uz
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Kanalga Telegram’da o‘tish

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Ko'proq ko'rsatish
1 810
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
You can't be worded and prayerless. The WORD is fuel for prayer.🔥 ~Pastor Paul Enenche በእግዚአብሔር ቃል የተሞላ ሰው አለመጸለይ አይችልም። የእግዚአብሔር ቃል የጸሎት ነዳጅ ነዉ።🔥

“ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።”— መዝሙር 68፥31 ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር አንስታ ሪቫይቫል መቀበል ከቻለች እውነት ነው ዓለም ይባረካል!😭 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የተወደዳችሁ የዛሬው ጥናት በጽሑፍ ነው የቀረበው ሙሉውን እንድታነቡት😍

የሮሜ ጥናት አምስተኛው ትምህርት: 4፥1-4፥25 አብርሃም በእምነት የመጽደቅ ምሳሌ: በእምነት እንጂ በስራ አይደለም። በጠቅላላው የአይሁድ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የያዙ ሰዎች አብርሃምና ዳዊት በስራ ሰይሆን በእምነት የመጽደቅ ምሳሌ ናቸው ---ሮሜ 4፥1-25--- በአራተኛው ትምህርቱ ያብራራውን እውነት ከግምት በማስገባት ሐዋሪያው ጳውሎስ ጥያቄ በመጠየቅ አምስተኛውን ትምህርት ይጀምራል በዚህም ትምህርቱ የእስራኤል አባት የሆነውን አብርሃምንና ታላቁን ንጉሥ ዳዊትን በመጥቀስ እነዚህ ሃያላን እንኳ በስራ ሰይሆን በእምነት የመጽደቅ ምሳሌ እንደሆኑ ያስረዳል። በመጀመሪያ አብርሃም እንዴት ነው የጸደቀው? ---በእምነት የሚገኘውን ጽድቅ በተመለከተ አባት አብርሃም ምን አገኘ? ዘፍጥረት 15፥6 ---እግዚአብሔር የአብርሃምን እምነት ጽድቅ አድርጎ እንደ ቆጠረለት ይናገራል--- አብርሃም የጸደቀው በእምነት ( በእግዚአብሔር ፊት ፀጋን ወይም ሞገስን አግኝቶ) እንጂ በስራ አይደለም --ሮሜ 11፥6--- ፀጋ ለስራችን ምላሽ እንደ ክፍያ የሚገኝ አይደለም። አብርሃም በእምነት የሚገኘውን ጽድቅ በፀጋ ከእግዚአብሔር ከተቀበለ በኋላ የሰራቸው ስህተቶች:- (1) የሚስቱ አገልጋይ ወደነበረችው አጋር በመግባት እስማኤልን ወልዷል--ዘፍጥረት 16-- እስማኤል "የባሪያይቱ ልጅና እንደ ስጋ ልማድ የመጣ ልጅ" ተብሎ ተጠርቷል--- ይህ ማለት እስማኤል የመጣው በስጋዊ መንገድ እንጂ በእግዚአብሔር ፈቃድ አልነበረም ማለት ነው--ገላትያ 4፥23--- (2) አብርሃም በእምነት ከጸደቀ በኋላም አቤሜሌክን በመፍራት ሣራ ሚስቱ እንዳልሆነች በመናገር ዋሽቷል --ዘፍ 20--- ይሄ ቢሆንም ግን እግዚአብሔር በአብርሃም ስህተት ላይ ተመስርቶ ሐሳቡን አልለወጠም ---ሉቃ 22፥31-32 ከለው ሃሳብ ጋር በንጽጽር ተመልከቱ--- በቀደመው ትምህርት የተመለከትነው በእምነት የመጽደቅ ውጤት በአባት አብርሃምም ላይ የሚሰራ ነው ይህም ከትምክህት ነጻ መሆን ነው-- አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን ኖሮ፣ የሚመካበት ነበረው፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት መመካት አይችልም ---ምክንያቱም የጸደቀው በእምነት እንጂ በስራው አይደለም። ሮሜ 4፥4-5: ቁጥር አራት አመክንዮአዊ በሆ አገላለጽ ለሚሰራ ሰው በምላሹ የሚሰጠው ደመወዝ እንጂ ፀጋ(ስጦታ) እንዳልሆነ ያስረዳል ---በመቀጠልም ብዙዎች ኃይመኖተኛ ሰዎች ለመቀበል የሚቸገሩትን እውነት ይናገራል-- “ነገር ግን ለማይሠራው፣ ኃጥኡን ሰው ጻድቅ በሚያደርግ በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቈጠርለታል።” ይሄ እንዴት ይሆናል? በዚህ ትምህርት መጨረሻ ላይ ግልጽ መልስ የሚሰጥበት ጥያቄ ነው። ሮሜ 4፥6-8 (መዝሙር 32፥1-2) ዳዊት በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ጽድቅን ያለስራ ስለሚቆጥርለት ሰው ብፅዕና እየተናገረ ሦስት ሐሳቦችን ይጠቅሳል: 1. የመተላለፍ(lawlessness) ይቅርታ:- ያለፈው ሕግ አልባ የሆነ ድርጊቱ ሙሉ በሙሉ በይቅርታ ታልፏል። 2. የኃጢአት ስርየት:- ኃጢአቱን እግዚአብሔር ላለማየት ሸፍኖታል ወይንም ሙሉ በሙሉ አስወግዶታል። 3. እግዚአብሔር ኃጢአትን አይቆጥርበትም:-ኃጢአት ቢያደርግ እግዚአብሔር ኃጢአቱን አያስብም። ሮሜ 4፥9-12 ---ከላይ የተዘረዘረው በረከት የተገረዙትን ብቻ የሚመለከት ነው ወይም ለአሕዛብም ጭምር ነው? --- አብርሃም እምነቱ ጽድቅ ሆኖ የተቆጠረለት ከመገረዙ በፊት ነው---መገረዝ የጽድቅ ማህተም ነው እንጂ ለመጽደቅ የተደረገ ስራ አይደለም---የትኛው ኢየሱስ ክርስቶስን የመነ ሰው የሚያደርገው ውጫዊ ስራና ስርዓት ያለስራ በእምነት ያገኘው ጽድቅ ምልክት እንጂ ለመጽደቅ የሚደረግ አይደለም--ስራ ያለስራ የተገኘ ጽድቅ ማህተም ነው። አብርሃም እንዴት አባት ሆነ? የአብርሃም አባትነት ለነማን ነው? አብርሃም አባት ለመሆን ያበቃው ብቸኛው ቅድመ ሁኔታ እምነት ነው። በመሆኑም አብርሃም የብዙ ሕዝቦች አባት ነው-- 1. በእምነት ታዘው ለተገረዙት:( አይሁድ) 2. ሰይገረዙ በእምነት ለሚኖሩ:( አሕዛብ) ሮሜ 4፥13-22 እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለዘሩ "ለክርስቶስ" ዓለምን እንደሚወርሱ ተስፋን የሰጣቸው ሕግ ከመሰጠቱ ቢያንስ ከ 430 ዓመት በፊት ነው---ገላትያ 3፥16-18---የተስፋውም መፈጸም በፍጹም ሕግን በመጠበቅ ላይ የተመሰረተ አይደለም--ነገር ግን በእምነት በሆነ ጽድቅ ነው። ሕግ በዓመጽ ሁሉ ላይ የእግዚአብሔርን ቁጣ ያመጣል እንጂ የእግዚአብሔርን ፀጋ ወይም ተስፋ አያስገኝም--4፥14-15-- ሮሜ 4፥18- ተስፋን መቀበል እንዴት ይቻላል? የአብርሃምን የእምነት አካሄድ መከተል የግድ ነው። 1. እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ ምንም አይነት የሚጨበጥ ነገር ሰይኖር በእምነት ተቀበለ። 2. ተስፋ የሰጠው እንጂ እርሱ በራሱ ተስፋውን ማምጣት የማይችል መሆኑን ቢረዳም በእምነት አልደከመም። 3. እግዚአብሔር የሰጠውን ተስፋ ሰይጠራጠር በእምነት የጸና ሆነ--ይህም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። በዚህም ምክንያት አብርሃምና ሣራ በሰውነታቸው የእግዚአብሔርን ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ሃይል ተቀበሉ ተስፋውም ተፈጸመ እግዚአብሔርም ከበረ--- በተጨማሪ ዕብራውያን 11፥11-12-- ሮሜ 4፥23-25 የትምህርቱ መደምደሚያ: ልክ አብርሃም በእምነት እንደጸደቀው: የኢየሱስ ክርስቶስን ሞትና ትንሳኤ ለምናምን ሁሉ ጽድቅ ይቆጠርልናል--- ሞቱ ለእኛ ኃጢአት ዋጋ የከፈለበት ስሆን --- ከሙታን መነሳቱ ደግሞ እርሱ ጻድቅ መሆኑን ያረጋገጠበት ነው---በተጨማሪ የኢየሱስ ከሙታን መነሳት የሚያምኑትን ሁሉ ጽድቅ ያረጋገጠ ነው እኛም ከእርሱ ጋር አንድ ሆነናልና --- ቆላ 2፥11-12፣ ኤፌ 2፥4-6--። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ሰላም ለእናንተ ይሁን የተወደዳችሁ ይሄንን ፖስተር አሁን ወደላችሁበት ግሩፕ እና በinbox ወደምታወሯቸው ሰዎች ሁሉ በመላክ የእግዚአብሔርን ስራ አብረን እንስራ! ስለምትታዘዙ አመስግናለሁ😍

የሮሜ መጽሐፍ ጥናት የብዙዎቻችንን አእምሮ እያደሰ ሕይወታችንን እየለወጠ ያለው የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ዛሬ ማታ 3:ዐዐ ላይ ይቀጥላል! ትምህርቱን ከመጀመሪያው ያልተማራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ቻናሉን
የሮሜ መጽሐፍ ጥናት የብዙዎቻችንን አእምሮ እያደሰ ሕይወታችንን እየለወጠ ያለው የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ዛሬ ማታ 3:ዐዐ ላይ ይቀጥላል! ትምህርቱን ከመጀመሪያው ያልተማራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ቻናሉን በመቀላቀል በድምፅና በጽሑፍ የቀረቡትን ትምህርቶች ተከታተሉ እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ አስተሳሰባችሁን፣ አነጋገራችሁን፣ አካሄዳችሁን፣ አገልግሎታችሁን የሚቀይር ጥልቅ እውነት ተገኙበታላችሁ! የእግዚአብሔር ቃል ፈጽሞ ይለውጣል🔥 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የብዙዎቻችንን አእምሮ እያደሰ ሕይወታችንን እየለወጠ ያለው የሮሜ መጽሐፍ ጥናት ዛሬ ማታ 3:ዐዐ ላይ ይቀጥላል! ትምህርቱን ከመጀመሪያው ያልተማራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ወደ ላይ እየሄዳችሁ በድምፅና በጽሑፍ የቀረቡትን ትምህርቶች ተከታተሉ እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ አስተሳሰባችሁን፣ አነጋገራችሁን፣ አካሄዳችሁን፣ አገልግሎታችሁን የሚቀይር ጥልቅ እውነት ተገኙበታላችሁ! የእግዚአብሔር ቃል ፈጽሞ ይለውጣል🔥 @TheDeepThingsOfGod

ክፍል 2 ~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት" ~ልጅ ዳን። ክፍል 3ን ለማግኘት 👇👇👇 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

🔥እግዚአብሔር ሰዎችን የፈጠረበት ዓላማ ክብሩን ለመግለጥ ነው! ከዚህ ዘላለማዊ ዓላማ መጉደል ነው ኃጢአት። ወንድሞቼና እህቶቼ ሁሉ ቀርቶብን ክብሩ ቢገኝልን አትርፈናል!🔥

ክፍል 1 ~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት" የእግዚአብሔር ክብር ምንድነው? ~ልጅ ዳን። ክፍል 2ን ለማግኘት 👇👇👇 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ቅዱስ አባት ሆይ እባክህ እኔንና ትውልዴን በእውነትህ እና በመንፈስህ ጎርፍ አጥለቅልቀን? እባክህ! 😭

የሮሜ ጥናት 3፥21-31-የእግዚአብሔር መፍትሔ--በእምነት ብቻ የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ-- ሕግና ነቢያት በብሉይ ዘመን አስቀድመው የመሰከሩለት ጽድቅ ነው እንጂ የሐዋሪያው ጳውሎስ የፈጠራ ትምህርት አይደለም ት. ኤር 23:6፣ ት. ኢሳ 61:10--- ይህም ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው። ልዩነት የለም። አሕዛብም ቢሆን አይሁድ ሁሉም ኃጢአተኞች እንደሆኑ አስቀድመው ተከሰዋል---በኢየሱስ ክርስቶስ የቤዛነት(የማዳን) ስራ የሚያምኑ ሁሉ እንዲሁ በነጻ እንዲጸድቁ እግዚአብሔር ወስኗል። ኃጢአት/sin/ ምንድነው? ኃጢአት በጥቅሉ አላማን መልቀቅ ወይንም ከተፈጠሩበት ዓለማ መጉደል ነው። የሰው ልጅ የተፈጠረበት ዓላማ የእግዚአብሔር ክብር ነው--ሮሜ 3፥23--- ከኃጢአት ጋር በተመሳሳይ መልኩ የሚታይ ነገር ግን ትንሽ ልዩነት ያለው ቃል: በደል/transgression/ ምንድነው? በደል በግልጽ የተሰመረን መስመር እያወቁ ጥሶ ማለፍ ወይንም በሌላ አገላለጽ የተጻፈውንና የተገለጠውን ሕግ አለመታዘዝ ማለት ነው። እግዚአብሔር የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እንዲፈስ ያደረገባቸው ሦስት ምክንያቶች: 1)-ለብዙ ዘመናት በትዕግስት ያለፈው የሰዎች ኃጢአት ላይ ቁጣውን ለመግለጥ--- 2)-እግዚአብሔር ኃጢአትን በመቅጣት ጽድቁን መግለጥ ስላለበት ኢየሱስን የማስተሰረያ መስዋዕት በማድረግ ጽድቁን ገልጧል--- 3)-በአሁኑ ዘመን በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ኃጢአተኞችን እርሱ እራሱ ጻድቅ ሆኖ ማጽደቅ እንዲችል ነው ወይም የእርሱን ጻድቅ መሆን ጥያቄ ውስጥ በማያስገባ መልኩ የሚያምኑ ኃጢአተኞችን ለማጽደቅ ነው--ሮሜ 3፥25-26--- በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በጸጋ የመጽደቅ ውጤት በሰዎች ላይ: ---ትምክህትን/ትዕቢትን/ ማስቀረት---ምክንያቱም ይህ ጽድቅ የተገኘው ሕግን በመፈጸም ሰይሆን ኢየሱስ የፈጸመውን በማመን ነው---ለትምክህትና ለትዕቢት ምንም አይነት ቦታ የለም--- የሮሜ መልእክት አንዱ ማእከላዊ ሐሳብ:-“ማንም ሰው ሕግን በመፈጸም ሳይሆን፣ በእምነት እንደሚጸድቅ እናረጋግጣለን።” — ሮሜ 3፥28 ሕግ ለአይሁድ ብቻ የተሰጠ ነበር---በእምነት የሚገኘው ጽድቅ ግን ለአይሁድም ለአሕዛብም በነጻ የተሰጠ ነው---እግዚአብሔር የሁሉም አምላክና አንድ ብቻ ነው (ይሄ አይሁድ አጥብቀው የሚያምኑትና የሚናገሩት እውነት ነው) ---ይሄንን በአይሁድ እምነት የሚዘወተር አረፍተ ነገር በመጥቀስ ሐዋሪያው አይሁድ ለማመን የሚቸግራቸውን እውነት ይናገራል --- አሕዛብም ልክ እንደ አይሁድ በእምነት ይጸድቃሉ። የዚህ ምዕራፍ የመጨረሻው ቁጥር ጥያቄና መልስ ነው(የአይሁድ የተለመደ የአነጋገር ስርዓት) ---ጽድቅ በእምነት የሚገኝ ከሆነ ሕግን ዋጋ የሌለው እናደርገው ይሆን?---ሐሳብህ ይጥፋ! ጽድቅ በእምነት ስገኝ ሕግ ይጸናል እንጂ ዋጋ የሌለው አይሆንም--- ሕግን በሙላት ዋጋ እንዳለው አምነው መቀበል የሚችሉ ሰዎች ሕግ የተፈጸመላቸው ሰዎች ናቸው---ኢየሱስን የሚያምኑ ሰዎች ደግሞ ያመኑት እርሱ ሕግን ፈጽሞላቸዋል። በኢየሱስ ደም በእምነት ከተገኘው ጽድቅ የተነሳ እጅግ ሐሴት ማድረግ አለብን: “በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፤ ነፍሴ በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች፤ ሙሽራ ራሱን እንደሚያሳምር፣ ሙሽራዪቱም በዕንቆቿ እንደምታጌጥ፣ የድነትን ልብስ አልብሶኛል፤ የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛል።” — ኢሳይያስ 61፥10 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ክፍል 3 ~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት" የእግዚአብሔር ክብር እንዴት ማየት ይቻላል? ~ልጅ ዳን 🔺🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🀄️🔺 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ክፍል 1 ~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት" የእግዚአብሔር ክብር ምንድነው? ~ልጅ ዳን። ክፍል 2ን ለማግኘት 👇👇👇 〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

የእግዚአብሔር ክብር ምንድነው? ከሮሜ ጥናት ጋር ልንማረው የሚገባ እውነት ነው።

Justified:- Just as if I'd never sinned!

የሮሜ ጥናት 3፥21-31 (አራተኛው ደረጃ) እግዚአብሔር ያቀረበው መፍትሔ (በእምነት የሚገኝ የእግዚአብሔር ጽድቅ) 👇👇👇ተቀላቀሉን 👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

ዛሬ ማታ 3:00 የሮሜ ጥናት 3፥21-31 (አራተኛው ደረጃ) እግዚአብሔር ያቀረበው መፍትሔ (በእምነት የሚገኝ የእግዚአብሔር ጽድቅ) በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑትን ኃጢአተኞች ጻድቁ እግዚአብሔር ያጸድቃቸዋል😁 👇👇👇ተቀላቀሉን 👇👇👇 @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

እስከ አሁን ድረስ በመጀመሪያዎቹ ሦስት ምዕራፎች ሰዎች ሁሉ አይሁድም ቢሆኑ አሕዛብ ዓመጸኞች እና ኃጢአተኞች እንደሆኑ ሐዋሪያው ጳውሎስ ከሷቸዋል። አሕዛብ ሕሊና አይሁድም ሕግ የተሰጣቸው ቢሆንም ለእግዚአብሔር ስላልታዘዙ ማመካኛ የሌላቸው መሆኑና በእግዚአብሔርም ፊት መጽደቅ የተሳናቸው እንደሆኑ ተመልክተናል። በዚህ ምክንያ ዓለም ሁሉ ጻድቅ ከሆነው ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች እንደሆኑ ተምረናል። እግዚአብሔር ጻድቅ ፈራጅ በመሆኑ ፍርዱ አይቀሬ ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር ሰዎች ከዚህ የሚድኑበትን መንገድ አዘጋጅቷልን? አዎ። በሁሉም አይነት ክፋትና ዓመጽ ለተሞላ እና ለወደቀ ሰው ፍቅሩን የገለጠው በዚህ መንገድ ነው። በቀጣይ እግዚአብሔር ሰዎችን ለማጽደቅ ያዘጋጀውን አዲስ መንገድ እንመለከታለን። @TheDeepThingsOfGod @TheDeepThingsOfGod

በጣም በሚያስገርም ሁኔታ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ዓመት ተኩል ሲያስተምር አንድም ቀን አነቃቂ ስብከት ሰብኮ አያውቅም እንደውም ትምህርቱ "ይሄንንማ ማን ልቀበለው ይችላል?" የሚያስብል ነበር። በሁሉም አይነት ክፋት ለተሞላ የአዳም ልጅ አነቃቂ ንግግር የምትሰብክ ቤተክርስቲያን እያየሁ እንዴት አላለቅስ😭