uz
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Kanalga Telegram’da o‘tish

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Ko'proq ko'rsatish
1 810
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
Ma'lumot yo'q30 kun
Postlar arxiv
ሁላችሁም ይህንን መልእክት እንድትሰሙት! መሰረታዊ መልእክት ነዉ!

#VictorWisdom! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit
#VictorWisdom! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit

መጽሐፍ ቅዱሴን እንዴት ለንብብ? (#መንፈሳዊ ንባብ) -ይህንን መልእክት ከሰማችሁት እና መርሁን ከተከተላችሁ: ከመጽሐፍ ቅዱስ ሕይወት ታተርፋላችሁ! ስሙት! 🦋🔥Transfiguration 🔥🦋 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#ቃሉን_የማነበው_እስከ_መች_ነው!!?? .... በቀንም በማታ የማስበው አነብንቤ ብቻ የማላልፈው የእግዚአብሔርን ቃል የማነበው . . . ህይወቴን እስኪቀይረው ነው ገብቶኝ በኑሮዬ እስክኖረው!!! (( 🐛........🦋))

ይህንን መዝሙር ለእግዚአብሔር ዘምሩለት: -እግዚአብሔር በማደሪያው ያለ:... @አዜብ ሃይሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“በብዙ ሌላ ቃልም መሰከረና፦ ከዚህ ጠማማ ትውልድ ዳኑ ብሎ መከራቸው።” — ሐዋርያት 2፥40

እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስን በእኔ ያከብረዋል! በአንተም በአንቺም እንድያከብረው እጸልያለሁ!🔥🔥🔥 @TheDeepThingsOfTheSpirit

#መጽሐፍ_ቅዱሴን_እወደዋለሁ!!!😍 ተወዳጆች ሆይ የህይወትን መንገድ ማወቅ ከወደዳችሁ ይህንን ማስተማር የሚችል ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚወዳደር መጽሐፍ የለም። 👉መጽሐፍ ቅዱስ ስለ አምላክ: ስለ ሰዉ ልጅ: ስለ ሰይጣን ስለ መልአክት ስለ ሌሎች ፍጥረታት እንድሁም ስለምታየው እና ስለማይታየው ትክክለኛው እውቀት ይሰጣል። 👉ከሁሉም በለይ ደግሞ ለሰው ልጅ ጥቅም: ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ሕይወት የሚገኝበትን ጥበብ ይሰጣል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ችግሩን የፈጠረው ሰው መፍትሔውን ይዛ ከመጣ ትርፍ ለማግኘት የምደረግ ጨዋታ ነዉ: ያንን ሰው አትመኑት! ጠቢባን ሁኑ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር ልጆች ፀጋ ይብዛላችሁ! ክፋ አይነካችሁም: በዘመናችሁ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ሐሴት በእናንተ ይሁን! እወዳችኋለሁ!😍 @TheDeepThingsOfTheSpirit

የተቀባ መዝሙር ነዉ: ዝም ብላችሁ ስሙት! -You are all that matters!🔥🔥🔥 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ክርስቲያን ነህ/ነሽ? ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ✍️ዛሬ ለይ እጅግ ብዙ ቁጥር ያለው ሰው "ሃይማኖትህ ምንድነው?" የሚል ጥያቄ ከጠየቃችሁት ያለመረዳትና በልምድ "ክርስቲያን ነኝ" ይላል: አንዳንዱ ሰው ኦርቶዶክስ ስለሆነ ክርስትያን የሆነ ይመስለዋል: ሌላው ደግሞ ጴንጤ መሆን ክርሰቲያን መሆን ይመስለዋል: እውነታው ግን ከዚህ የራቀ ነዉ። ኦርቶዶክስም ሆነ ጴንጤ( Protestant) ሰዎች ቤተክርስቲያንን ተቋማዊ መልክ እንዲኖራት የሰየሙላት የተቋም ስም እንጂ የክርስትና ክልል አይደለም: ወይም እግዚአብሔራዊ የሆነ የእውነተኛ ቤተክርስቲያን ምልክት አይደለም! ታዲያ ክርስቲያን ማነው? ክርስቲያን ማለትስ ምን ማለት ነዉ? ለዚህ ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠንን መልስ ካየን በኃላ ብዙዎቻችን እራሳችንን እንደምንፈትሽ እና "የእውነት ክርስቲያን ነኝ?" ብለን እንደምንጠይቅ አልጠራጠርም! 👉ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ "ክርስቲያን" የሚል ቃል የተጠቀሙት በአንጾኪያ ነበር: በዚህ ጊዜ ቤተክርስቲያን በእስጢፋኖስ ላይ ከደረሰው ሞት የተነሳ ታላቅ ስደት ውስጥ ገብታ ነበር: የተበተኑት ቅዱሳን ቃሉን እየሰበኩ አንጾኪያ ደርሰው በዚያ ለነበሩ ግሪኮችም ቃሉን ሰበኩ: ከዚህ በኃላ በኢየሩሳሌም የነበረችው ቤተክርስቲያን ባርናባስን ወደ አንጾኪያ ላከችው: እርሱም "በልባቸው ፈቃድ በጌታ ጸንተው እንድኖሩ" ከመከራቸው በኃላ "ጳውሎስን" ፍለጋ ወደ ጠርሴስ መጥቶ አገኘው: ወደ አንጾኪያም ይዞት ተመለሱ: ከዛም በአንጾኪያ የነበረችውን ቤተክርስቲያን "አንድ አመት ሙሉ የጌታን መንገድ አስተማራቸው!" በዚህ ጊዜ ነዉ ለመጀመሪያ ጊዜ "#ደቀመዛሙርት" ክርስትያን የተባሉት። “ባገኘውም ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ።” — ሐዋርያት 11፥26 👉በዚህ ጥቅስ መሰረት ክርስቲያን የተባሉት እነማን ናቸው? =ደቀመዛሙርት ናቸዉ። ይህ በግልጽ የሚያስረዳን "#ክርስቲያን" የሚለውን የከበረ ስም መግኘት ያለበት "ኦርቶዶክስ" ወይም "ጴንጤ" የሆነ ሰው ሰይሆን "ደቀመዝሙር" የሆነ አማኝ ብቻና ብቻ ነዉ!!!!! ደቀመዝሙር ነህ? ደቀመዝሙር ነሽ? አዎ ከማለታችን በፊት ደቀመዝሙር ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት: "ደቀመዝሙር" የሚለው የቃል ትርጉም "የመምህሩ ብቻ ተማሪ"(A personal student of a teacher" ወይም "የመሪው ብቻ ተከታይ" (A personal follower of a leader) ማለት ነዉ። የኢየሱስ ብቻ ተማሪ ነህ/ነሽ? የኢየሱስ ብቻ ተከታይ ነህ/ሽ? አስደንጋጭ እንደሆነ ግልጽ ነዉ! እውነታው ግን ይሄ ነዉ። ለዚህ ነዉ ኢየሱስ ደቀመዝሙሩ ለመሆን የሚፈልግ ሰው ማድረግ ስላለበት ነገር እንደዚህ የተናገረው: ሉቃስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁶ ማንም ወደ እኔ የሚመጣ ቢኖር አባቱንና እናቱን ሚስቱንም ልጆቹንም ወንድሞቹንም እኅቶቹንም የራሱን ሕይወት ስንኳ ሳይቀር ባይጠላ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም። ²⁷ ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም። የእውነት ደቀመዝሙር ነህ? ነሽ? እናትህ አባትህ የቅርብ የምትላቸው ነገሮች ሁሉ: በእኛ ዘመን ቢሆን ኢየሱስ ስልካችንን ኮምፒውተሮቻችን ሁሉ እንድንጠላ የሚጠይቀን ይሆናል ብዬ አስባለሁ! ይህ ማለት ደቀመዝሙር ለመምህሩና ለአስተማሪው አሰተማሪነት እና መሪነት መሰናክል የሚሆንን የትኛውንም ነገር: እምብ የማለት ግዴታ አለበት! የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ክርስቲያን ነኝ! እንደምንለው ነገሩ ቀላል አይደለም! ደቀመዝሙር መሆን ይጠይቃል! ደቀመዝሙር መሆን ደግሞ ዋጋ ያስከፍላል! ይህም ቢሆን ከምንቀበለው ሽልማት ጋር ስነጻጸር የምንከፍለው ዋጋ ምንም እንደሆነ እቆጥራለሁ! ጸጋ ይብዛላችሁ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሰላም የእግዚአብሔር ልጆች ዛሬ ጥያቄ ልጠይቃችሁ ነዉ: ክርስትያን ነኝ ስትሉ ምን ማለታችሁ ነዉ? ክርስትያን ምን አይነት ሰው ነው? መመለስ የምትችሉ ሁላችሁ መልሱ Comment ለይ: እና እንወያይ? እስከ ማታ ድረስ...

የአስተሳሰብ ስርዓታችን እንደ እግዚአብሔር ቃል ካልሆነ ፍጹም ለውጥን መለማመድ ምኞት ብቻ እንደሆነ ይቀራል! አንድ ሰው ግን የአስተሳሰብ ስርዓቱን በእግዚአብሔር ቃል መገንባት ከቻለ ፍጹም ለውጥን እሁን ማድረግ ይችላል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🦋🔥ፍጹም ለውጥን እሁን የምናደርግበት ቀላሉና ብቸኛው መንገድ!*🔥🦋 ቀጣዩን ለመስማት ተቀላቀሉን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🔥የእግዚአብሔር ቃል🔥 👉በእውነተኛ የክርስትና እምነት ውስጥ ለትምህርቶቻችን ለመንፈሳዊ ለልምምዶቻችን: ለአስተሳሰብ ስርዓታችን ብሎም ለምንናገርበት መንገድ በአጠቃላይ ለምንኖረው የሕይወት አይነት ትክክለኛው መለኪያ(Standard), የእግዚአብሔር ፈቃድ የተገለጠበት መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ እንደሆነ ታውቃላችሁ? 👉መጽሐፍ ቅዱስን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በቀጣይነት የማያጠና ሰው ፍጹም( genuine) የሆነ የክርስትና ሕይወት ልኖረው በፍጹም አይችልም! 👉ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በቂ ጊዜ የማያሳልፍ አማኝ: በትምህርት ንፋስ የሚፍገመገም: የአስተሳሰብ ስርዓቱ ጨርሶ በእውነት ያልተገነባ ከዓለም እና ከኃጢአት በታች የሆነ ብሎም ለሰይጣን ሽንገላ የተጋለጠ ልሆን ይችላል! ደግሞም ይሆናል: ለምን? ምክንያቱም "የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደሆነ አያውቅም" በዚህ ምክንያት በዓለም ውስጥ ያሉትን ይመስላል። 👉የለ እግዚአብሔር ቃል መረዳት በፍጹም እውነተኛ የክርስቲያን ሕይወት መኖር አይቻልም! "ቃሉ በሙላት ይኑርባችሁ!" 👉የእኛ የራሳችን አስተሳሰቦች ምልከታዎች ወይም ስሜቶች አሁን ያለንበት ሁኔታዎች በፍጹም ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ለውድድር የሚቀርቡ አይደሉም! እኛ በሕይወታችን ብንገልጠውም በንገልጠውም የእግዚአብሔር ቃል በራሱ እውነት ነዉ! በራሱ እውነት እንደሆነ ይኖራል! ከእኛ ሁኔታ ተነስተን የእግዚአብሔርን ቃል ለመተንተን የሚደረግ ጥረት የስህተቶች ሁሉ መጀመሪያ ነዉ! 👉የእግዚአብሔርን ቃል መንፈስ ቅዱስ እንዳለው አንብቡት እመኑት አሰላስሉት ከዛም አውጁ በዚህ መንገድ የእግዚአብሔርን ቃል በሕይወታችን እንድሰራ ማድረግ ይቻላል! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

2ኛ ጢሞቴዎስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ነገር ግን በመጨረሻው ቀን የሚያስጨንቅ ዘመን እንዲመጣ ይህን እወቅ። ² ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ ይሆናሉና፥ ገንዘብን የሚወዱ፥ ትምክህተኞች፥ ትዕቢተኞች፥ ተሳዳቢዎች፥ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፥ የማያመሰግኑ፥ ³ ቅድስና የሌላቸው፥ ፍቅር የሌላቸው፥ ዕርቅን የማይሰሙ፥ ሐሜተኞች፥ ራሳቸውን የማይገዙ፥ ጨካኞች፥ መልካም የሆነውን የማይወዱ፥ ⁴ ከዳተኞች፥ ችኩሎች፥ በትዕቢት የተነፉ፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ ይሆናሉ፤ ⁵ የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። ⁶-⁷ ወደ ቤቶች ሾልከው እየገቡ፥ ኃጢአታቸው የተከመረባቸውን በልዩ ልዩ ምኞትም የሚወሰዱትን ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደ ማወቅ ሊደርሱ ከቶ የማይችሉትን ሞኞችን ሴቶች የሚማርኩ፥ ከእነዚህ ዘንድ ናቸውና። ⁸ ኢያኔስና ኢያንበሬስም ሙሴን እንደ ተቃወሙት፥ እንዲሁ እነዚህ ደግሞ አእምሮአቸው የጠፋባቸው ስለ እምነትም የተጣሉ ሰዎች ሆነው፥ እውነትን ይቃወማሉ። ⁹ ዳሩ ግን የእነዚያ ሞኝነት ደግሞ ግልጥ እንደ ሆነ፥ ሞኝነታቸው ለሁሉ ይገለጣልና ከፊት ይልቅ አይቀናላቸውም። ¹⁰ አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤ ¹¹ በአንጾኪያና በኢቆንዮን በልስጥራንም የሆነብኝን የታገሥሁትንም ስደት ታውቃለህ፤ ጌታም ከሁሉ አዳነኝ። ¹² በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ። ¹³ ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ። ¹⁴ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤ ¹⁵ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። ¹⁶-¹⁷ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። @TheDeepThingsOfTheSpirit

እትዮጵያ! እትዮጵያ! እትዮጵያ! ስሙት; እና ጸልዩ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Blessed are you! ( English + Hebrew) be blessed! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።” — ዮሐንስ 6፥63