቡ ነው ብለዋል። በዚህም ከ300 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በአካባቢው እንደሚገኙ ነው የጠቆሙት። ወደ ደሴ ከተማ እየገቡ ያሉ ተፈናቃዮች በሽብርኝነት የተፈረጀው ህወሓት ወረራ ከፈጸመባቸው የሰሜን ወሎ አካባቢዎች እና የአፋር ክልል መሆኑን ምሳዬ ይናገራሉ። በዚህም የሰሜን ወሎ ዞን አጠቃላይ ነዋሪዎች፣ ከአፋር ክልል የአንድ ወረዳ ነዋሪዎች፣ እንዲሁም የሌሎች አካባቢ ተፈናቃዮች ወደከተማው መግባታቸው ነው የተገለጸው። በደሴ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ሲጠቀሙባቸው የቆዩትን አምስት መጠለያ ጣቢያዎች ባሳለፍነው ሰኞ ወደ ዘጠኝ እንዳሳደጉት የገለጹት የመምሪያ ኃላፊዋ፣ መጠለያዎቹን የማይጠቀሙና ቤት ተከራይተው እንዲሁም ዘመድ ጋር ተጠግተው የሚኖሩ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። በመጠለያ ለሚገኙት የሕብረተሰብ ክፍሎች የከተማው ነዋሪዎች ምግብ እና አልባሳት በማሟላት የሰብዓዊ ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነ ነው የገለጹት። በከተማዋ የሚገኙ የጤና ተቋማት የጤና አገልግሎትን በመስጠት እንዲሁም ገንዘብ ያላቸው ገንዘብ በመስጠት ተፈናቃዮችን እያገዙ ይገኛሉ ተብሏል። ©ሀሩን ሚድያ
Hammasini ko'rsatish...
የደሴ ከተማ አስተዳደር ለተፈናቃዮች ድጋፍ ለማድረግ መቸገሩን ገለጸ ሀሩን ሚድያ ነሐሴ 22፣ 2013 አድስ አበባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ወደ ከተማው የሚገቡ የተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ የሰብዓዊ ድጋፎች ለማድረግ ተችግሬያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ የደሴ ከተማ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ምሳዬ ከድር እንደገለጹት፣ የቀይ መስቀል፣ የአደጋ መከላከያ እና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት የተለያዩ አካላት ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም፣ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ለመጣው የተፈናቃዮች ቁጥር የተሰጡ የሰብዓዊ ድጋፎች አነስተኛ ናቸው ብለዋል። አያይዘውም በየቀኑ የሚገቡትን ተፈናቃዮች ለማስተናገድ ተከታታይ የ
Hammasini ko'rsatish...
ስለጠፋን አፋ በሉን❤❤❤
Hammasini ko'rsatish...
Islamic wallpaper Islamic quote Islamic picture Islamic Perfiles
Hammasini ko'rsatish...
FREE PALESTINE
Islamic wallpaper
Islamic Perfiles
Open the channel
#ይህ_ቻናል_የሙንሺድ #ኑረዲን_ከይረዲን__ቻናል_ነው #Join__እያላቹ_ቤተሰብ_ሁኑ 👇👇 @nuredin_keyredin @nuredin_keyredin
Hammasini ko'rsatish...
🎧የከቨር ስራዎች🎧
🎤አዳዲስ ነሺዳዎችኔ🎤
🎧ኑረዲን ከይረዲን🎧
ትኩስ መረጃ
አዳዲስ ክስተቶች
ጥቆማዎችን
ከእናንተ ሚጠበቀው join ነው
share ማረግ አይርሱ
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.