TheDeepThingsOfGod
Kanalga Telegram’da o‘tish
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Ko'proq ko'rsatish1 810
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
1 810
መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄና በቀጣይነት ስትመረምሩ እና በተረዳችሁት እውነት ስትኖሩ የታደሰ አእምሮ ባለቤት፥ የተለወጠ ሕይወት ነዋሪ፥ ዓለምን የማይመስልና ከእግዚአብሔር ጋር ተባባሪ ሰዎች ትሆናላችሁ።
-Victor
1 810
ፓስተር ታምራት ሃይሌ ~ መጽሐፍ ቅዱስ እና ስልክ...
አባታዊ ምክር ለወጣቶች እና ለክርስቲያኖች ሁሉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከዚህ ይጀምራል።
መጽሐፍ ቅዱሱን ከፎቶ የማያነብ ክርስቲያን እግዚአብሔር እየተናገረኝ አይደለም ማለት አይችልም።
መጽሐፍ ቅዱሱን የሚያነብ ሰው እግዚአብሔር እንዴት እንደሚናገር ድምጹም ምን እንደሚመስል በትክክል ያውቃል፥ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ የእግዚአብሔር ድምፅ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ውስጥ እና መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ።
ወዳጄ A:-መንፈስ ቅዱስ #በእኛ_ውስጥ የለም እንደ ቆይ??
እኔ:-አለ! ዳግም ስለተወለድን #በእኛ_ውስጥ አለ።
ወዳጄ A:-ታዲያ ለምንድነው ወንጌል ስንሰብክ በእኛ #ድንቆች፣ #ተዓምራቶች እና #ምልክቶች የማይደረጉት??
👉እኔ:-የመንፈስ ቅዱስ #በአንተ_ውስጥ መሆን እና የመንፈስ ቅዱስ #በአንተ_ላይ መሆን ይለያያል።
የመንፈስ ቅዱስ በአንተ ውስጥ መሆን #ለአንተ ሲሆን የመንፈስ ቅዱስ በአንተ ላይ መሆን #ለሌሎች ነው።
መንፈስ ቅዱስ በአንተ ውስጥ የሚሆነው በጌታ አምነህ ስትድን መንፈስህ ዳግም ሲወለድ ነው። የእርሱ(የመንፈስ ቅዱስ) በአንተ ውስጥ መሆኑም ለጽድቅ፣ ለደህንነት፣ ለቅድስና፣ እግዚአብሔርን ለመምሰል እና ከሀጥያት የበላይ የሆነን ህይወት ለማኖር ነው።(#ለአንተ_ጥቅም ነው)
👉የመንፈስ ቅዱስ በአንተ ላይ መሆን ግን ለድሆች ወንጌልን፣ ለታሰሩት መፈታትን፣ለዕውሮች ማየትን፣ ለተጠቁት ነጻ መውጣትን፣ ለታመሙ ፈውስን ትሰብክ ዘንድ ነው።(#ለሌሎች_ጥቅም ነው)
የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ #በእኔ_ላይ ነው፥ #ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤ ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ #ለተማረኩትም ነጻነትን #ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል።”
ኢሳይያስ 61፥1
ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ #በእናንተ_ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ #ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።—ሐዋርያት 1፥8
👉The Spirit of God in you is #for_you; the Spirit of God up on you is #for_others(It will make you heal the sick,deliver the captives,recover the sight to the blind,do miracles & wonders and raise the dead).
✔️Share it
Join @Godsgospel
@Godsgospel
1 810
12/01/2014
አጥብቀን እንጸልይ!
በሌሊት ራዕይ ትላንት በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ላይ አዲስ ዝናብ እየዘነበ ተመልክቻለሁ፥ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ዝናብ በኢትዮጵያ ላለች ለክርስቶስ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን እና ለዚህ ትውልድ የተቀጠረ ነዉ።
የአሁኑ ዝናብ ቤተክርስቲያንን እንዳያልፍ አጥብቀን እንጸልይ!🌧
1 810
በብዙ መልኩ አንድ ሃገር ያለችበት ሁኔታ ቤተክርስቲያን ያለችበትን የመንፈሳዊ ጤንነት ደረጃ ያሳያል፥ ቤተክርስቲያን ያለችበት ሁኔታ ደግሞ እረኞች(አገልጋዮች) ምን አይነት እንደሆኑ ያመለክታል።
-Victor
1 810
-SeekingGod!
-SeekGodForWhoHeIs!
Many seek God for what He has or what He can give, but few seek Him for who He is.
Receive Grace to seek him for who He is, In the mighty Name of Jesus Christ!
ብዙዎች እግዚአብሔርን ስላለው ነገር ወይም ስለሚሰጠው ነገር ይፈልጉታል፥ እጅግ ጥቂቶች ግን ስለማንነቱ ይፈልጉታል።
በሃይለኛው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እግዚአብሔርን ስለማንነቱ የምትፈልጉበትን ፀጋ ተቀበሉ።
1 810
“Let us be glad and rejoice, and give honor to him: for the marriage of the Lamb has come, and his wife has made herself ready.”
— Revelation 19፥7
Are you rapture ready? are you prepared?
https://www.instagram.com/p/CT_9HHGIe34/?utm_medium=share_sheet
1 810
ሰይጣን:- ሁልጊዜ እውነተኛ የክርስቲያን ኑሮ የምትኖር ከሆነ፥ ክርስቶስን በእውነት እና በጽድቅ የምትከተል ከሆነ፥ ወንጌልን አንዳንዴ ለሰዎች አእምሮ የሚመች አድርገህ ከልሰበክ፥ COMPROMISE የማታደርግ ከሆነ ብዙ ነገር ታጣለህ፥ ጓደኛ ታጣለህ፥ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ታጣለህ፥ ወዳጆች ታጣለህ፥ ገንዘብ ታጣለህ... ብቻ ብዙ ነገር ታጣለህ!😂
እኔ:- “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም።” ተብሎ ተጽፏል፥ ሂድ አንተ ሰይጣን🤣😂
ሰይጣን:-😡
1 810
ጥሩ መጀመር ጥሩ መጨረስ ላይሆን ይችላል:
ሰይጣንም የጀመረው ከእግዚአብሔር ጋር ነበር፥ ትልቅ ቅባትም ከእግዚአብሔር ተቀብሎ ነበር፥ ትዕቢት እና ትምክህት ግን አሳተው፥ ከውስጡ እሳት ወጥቶ በላው በሚያዩት ሁሉ ፊት እግዚአብሔር አመድ አደረገው።
በለዓምም የጀመረው ከእግዚአብሔር ጋር ነበር፥ ንጹሕ ነቢይም ነበር፥ የገንዘብ ፍቅር ግን አሳተው እብደቱን እግዚአብሔር በአህያ ተናግሮ እስኪገታ ድረስ ታወረ፥ አህያ ከእርሱ ተሽላ የእግዚአብሔርን መልአክ ተመለከተች፥ በንዋይ ፍቅር ተቃጥሎ የነቢይነት ጥሪውን አበላሸው የእግዚአብሔርን ሕዝብ የሚያስት ትምህርት በማስተማር፥ የሰይጣን መሳሪያ ሆነ።
ሳኦልም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር የጀመረው፥ የንግስና ቅባትም ተቀብሎ ነበር። ትዕግሥት ማጣት አሳተው፥ ፈጥኖ ድል ለማግኘት በማሰብ ለእርሱ ያልተገባ ስራ ሰራ በዚህም አህያ ከሚፈልግበት አንስቶ የቀባውን እግዚአብሔርን በደለ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ተለየው እናም በዘመኑ ሁሉ የአጋንንት መጫወቻ ሆነ።
ዴማስም ከእግዚአብሔር ጋር ነበር የጀመረው፥ የወንጌል ስብከትን ስራው አድርጎ ነበር። ከታላላቆቹ ሐዋሪያት ከነ ቅዱስ ጳውሎስም ጋር አብሮ ሰራተኛ የመሆንን እድል አግኝቶ ነበር፥ የዓለም ፍቅር ግን አሳተው፥ ከሐዋሪያትም ተለይቶ ወደ ተሰሎንቄ ሄደ።
ከምንም በላይ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት እንውደድ፥ እንጠብቅ!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
😭ከቤተክርስቲያን ነጋዴዎችን፥ ሳንቲም ለዋጮችን፥ ችግር ፈቺ መስለው የቤተመቅደሱን ክብር ያረከሱትን፥ በውሸት የሰዎችን ክስ የሚያጸዱትን፥ ወንጌልን ያጣመሙትን፥ የበግ ለምድ ለብሰው መካከል የገቡ ተኩላዎችን ጌታ እየገረፈ የሚያስወጣበት ጊዜ ይመጣል፥ በእውነት መንፈስ እና በእግዚአብሔር ቃል ስልጣን የተሞሉ የእግዚአብሔር ሚስጥር መጋቢዎችና የክርስቶስ ምስክሮች ይነሳሉ።
“ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት ተነሥቶ የሚጀመርበት ጊዜ ደርሶአልና፤ አስቀድሞም በእኛ የሚጀመር ከሆነ ለእግዚአብሔር ወንጌል የማይታዘዙ መጨረሻቸው ምን ይሆን?”
— 1ኛ ጴጥሮስ 4፥17
1 810
ለመጽሐፍ ቅዱስ ያለን ቦታ ለኢየሱስ ያለንን ቦታ ያሳያል፥ ሰው መጽሐፍ ቅዱሱን ከሚወደው በላይ ኢየሱስን መውደድ አይችልም።
