TheDeepThingsOfGod
Kanalga Telegram’da o‘tish
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Ko'proq ko'rsatish1 810
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
Ma'lumot yo'q30 kun
Postlar arxiv
1 810
...ነገር ግን የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ በምድር ላይ እምነትን ያገኝ ይሆንን?””
— ሉቃስ 18፥8 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ዮሐንስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።
👉የወንድና የሴት ውጤት አይደለም! የእግዚአብሔር ምክር ነዉ: ስጋ የሆነው!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
The #SHOCKING Generals where in Africa!!!
#አስደንጋጮቹ_ጀነራሎች_የነበሩት_አፊሪካ_ውስጥ_ነበር!!!
ስለ ተለያዩ ጀነራሎች እንዳነበባችሁ አውቃለሁ: እኔም አንብቤያለሁ ጀነራሎች ናቸዉ! እግዚአብሔር ከሰው የማድረግ አቅም በላይ የሆነ ነገር እንደሰራባቸውም አውቃለሁ ነገር ግን አብዛኛው ሰው የማያውቋቸው #የኤልያስ አይነት ጀነራሎች እስከ ዛሬ ከምታውቃቸው ጀነራሎች ሁሉ በበለጠ እግዚአብሔር የተጠቀማባቸው ጀነራሎች የነበሩት አፍርካ ውስጥ ነበር!!
ለማመን የሚከብድ ሊሆን ይችላል: እውነታው ግን ይሄ ነዉ: በስፋት የጽሑፍና የምስል ማስረጃ ስለሌለ አልታወቁም ነገር ግን እግዚአብሔር በአንዳንዶቹ የሰራውን ማመን አትችሉም: ከአእምሮ በላይ እና እስከ ዛሬ በምታውቋቸው ጀነራሎች በአንዳቸውም ሕይወት ያልተገለጠ የእግዚአብሔር ሃይል ተገልጦባቸው ነበር!
እግዚአብሔር በአፍሪካ ያደረገው እና አሁንም ልያደርግ ያለው: የመለኮት ሃይል መግለጥ ዓለምን ብቻ ሳይሆን ሰማያትንም የሚያንቀጠቅጥ ነዉ!
👉በመጨረሻው ዘመን ከቤተክርስቲያን ንጥቀት በፊት ምድርን የሚያስደነግጡ እና የሚያነቁ የእግዚአብሔር መልእክተኞች የሚነሱት ከአፍሪካ ነዉ: ይህም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሚስጢር ተቀምጧል!
👉የመጨረሻው ዘመን መገለጥ ልሆን ነዉ: ጊዜው ደርሷል!
ከላይ ያለውን ሁሉ በቅርቡ እገልጻለው: የአፊሪካ ጀነራሎችን ታሪኪ ለማቅረብ እሞክራለሁ! ምክንያቱም ጊዜው ደርሷል ብዬ አምናለሁ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Don't miss this❗️❗️❗️
ዛሬ ማታ 3:00 ጀምሮ #7 ዙር በ ThingsOfGod~Group: ፈጹም ለውጥን (Transfiguration) እንዴት መለማመድ እንደምንችል #መንፈስ ያስተምረናል: ደግሞም እንጸልያለን! በዘመን መጨረሻ የእግዚአብሔር ሃሳብ ፍጹም የተለወጡ እና እንደ ክርስቶስ የሆኑ ልጆቹን በዓለም ሁሉ ላይ መግለጥ ነዉ!🔥
“የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና።”
— ሮሜ 8፥19
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
𝚋𝚢 𝚜𝚝𝚊𝚢𝚒𝚗𝚐 𝚒𝚗 𝚝𝚑𝚎 ᴘʀᴇsᴇɴᴄᴇ ᴏғ ɢᴏᴅ 𝚕𝚘𝚗𝚐 𝚎𝚗𝚘𝚞𝚐𝚑, 𝚘𝚗𝚎 𝚌𝚊𝚗 𝚒𝚖𝚙𝚊𝚛𝚝 𝚊𝚗𝚍 𝚍𝚎𝚟𝚎𝚕𝚘𝚙 𝚝𝚑𝚎 ɴᴀᴛᴜʀᴇ ᴏғ ɢᴏᴅ.
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#ለጌታ_የፍቅር_ቃል!😭❤❤❤
ተባረኩበት
#ካላየሁ_ክብርህን!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የእግዚአብሔር ልጆች አደገኛ መሳሪያ ናችሁ!
👉በእግዚአብሔር እጅ እንዳለ ፍላጻ ናችሁ!
👉የጠላት ምሽግ በእናንተ ይፈርሳል!
👉ግባችሁን አትስቱም! አሜን!
“ብልቶቻችሁንም የዓመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ፥ ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ፥ ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ።”
— ሮሜ 6፥13
#በእግዚአብሔር_እጅ_እንዳለ_የጦር_እቃ_ለመሆን_መምረጥ_እንችላለን!
#I_AM_A_WEAPON!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የፍጹም ለውጥ እንቅፋቶች!
#ስሙት!
#መሮጦ_መያዝ!
🔥🦋Transfiguration🦋🔥
#በመጨረሻ አብራችሁኝ ጸልዩ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
December 21 በዚሁ ቻናል በመንፈስ ቅዱስ የተናገርኩትን ትንቢታዊ መልእክት ተመልከቱ! "Abortion saves Lives!" ይላል በአሜሪካ ውርጃ እንደዚህ በአደባባይ የሚደገፍ ነገር መሆኑ ነዉ!
ከላይ ያለውን: screenshot አድርጌ ያገኘሁት: Torch of Christ Ministry ዛሬ January 5 ከለጠፉት ልጣፍ ነዉ!
#GetReady!
#PrepareForRapture!
#PrepareForTheDayOfTheLord
#የእግዚአብሔር ልጆች ተዘጋጁ!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉ለቤተሰቦቻችሁ ማምለጥ ምክንያት መሆን!
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
“እግዚአብሔርም ኖኅን አለው፦ አንተ ቤተሰቦችህን ሁሉ ይዘህ ወደ መርከብ ግባ፤ በዚህ ትውልድ በፊቴ ጻድቅ ሆነህ አይቼሃለሁና።”
— ዘፍጥረት 7፥1
👉አስተውሉ: እግዚአብሔር ጻድቅ ሆኖ ያገኘው: ኖኅን እንጂ የኖኅን ቤተሰቦች አይደለም: ነገር ግን: የቤቱ ራስ የነበረው ኖኅ በእግዚአብሔር ፊት ትክክልኛ ሆኖ ስለተገኘ: ቤተሰቦቹ ሁሉ ከጥፋት ውሃ ዳኑ!
👉ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ የእግዚአብሔር መንፈስ እንደተናገረኝ: በመጣው አድስ ወቅት: ከጥፋቱ ድነው በእግዚአብሔር ፊት በጽድቅ በልብ ሰላም እና በሐሴት መኖር የሚችሉ ሰዎች: እውነተኛ መንፈሳዊነትን የሚለማመዱ ሰዎች ብቻ ናቸው! ሌሎቹስ ካላችሁኝ: እጅግ የሚያስጨንቅ ዘመን በራሳቸው ላይ ነው: እውነተኛ መንፈሳዊነትን የማይለማመዱ ሰዎች ሁሉ መቆም ባለመቻል ዝለው ይወድቃሉ: የተረፉት ደግሞ: በጭንቀት: በሐዘን ይደክማሉ: በዚህ ጊዜ ነዉ: አመጽ የሚበረታው። ነገር ግን ኖኅ ለቤተሰዎች ሁሉ የማምለጫ በር እንደሆነ ይህንን የምታነቡ የእግዚአብሔር ልጆች: እናንተም ለቤተቦቻችሁ በር እንድትሆኑ ትጉ! ኢያሪኮ በእስራኤል አምላክ እና ልጆች ፊት እንደ ገለባ ክምር ስትፈርስ እንደ እብቅ ስትበተን: ጋለሞታይቱ ረዓብ ግን ቤተሰቦቿን ይዛ: ከማይታዘዙ ጋር በእምነት አልጠፋችም!!!
👉በጌታ ስር እንስደድና እንጽና: እንደግ ሕይወቱም በእኛ ይብዛ: በቃሉ ላይ እንመስረት: በጸሎት በመትጋት እውነተኛ መንፈሳዊነትን መለማመድ እንቀጥል! ከእኔ የተነሳ: ቤተሰቦቼ በጽድቅ በልብ ሰላም በሐሴት ይኖራሉ: አይጠፉም: በሚያስጨንቅ ዘመን እንኳ በምድር ላይ እንበዛልን! እንበለጽጋለን! አሜን አሜን!
- 𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሉቃስ 21
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤
²⁶ ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና።
👉ይህ ስለ ሰዎች ነዉ። የእግዚአብሔርን ሕይወት የተካፈልን እኛ ግን: በተካፈልነው ሕይወት እያደግን በዚህም በሚያስጨንቅ ዘመን ፍጹም በሆነ የልብ ሰላም እና ሐሴት እንኖራለን! ደግሞም ተነስተን እናበራለን! የጨለማ መበርታት ለብርሃን አድል ነዉ😊።
የእምነት አዋጅ
👇👇👇👇👇
(👉ከእግዚአብሔር በመወለድ የአምላክን ሕይወት ተካፍያለሁ! በየትኛውም ወቅት: ከጊዜው በላይ ነኝ! የምነሳበት እና የማበራበት ጊዜዬ ነዉ! ፍርሃት በእኔ በፍጹም ቦታ የለውም!😁 አሜን! ሃሌሉያ😆😆😆)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የእግዚአብሔር ልጆች በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ልንገራችሁ: ከእግዚአብሔር ጋር ተጣበቁ! የእግዚአብሔርን ሕይወት መለማመድ ጀምሩ: ቀጣዩ ወቅት: የሰው ሕይወት የማይሰራበት ጊዜ ነዉ።
-𝓹𝓻𝓸𝓹𝓱𝓮𝓽 𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
1 810
✍️ኢየሱስ ብቻ❗️
...መንገድ እውነት ሕይወት -ዮሐንስ 14:6
👉ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅ: እግዚአብሔርን( ያልተፈጠረውን ፈጣሪ) ለማወቅ፣ ለማየት እና ለማግኘት ጥልቅ ፍላጎት ያደረበት ፍጡር ነው: ይህ መልካም እና እግዚአብሔር በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ያኖረው ነዉ: ምንጩን ማወቅ የማይፈልግ ማን አለ? የማያስተውሉ እንስሳት እንኳ ይህንን ስለሚያውቁ አሳ ከባህር ዛፍ ከምድር አይነቀሉም: ሕልውናቸው በመገኛቸው ላይ የተደገፈ በመሆኑ ነዉ። የሰው ልጅ ያልተፈጠረው ፈጣሪ ከፈጠራቸው ፍጡራን ሁሉ የላቀ እና የከበረ ነው: እውቀት ነጻ ፈቃድ እና ስሜትም አለው: በዚህ ምክንያት ምንጩ ከሆነው ከአምላክ ጋር ለመቆየት አልቻለም: ከገነት ከወጣ በኋላ ከምንጩ ተለያይቶ ባዶ መሆኑ በጥልቀት ስለገባው: ባዶነት ስጮህበት ከዚህ የውስጥ ጩሀት ማምለጥ ግብ አድርጎ: ባለመታዘዝ የተለየውን ምንጩን ፍለጋ ተያይዞታል: ብሆንም ግን የማይነጥፍ ፍቅር ያለው: አምላክ ከሰው ልጅ የራቀ አልነበረም። መጽሐፍ ስለዚህ እንደዚህ ይላል:
ሐዋርያት 17 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁶ የሰውን ዘር ሁሉ ከአንድ ወገን ፈጥሮ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ አደረገ፤ የዘመናቸውን ልክና የመኖሪያ ስፍራቸውንም ዳርቻ ወሰነላቸው።
²⁷ ይኸውም ሰዎች እግዚአብሔርን ፈልገው ተመራምረው ምናልባት ያገኙት እንደሆነ ብሎ ነው፤ ይህም ቢሆን እርሱ ከእያንዳንዳችን የራቀ ሆኖ አይደለም።
👉አምላክ ከሁሉም ሰው የራቀ አይደለም: ነገር ግን ኃጢአት የሰው ልጅ አምላክን እንዳያውቅ እንዳያይ እና ከአምላክ ጋር ህብረት እንዳይኖረው ሰውን ከአምላክ የሚለይ ግንብ ሆኖል!
“ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፥ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል።”
— ኢሳይያስ 59፥2
👉የሰው ልጅ ግን ስለ አምላክ የጽድቅ የፍርድ የፍትህ እና የእውነት ጥማት ሳይረዳና ከኃጢአቱ ሳይነጻ አምላክን ለማወቅ እና ለመገናኘት: የራሱን መንገድ ማበጃት ተያይዞት ቀጠለ: በዚህም ከእውነተኛ እውቀት በጸዳ ፍለጋው ውስጥ ለሰይጣን ማታለልም በመውደቅ: ራሱን ለስህተት አሳልፎ ሰጠ: አስተውሉ ሰይጣን የእግዚአብሔር ጠላት ነዉ: ይህንንም ጠላትነቱን የሚገልጸው አምላክ በመልኩ እና በምሳሌው የፈጠረውን ሰው: በማሰናከል እና ከእውነት በመለየት ነዉ። የሰው ልጅ: አምላክን ለማወቅ ለማየት እና ለመገናኘት የነበረው ፍላጎት መልካም ቢሆንም የእግዚአብሔርን ባሕርይ ያላገናዘበ ነበር: በዚህ ፍለጋ ውስጥ ነዉ: ካላይ እንደጠቀስኩት በሰይጣን ውሸት በመታለል ለራሱ አማልክት ማበጀት: ያበጃቸውን ማምለክ: ራሱን ማምለክ: የተፈጠሩ ነገሮችን ማምለክ እና በተፈጠሩ ነገሮች ምሳሌ የተቀረጹ ነገሮችን ማምለክ እና ማገልገል የጀመረው።
👉እግዚአብሔር ግን ዓለሙን እንዲሁ በመውደድ: ራሱ የሚታወቅበትን የሚታይበትን እና የሚገኝበትን መንገድ አቀረበ: ይህንንም ለማድረግ ከብዙ ዘመን በፊት ለራሱ የተለየን ወገን መረጠ: ለዚህም ወገን ሕግንና ነቢያትን በመስጠት ስለሚመጣው እና አሕዛብ ሁሉ ስለሚባረኩበት ዘር "መሲሕ" ወንጌልን ሰበከ: በትክክለኛውም ጊዜ ይህንን ዘር ወደ ምድር ላከው: ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ወይም "አማኑኤል" ይሉታል ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ በተነገረው መሰረት: #የእግዚአብሔር_አካላዊ መገለጥ የሆነው ዘር ተወለደ! ለ 33 ዓመት ተኩል ምድር ላይ በመመላለስ: በመልኩ የፈጠራቸውን እና ከእረኛው ጠፍቶ እንደምቅበዘበዝ በግ: ባለማወቅ የነፍሱ እረኛ ከሆነው ከአምላኩ ጠፍቶ የአውሬዎች መጫወቻ የሆነውን የሰው ልጅ ፈለገ: እውነትን ገለጠ: ሕይወትን ሰጠ: ሰው ዘመኑን ሁሉ ስፈልገው የነበረውን አምላክ ለሰው ሁሉ አስታወቀ: መንገድም ሆነ!
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6
👉ኢየሱስ ብቻ መንገድ!
👉ኢየሱስ ብቻ እውነት!
👉ኢየሱስ ብቻ ሕይወት!
✍️ሌላው ሁሉ ገደል!
✍️ሌላው ሁሉ ውሸት!
✍️ሌላው ሁሉ ሞት!
(ይህ የማይለወጥ እና ዘላለማዊ ነዉ! በኢየሱስ ከልሆነ ያልተፈጠረውን ፈጣሪ ለማወቅ ለማየት እና ለማግኘት የሚደረግ: ነገር ሁሉ ኃይማኖትም በሉት ፍልስፍና ገደል: ውሸት እና ሞት ነዉ! የሰው ልጅ ሆይ "ፈጣሪህ ራሱ ያቀረበውን መንገድ እውነት እና ሕይወት እነድትቀበል: እና እንድታምን እነግርሃለሁ! እምቢ የምትል ከሆነ: ግን: ተመልከት! ተደነቅ! ጥፋ!!!)
ለማያምኑ ሰዎች አጋሩ!
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
Join👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉የማይቋረጥ የመንፈስ ቅዱስ ሕልውና ውስጥ መኖር!!!!
ᴇɴᴛᴇʀ 𝚒𝚗𝚝𝚘 𝚝𝚑𝚎 𝙥𝙧𝙚𝙨𝙚𝙣𝙘𝙚 𝙤𝙛 ɢ𝙤𝙙, 𝚜𝚝𝚊𝚢 𝚝𝚑𝚎𝚛𝚎, 𝚕𝚒𝚟𝚎 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝚕𝚒𝚏𝚎 𝚏𝚛𝚘𝚖 𝚝𝚑𝚎𝚛𝚎 𝚊𝚗𝚍 𝚋𝚎 𝚊 𝚋𝚕𝚎𝚜𝚜𝚒𝚗𝚐 𝚝𝚘 𝚘𝚝𝚑𝚎𝚛𝚜.
-𝓿𝓲𝓬𝓽𝓸𝓻
ወደ እግዚአብሔር መገኘት ግቡ እዚያው ቆዩ ሕይወታችሁን ከመገኘቱ ኑሩ: እናም ለሌሎች በረከት ሁኑ።
በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ ያለማቋረጥ የመኖር ሚስጢር!
✍️የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች አንድ መረዳት ያለባችሁ እውነት: በአዲሱ ኪዳን: እንደ ብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር መንፈስ በእኛ ላይ እየወረደ ተመልሶ እንደማይሄድ ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ስናገር "የእግዚአብሔር መንፈስ እንደ እርግብ ወረደበት አረፈበትም ይላል" -ማቴዎስ 3:16
✍️አንድ መንፈስ ቅዱሳን የተቀበለ ክርስቲያን በቀጣይነት መንፈስ ቅዱስ በሕይወቱ ይኖራል: ምክንያቱም ጌታ "“...እርሱም ከእናንተ ጋር ለዘላለም የሚኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥16 ብሏልና! መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር ለዘላለም ነዉ የሚኖረው።
✍️ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን እንዳናሳዝነዉ መጠንቀቅ አለበን! መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስን አታሳዝኑ ይለናል: ከዛም በላይ ደግሞ መንፈስን አታጥፋ ይለናል! ይህንን እንዳናደርግ መጠንቀቅ አለበን! እንዴት?
✍️በቀጣይነት ያለማቋረጥ መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን የመኖሩን: እውነት በማወቅ እና በእምነት ከእርሱ ጋር ሕብረት በማድረግ ነዉ! መንፈስ ቅዱስ በማይናወጥ ታማኝነቱ: ሕብረቱን ይሰጠናል: ክርስቶስን በእኛ ላይ እስክቀርጸው: ይተጋል! በየጊዜው ኢየሱስ ክርስቶስ ካለው እየወሰደ ለእኛ በመናገር: ወደ መለኮት ሕብረት ይጋብዘናል!
✍️ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በቀጣይነት ሕብረት የሚያደርግ ሰው: ለሌሎች በረከት ይሆናል! አሜን!
“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥14
join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
When we walk with the lord
In the light of his word,
What a glory he sheds on our way
When we do his good will
He abides with us still and
With all who trust and obey!
Trust and obey for there is no other way,
To be happy in Jesus but to trust and obey!
-my voice is just amazing, aa! Try not to undermine yours😁😂
The song i love the most!😍
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ማርቆስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹-¹² እንዲህም አላቸው፦ ለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግሥት ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፤ በውጭ ላሉት ግን፥ አይተው እንዲያዩ እንዳይመለከቱም፥ ሰምተውም እንዲሰሙ እንዳያስተውሉም፥ እንዳይመለሱ ኃጢአታቸውም እንዳይሰረይላቸው ነገር ሁሉ በምሳሌ ይሆንባቸዋል።
…
³³ መስማትም በሚችሉበት መጠን እነዚህን በሚመስል በብዙ ምሳሌ ቃሉን ይነግራቸው ነበር፤ ያለ ምሳሌ ግን አልነገራቸውም፥
³⁴ ለብቻቸውም ሲሆኑ ነገሩን ሁሉ ለገዛ ደቀ መዛሙርቱ ይፈታላቸው ነበር።😊
