uz
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Kanalga Telegram’da o‘tish

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Ko'proq ko'rsatish
1 810
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
sticker.webp0.25 KB

ከ Revivalists የተነሳ "GOD IS BACK" የተባለበትም ዘመን ነበር! -እግዚአብሔር ሆይ እንደገና አድርገው! በእኛም ዘመን "እግዚአብሔር ወደ ሕዝቡ ተመልሷል ይባል!"😭😭😭 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከባድ የመንፈስ ቅዱስ ዝናብ በዘመናችን ይሆናል! ዝናብ ከሰማይ ወርዶ ምድርን እንደሚያረሰርስ ፍሬም እንድታፈራ፤ ለበላተኛ መብልን ለዘሪም ዘርን እንድትሰጥ እንደሚያደርግ: ልክ እንደዚሁ በስጋ ለባሽ ሁሉ ላይ የሚዘንበው የእግዚአብሔር መንፈስ ነዉ። “ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ #አፈስሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልምን ያልማሉ፥ ጐበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፤” — ኢዮኤል 2፥28 ይህ የመንፈስ ቅዱስ ዝናብ እንድንረሰርስና ከመብራታቸው ጋር ዘይት የሌላቸው እንዳንሆን ፤ለክርስቶስም ፍሬ ማፍራት እንድንችል ያደርገናል! ፈውስ ለሚያስፈልጋቸው ፈውስን! የመፈወስ ሃይል ለሚያስፈልጋቸው ደግሞ የሚፈውስን ሃይል ይሰጣል! ይህን የመንፈስ ቅዱስ ዝናብ ከየትኛውም ጊዜ በላይ መፈለግ ያለብን ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነዉ! ምክንያቱም ከእርሱ ሌላ ምንም ተስፋ የለንም! ፈውስ ያስፈልገናል! ሕዝቦች ፈውስ ያስፈልጋቸዋል! በሁሉም እረገድ ዓለምም ፈውስ ያስፈልጋታል! “በኋለኛው ዝናብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዝናቡን ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል፤ እርሱም የበልግ ዝናብን ለእያንዳንዱም በሜዳ ውስጥ ሣርን ይሰጣል።” — ዘካርያስ 10፥1 ፈዋሹን ኢየሱስ ክርስቶስን በእያንዳንዳችን ማክበር የሚችለው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ! ስለዚህ የእግዚአብሔር መንፈስ ይፍሰስብን! አሜን! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ክበርልኝ_ሜሮን_ተሰማ_Kiberlign_Meron_TessemaMP3_160K.mp37.80 MB

ዛሬ በአንድ ቦታ ተገኝቼ አገለገልኩ ይህንን ልነግራችሁ እፈልጋለሁ! ልክ ለማገልገል ወደፊት ስወጣ እዚህ ያለሀው ለሌሎች አይደለም ለራስህ ነዉ! የሚል መንፈስ ቅዱስ በልቤ የፈጠረው ጠንካራ እምነት ተመለከትኩ! እና እዚህ ያለሁት ለእናንተ አይደለም ለራሴ ነዉ አልኳቸው! የመልእክትን ቃል ከጨረስኩ በኃላ መንፈስ ቅዱስ እኔን እራሴን በተለየ ሁኔታ ነካኝ! አያችሁ ለማገልገል እንኳ መድረክ ላይ ስንቆም ስለሰዎች ሰይሆን ስለራሳችን ነው መሆን ያለበት!ዋናው ተናጋሪ መንፈስ ቅዱስ ነዉ። እኛ ራሳችን ተገልጋዮች ነን! በዚህ ልብ የምናገለግል ከሆነ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በእኛ ያከብረዋል። መልእክቱ "ሁላችንም የሚያስፈልገን መለኮታዊ ግኑኙነት" / The encounter that we all need/ የሚል ነበር። እያንዳንዱ ክርሲቲያን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ግላዊ የሆነ መለኮታዊ ግንኙነት ያስፈልገዋል! ይህ ከልሆነ ግን እውነተኛ የክርስቲያን ሕይወት መኖር ምኞት ብቻ ነዉ የሚሆነው። ከዚህ አስፈላጊነት ተነስቶ መንፈስ ቅዱስ መለኮታዊ ግንኙነት(encounter) ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስተምሮናል። በጣም የተወደደ ጊዜ ነበረን! ለእናንተም እጸልያለሁ! በመንፈስ ቅዱስ ሃይል እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን ይግለጥላችሁ! ከኢየሱስ ጋር ፊት ለፊት መገናኘት ይሁን! አሜን አሜን! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መስቀል ላይ የሞተልኝ፤ በደም ዋጋ የገዛኝ፤ ከሙታን የተነሳልኝና ሕይወቱን የሰጠኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነዉ: ከእርሱ ወድያ ላውቅ አልሻም! ከእርሱ ውጪ ማንም በእኔ መገለጫ ማግኘት አይችልም! የሞተልኝና የተሳልኝ እርሱ ብቻ በእኔ ይኖራል! ይታያል! ይከብራል! መንፈስ ቅዱስ ይህንን እያደረገ ነዉ ደግሞም በሃይል ማድረጉን ይቀጥላል። ክርስቶስን በእኔ አክብረው ብላችሁ መጸለይ እና ይህንን በሙሉ ልባችሁ መፈለግ ስትጀምሩ በዚያኑ ጊዜ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ተስማማችሁ ማለት ነዉ። መንፈስ ቅዱስ የመጣበት ትልቁና የመጀመሪያው አጀንዳ ኢየሱስ ክርስቶስን ማክብር ነዉ: ኢየሱስ በምድር በነበረበት ወቅት የአብን ፈቃድ በማድረግ ሙሉ ደስታ ያገኝ ነበር፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ምድር ላይ ደስታው የሚፈጸመው ኢየሱስን ስያከብር ነዉ! ታድያ ምን እንጠብቃለን!? የሚወደውን በመውደድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እንስማማ እንጂ! የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መስማማት ከፈለጋችሁ አንድ ነገር ብቻ አድርጉ! ክርስቶስን በእኔ አክብረው ብላችሁ ጸልዩ! ይህንንም አጥብቃችሁ ፈልጉ። “የእኔ ከሆነው ወስዶ እንድታውቁ በማድረግ ያከብረኛል።” — ዮሐንስ 16፥14 (አዲሱ መ.ት) 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

what's_going_to_happen_during_the_coming_revivalThe_most_honorable.aac4.39 KB

that time the lord hides himself is over😭.aac5.13 KB

A GLORIOUS WAVE OF THE SPIRIT

#ስሙ! We are that Generation! Prophet Emmanuel makandiwa! ተዘጋጁ ከባድ የመንፈስ ቅዱስ ሞገድ ይሆናል!😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

የልብ አይኖቻችሁ በሃይል ይከፈቱ! በኢየሱስ ስም: አይኖቻችሁን አዝዣለሁ አሁን ይከፈቱ!

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ያላየነውን ኢየሱስን ማሳየት አንችልም! ስለዚህ ኢየሱስን ደግማችሁ ደጋግማችሁ ማየት እንድትችሉ መንፈስ ቅዱስ የልብ አይኖቻችሁን በሃይል ይክፈት! ሰው ሁሉ እስክያየው ድረስ ክርስቶስ በእኔና በእናንተ ይታያል! ምኞት አይደለም! እምነት ነዉ!🔥 አሜን ይህ ብቻ በዘመናችን ይሆናል! ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ደምቆ፤ ልቆና ከፍ ብሎ ይታይብናል! መንፈስ ቅዱስ ይህንን እንደሚያደርግ ተናግሯል። አስባችሁታል በየትምህርት ቤቱ፤ በየመንገዱ፤ በየመስሪያ ቤቱ፤ በየቤቱ ፤ በየቤተክርስቲያኑ ሁሉ ክርስቶስ በእኛ ስገኝ!? ስናገር? ስሰራ? አስባችሁታል!???😭 አሮጌው ሰዋችን ፈጽሞ ተሰቅሎ ክርስቶስ በእኛ ስኖር፤ አስባችሁታል!? በእኛ ዘመን ያሚፈጸመው የእግዚአብሔር አጀንዳ ይህ ነዉ።በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።” — ኤፌሶን 1፥10 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Open the eyes of my heart, I want to see you! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የሚያስፈልገው አንድ ነገር ነዉ። One thing is need full.

ለእግዚአብሔር ከመስራት በእግዚአብሔር መሰራት ይቀድማል! ...በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህንን ስሙኝ! እግዚአብሔርን ለማሳወቅ ከመፈለግ በፊት እግዚአብሔርን ለማወቅ መፈለግ እና መትጋት ይቀድማል! አሁን አሁን ነቢይ/ሐዋሪያ የሚል መጠርያ ባለቤት መሆንና በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በፀጋ ስጦታዎች ማገልገል መቻል: የስኬት መንገድ ተደርጎ እየታሰበ: እንደምንም ጾሞና ጸልዮ የፀጋን ስጦታ በመቀበልና ፈጥኖ ወደ አደባባይ መውጣት የተለመደ ሆኗል። ነገር ግን የዚህ አይነት አገልግሎት ትክክለኝነትና ቀጣይነቱ ምንም ዋስትና የሌለው ነዉ! እግዚአብሔርን ከላወቃችሁት አገልግሎት ትጀምሩ ይሆናል እንጅ መቀጠል እና መፈጸም በጣም አሰልቺ ነገር ነዉ! መንገዱን የማናውቅ እና አደራረጉን ብቻ የምንሻ ከሆነ እመኑኝ በአገልግሎታችን ክርስቶስም አይከብርም፤ ቤተክርስቲያንም አትታነጽም፤ በውጭ ያሉም አይሳቡም! ለእግዚአብሔር ከመስራት በፊት በእግዚአብሔር መሰራት የሚቀድመው ለዚህ ነዉ። እግዚአብሔርን በልምምድ በግላችን ለማወቅ መናፈቅና መፈለግ ያለብን ለዚህ ነዉ። እግዚአብሔር ከአገልግሎታችን በላይ እኛን ይፈልገናል! ስለእርሱ ለመስበክ ከለን መሰጠት በላይ እርሱን ለመስማት ያለንን መሰጠት ይፈልገዋል። የማሪያምና የማርታ ልዩነት ይህ ነበር፤ ማሪያም ኢየሱስን ለማወቅ ሲናገራት ለመስማት፤ ከእርሱ ጋር ሕብረትን መረጠች: ማርታ ግን ያገለገለችው እየመሰላት በብዙ ነገር ባከነች! ኢየሱስ ግን ልታገለግለው ለተሯረጠችው ማሪታ ሰይሆን እርሱን ለመስማት ለመረጠችው ማሪያም እውቅና ሰጠ: መልካም እድል መርጣለችና ከእርሷ አይወሰድባትም አለ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Chose the best! Desire an encounter! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መዝሙር 51 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም። ¹⁷ የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። ¹⁸ አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት፤ የኢየሩሳሌምንም ቅጥሮች ሥራ።

ቤት ውስጥ ያለን ንቀንሃል ከእውነትና እምነት ተለያይተናል ማንነታችንን ጥለናል! ፍቅርንና አንድነትን ጠልተን፤ መለያየትን ወደናል ቅጥር እንደሌላት ከተማ ሆነናል፤ ሁሉም ያፌዝብናል: ደቂቁም ረቂቁም ተሰላቁበን! የአካልህ ራስ የሞትክላት ጌታ ምን ይሻለናል???? ጌታ መንፈስ ቅዱስ ፈውሰን፤ መልሰን፤ አድሰን፤ በሕይወትም አኑረን!....እንደ ቀደመው ዘመን መንነትህና ሃይልህ በእኛ ይታወቅ?😭😭😭 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የተወደደ መጋቢ ተስፋሁን ሙሉዓለም: ስለ ሪቫይቫል ከቤተክርስቲያን ጋር ያደረገው ጸሎት! #ኢትዮጵያዊያን_የናቅንህ_የእግዚአብሔር_ክብር_እባክህ_አትተወን!😭😭😭 #እየሰማችሁ_ፀጋ_ተካፈሉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Hear this in the name of Jesus Christ You shall reach and fulfill your prophetic destiny, by fire 🔥 by force💪!