uz
Feedback
ዕሴተ ✞ያሬድ Tube

ዕሴተ ✞ያሬድ Tube

Kanalga Telegram’da o‘tish

በዚህ ቻናል ውስጥ 👉መጻሕፈ ግጻዌ 👉የእለት ምስባካት 👉ውዳሴ ማርያም ዜማ 👉መስተጋብ ዜማ 👉ሥርአተ ማህሌት እና ዋዜማ 👉 ሃሳብ አስተያየት ጥቆማ👇 @St_gibereale ወይም @Menekrebot ☝☝☝☝☝☝ ይጦቅሙን እናመሰግናለን!!!

Ko'proq ko'rsatish
750
Obunachilar
+3224 soatlar
+1027 kun
+42130 kun
Postlar arxiv
Repost from N/a
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ስርአተ ዋዜማ ዘጥቅምት ገብረ መንፈስ ቅዱስ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 በ ፩ - ሃሌ ሉያ እንተ አጽናዕኮሙ ለአድባር በኃይልከ፤ወቅኦታን እሙንቱ በኃይል፤ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤አባ፤ጸሊ በእንቲአነ @menkir_tube ምልጣን፦ ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤አባ ጸሊ በእንቲአነ፤አባ ጸሊ በእንቲአነ አመላለስ፦ አባ ጸሊ በእንቲአነ/፪/ አባ ጸሊ ጸሊ በእንቲአነ/፬/ @menkir_tube ለእግዚአብሔር ምድር በምላህ፦ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ። @menkir_tube እግዚአብሔር ነግሠ፦ ጼና አልባሢሁ አባ መባእ ጽዮን ስሂን ገነት ከመ ይርአይ ዘሜላት ዘወረደ ውስተ ገነት ከመ ይርአይ ስነ ፅጌያት @menkir_tube ይትባረክ፦ ኪያከ መሠረት አንተ ብነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ እስመ ጸሎተ ጻድቅ ይሰምዕ እግዚአብሔር @menkir_tube ሰላም፦ ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም ዜና ምግባሩ ትሩፍ ለአረጋዊ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኮከብ ገዳም ፤ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም ፀጉያን እሙንቱ እምፅጌ ሮማን ወቀ ይሐን እምከላ ገዳም ፤ ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም ደቂቁ ሔራን ልኡላን ክቡር ወስያ፤ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም እንዘ የአርግ መስዋዕት ሰላም ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም፤ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም @menkir_tube አመላለስ፦ ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም/፪/ ድምፀ ወተሠብከ ውስተ አለም/፬/ 🇪🇹👇👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@menkir_tube👈                  👉@menkir_tube👈 👉@menkir_tube👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹       @menkir_tube     # Join & share

Repost from N/a
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ምስባክ ዘካልዓይ ጽጌ ☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️ ኤፌ ፮÷፩-፲ ራእ ዮሐ ፲፪÷፩-፲፫ ግብ ሐዋ ፮÷፳፫-፴ ወንጌል፦ሉቃ ፲፪÷፲፮-፴፪ ቅዳሴ፦ዘእግዝእትነ ምስባክ፦ ተዘከር እግዚኦ ከመ መሬት ንሕነ፤ ሰብእሰ ከመ ሣዕር መዋዕሊሁ፤ ወከመ ጽጌ ገዳም ከማሁ ይፈሪ። መዝ ፻፪÷፲፬ ትርጉም፦ አቤቱ እኛ አፈር እንደሆን አስብ፤ ሰውስ ዘመኑ እንደሣር ነው፤ እንደዱር አበባ እንዲሁ ያብባል። 🇪🇹👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@menkir_tube 👈 👉 @menkir_tube👈 👉 @menkir_tube👈 🇪🇹☝️☝️☝️☝️☝️🇪🇹    @menkir_tube #Join & share

አዲስ የቴሌግራም ቻናል ነው join አድርጉ

#የት_ነው_የምገባው የቀጠለ.. በመሆኑም እኛ ሰዎች እግዚአብሔርን ከማመን ወደኋላ ባለማለት ልባቸውን ከሁከት ነጻ ካደረግን ኢየሱስ ትልቅ ስፍራን አዘጋጅቶልናል። ዮሐንስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። ² በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤ ³ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። ⁴ ወደምሄድበትም ታውቃላችሁ፥ መንገዱንም ታውቃላችሁ። እስካሁን በተከታታይ በአራት ክፍሎች ባነሳነው መሠረት ገነት እገባለሁ ወይም አልገባም ከማለት ያለፈ ትርጉም አለው ይህም በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ፣ የክርስቶስን የማዳን (የለውጥነትን)ሥራ ከመቀበል አንጻር እና ሌሎችም ክርስቲያኖች ሌሎች ክርስቲያን ከሆኑቱ የምንለይበት ነገር ልዩ የሆነው ነገር ያዳነን እያዳነን ወደፊትም የሚያድነን ከነውርና ከነቀፋ ከኀጢአት ንጹህ የሆነ ቤዛነታችንን ያገኘንበት የተዋጀንበት ዛሬም የሚሰራ ትኩስ የሆነ ቅዱስ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ደም አለን። በምድር ባለን ህይወት እግዚአብሔርን ካመንን እርሱም በልጁ በኢየሱስ በኩል የገለጠውን ፍቅር ከተቀበልንና መንፈስቅዱስ ከማይከብርባቸው ነገሮች ከራቅን በማያሻማ መልኩ መግቢያችን ገነት መንግስተ ሰማያት ነው። ነገር ግን አንድ ማወቅ ያለብን ነገር ገነት እንዳንገባ ከሚያደርጉን ኀጢአቶች ካልራቅን በንስሐ በመቅረብ በቅዱስ ስጋውና በክቡር ደሙ በመክበር ወደ አባታችን ወደ ኢየሱስ ርስት መንግስት መድረስ እንችላለን። እርሱ እግዚአብሔር ግን ወደ ውድ ልጁ የፍቅር መንግስት አፍልሶናል። “እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን።” — ቆላስይስ 1፥13-14 መንግስቱን ወርሰን ከቅዱሳን ጋራ በክብርና በንጽህና ሆነን በጽዮን ተራራ ለበጉ እንድንዘምር የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሆንልን ዘንድ #ጌታ_ኢየሱስ_ይርዳን አሜን ተፈጸመ ዲያቆን የኋላሸት

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ምስባክ ዘቀዳማይ ጽጌ ሰንበተ ክርስቲያን 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 የዕለቱ ምንባባት፦ ሮሜ ፭÷፳፩-ፍ፡ም ራእ.ዮሐ ፩÷፩-፱ ግብ፡ሐዋ ፳፩÷፴፩-ፍ፡ም ወንጌል፦ዮሐ ፫÷፳፭-ፍ፡ም ቅዳሴ፦ዘእግዝእትነ ምስባክ፦ ፍሬ ፃማከ ተሴሰይ፤ ብፁዕ አንተ ወሠናይ ለከ፤ ብእሲትከ ከመ ወይን ሥሙር ውስተ ጽርሐ ቤትከ። ትርጉም፦ የድካምህን ፍሬ ትበላለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይሆንልሃል፤ ሚስትህ በቤትህ ዕልፍኝ ውስጥ እንደሚያፈራ ወይን ናት ። መዝ፡፻፳፮÷፪ 🇪🇹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🇪🇹

#የኢየሱስ_ማህተም ቅዱስ መስቀሉ ነው እንደክርስቲያን የግድ መሸከም ይኖርብናል ያለ ኢየሱስ መስቀል ባዶ ነንና የኢየሱስ መስቀል ከእንጨትነት ባሻገር የውለታን ጥግ የምናይበት ነው። ጌታ ኢየሱስ እኛን
#የኢየሱስ_ማህተም ቅዱስ መስቀሉ ነው እንደክርስቲያን የግድ መሸከም ይኖርብናል ያለ ኢየሱስ መስቀል ባዶ ነንና የኢየሱስ መስቀል ከእንጨትነት ባሻገር የውለታን ጥግ የምናይበት ነው። ጌታ ኢየሱስ እኛን ወደክብሩ ያቀረበበት ነው። መስቀል ቤዛችን ነው። ቤዛነቱ ደግሞበክርስቶስ የተደረገው ስራ ነው አንድም መስቀል ፍርድና የእግዚአብሔር ምህረት የተስማሙበት ነው። እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሰን። የክርስቶስ ሰላም ይብዛልን አሜን

"እርሱም የዚህን ዓይነት ትእዛዝ ተቀብሎ ወደ ውስጠኛው ወኅኒ ጣላቸው፥ እግራቸውንም በግንድ አጣብቆ ጠረቃቸው። በመንፈቀ ሌሊት ግን ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ እግዚአብሔርን በዜማ ያመሰግኑ ነበር፥ እስ
"እርሱም የዚህን ዓይነት ትእዛዝ ተቀብሎ ወደ ውስጠኛው ወኅኒ ጣላቸው፥ እግራቸውንም በግንድ አጣብቆ ጠረቃቸው። በመንፈቀ ሌሊት ግን ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ እግዚአብሔርን በዜማ ያመሰግኑ ነበር፥ እስረኞቹም ያደምጡአቸው ነበር" ሐዋ. 16:24 "የጠገበች ነፍስ የማር ወላላ ትረግጣለች፤ ለተራበች ነፍስ ግን የመረረ ነገር ሁሉ ይጣፍጣታል" ምሳ. 27:7 ለመመዝገብ ይህንን ይጫኑ https://forms.gle/XGBUJspsT9KydX2a8

#የት_ነው_የምገባው ክፍል 4 መልሱ ሊሆን የሚገባው ከዚህ በኋላ የሚመጣው ሀሳብ ሊሆን ይገባል። "እኔ ከዘመናት በፊት በሦስት አካል የተገለጸውን እግዚአብሔርን የማውቅ ኋላም ከሦስቱ አካላት መካከል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድ በስጋ በመገለጥ ከጽንሰት እስከ እርገት በሰራው የማዳን የቤዛነት(የለውጥነት)ሥራ የማምንና እግዚአብሔርም ያዘዘውን ለድህነት የሚያደርስ ከእምነት የሆነ መልካምን ስራ የምሰራ ስሆን ከምንም በላይ ግን የእግዚአብሔር ጸጋና የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ደም ጋሻና መከታዬ በመሆኑ ከሞት በኋላ የሚኖረኝ ህይወት እኖደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ገነት ነው" ይህ እርግጠኝነት ከትዕቢት ወይንም ከመታጀር የመነጨ አይደለም። እግዚአብሔርን ፈጽሞ ከማመንና ከመውደድ የመነጨ ነው እንጂ በነገራችን ላይ ሲኦል ነው የምገባው የሚለው አስተሳሰብ የግድ ትህትናን ይገልጻል ማለት አይደለም። አንድ ክርስቲያን ሲኦል ነው መዳረሻዬ ካለ ሌሎች ወደ ክርስትና ለመግባት የሚናፍቁ ሰዎችን የሚያርቅ እና መሰናከያ የሚሆን ነው። በእርግጥ የሰው ልጅ ምንም ያክል ኀጢአተኛ ቢሆን ወደገነት ይገባል የሚል መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ የለም። ነገር ግን ደግሞ ኀጢአት ከሰራ ደግሞ በንስሐ ከተመለሰ 1ኛ ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ¹⁰ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም። ስጋ ወደሙን ከተቀበለ... ዮሐንስ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁶ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ። ⁵⁷ ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል። ⁵⁸ ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል። በአጠቃላይ በእግዚአብሔር ላይ ፍጹም እምነትን ከጣለ ከዚህም እምነት የተነሳ የእግዚአብሔርን ህግጋት ከፈጸመ ይህ ሰው በእርግጠኝነት መዳረሻው ገነት ይሆናል። ይቀጥላል ..... ዲያቆን የኋላሸት

#የት_ነው_የምገባው ክፍል 3 እግዚአብሔር ሰዎች እርሱን እንዲዬመልኩት ግድ የማይል የነጻነት እና የፍቅር አምላክ ነው? እኛ ክርስቲያኖች የሚለየን ነገር በእግዚአብሔር ፊት ያለን ድርሻ ነው እኛ ማለት አባታችን እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ የገለጠውን ፍቅር ፣የክርስቶስን የቤዛነት ሥራ ያመንን በመሆኑ እግዚአብሔር ለእኛ ከአምላክነትም በላይ አባታችን ነው። ያላመኑቱ ግን አባታችን ሊሉ አይችሉም። ነገር ግን ወደዱም ጠሉም አምላካቸው ነው። ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማረን የሐዲስ ኪዳን ጸሎት እግዚአብሔርን አባታችን ብለን እንድንጠራ ነግሮናል። (ማቴ 6:9) እግዚአብሔር አባት ከሆንን እኛ ደግሞ ልጆች ነን ልጅ የሆነ ደግሞ አባቱን አብዝቶና አብልጦ ይወዳል።በተመሳሳይ አባትም እንደዚሁ ያደርጋል።ልጁ ያለውን የሚመኘውን ሁሉ ሊየደርግለት ይወዳል።በዚህም ምክንያት በአባትና ልጅ መካከል ጥልቅ ቁርኝት(ትስስር) ይፈጠራል።ልጅ ሁልጊዜም በአባቱ ይመካል።አባቱ እንደማሳፍረው ያምናል እምነቱም የሚገባ ነው። ጌታችንም በሉቃስ 11:11 ላይ እንደነገረን ኀጢአት ለባህርይው የሚስማማው የሰው ልጅ ክፉ ሲሆን ለልጁ እንጀራ ቢለምነው ድንጋይን፤ ዓሳ ስጠኝ ቢለው ስለ ዓሳው ምትክ እባብን ፤ብሎም እንቁላል ቢጠይቀው ጊንጥን አይሰጠውም። ታዲያ እንዲህ ከሆነ ንጹሐ ባህርይ የሆነው እግዚአብሔርማ ለእኛ ለልጆቹ ምን ያክል ይሰጠን ይሆን? ስለሆነም ከትንሣኤ ሙታን በኋላ ስለሚኖረን ህይወት ስንጠየቅ ገነት ነው ማለት ባንችልም ሲኦል ነው የሚለውን ትክክል ያልሆነ አስተሳሰብን ማስወገድ አለብን። ምክንያቱም የኛ ኢየሱስ በአባቱ ቤት ስለኛ ብዙ መኖሪያ አዘጋጅቶልናል። ዮሐንስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ² በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤ ³ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። እዚህ ላይ አንድ ነገርን መረዳት ይኖርብናል ክርስቲያኖች ወደፊት ስለሚኖራቸው ህይወት እርግጠኛ አለመሆናቸው ወይም ሲኦል እንደሆነ መናገራቸው የጌታችንን የማዳን ወይንም የቤዛነት ሥራ እና የእግዚአብሔርን ጸጋ ልዩ የማዳን ችሎታን ወደ ማክፋፋት(ማድፋፋት)ያደርሰናል። ስለዚህ ጥያቄው የት ነው የምትገባው/ቢው ከሆነ መልሱ ሊሆን የሚገባው.......... ይቀጥላል

#የት_ነው_የምገባው? ክፍል 2 በእውነቱ ቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ እኛን ለማጽደቅ የታመነ ነው። በአብዛኛው በሰዎች ዘንድ በተለይም በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ የሚታይ ነገር ቢኖር ከሞት በኋላ በሚኖረን ህይወት ወይንም በመግቢያችን ላይ እርግጠኛ ያለመሆን ሲሆን ምናልባትም እርግጠኛ ከተኮነ ደግሞ" የእኔ መግቢያ እኮ ሲኦል ነው" የሚል አስተሳሰብ ወይንም ንግግር አለ። አንዳንድ ክርስቲያኖች እኔማ የምገባው ሲኦል ነው የሚሉ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ አይ እኔ አላውቅም ብለው ይናገራሉ። በተወሰነ መልኩ ደግሞ ሌሎች አይ እርሱ የእግዚአብሔር ስራ ነው በማለት ይመልሳሉ። በጣም እጅግ በጣም ጥቂት የሆኑ በጣት የሚቆጠሩ ደግሞ አይ እኔ የምገባው ገነት ነው የሚል ምላሽን ይሰጣሉ። ገነት አገባለሁኝ የሚሉ ምናልባትም በእግዚአብሔር ላይ ጥልቅ የሆነ እምነት ያላቸው ሰዎች ሀሳብ ነው። ነገር ግን አንድ ጊዜ ጌታ ሞቶልኛል ምንም ባደርግ ብሰራ መግባያዬ ገነት ነው የሚሉ ሰዎችም አይጠፉም። በነገራችን ላይ ሲኦል እገባለሁኝ የሚሉ ሲኦልን ከመናፈቅ የመጣ አይደለም። ምናልባትም ትህትናን ለመግለጽ ራስን ዝቅ ለማድረግ የሚደረግ (የሚነገር) ይመስለኛል። ቢሆንም ግን የዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ፈጽም ሊቀየር እና ሊስተካከል የሚገባው ነው። በእርግጥ የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ማምለክ ያለበት ገነት ወይንም ሲኦል እገባለሁኝ በሚል መሆን የለበትም ኀያልና ብቸኛ እንዲሁም ሁሉን ቻይ አምላክ (Almighty God)በመሆኑ ብቻ እንጂ። እግዚአብሔር ለእኛ ላመነው ክርስቲያኖች ከአምላክነቱም በላይ አባታችን ሁኖናል። #በኢየሱስ ስናምንም ከምናገኛቸው ትልልቅ ጸጋዎች መካከል ዋነኛው የእግዚአብሔር ልጅ መሆን ነው። “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤” — ዮሐንስ 1፥12 በዚህም ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ልባችን ውስጥ እግዚአብሔርን አባታችን ብለን የምንጠራበትን የእውነትን እና የጽድቅን መንፈስ ያሳድርብናል። ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና። ¹⁵ አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና። ክርስቲያን በመሆናችን ካላመኑቱ የምንለየው እግዚአብሔር ለእኛ የሚሰጠን መግቦቱንና ጠብቆቱን ብቻ አለመሆኑ ነው። እነዚህንማ ላመኑትም ላላመኑትም መጋቢ በመሆኑ ይከውነዋል። ለሀጥም ለጻዲቅም እኩል ጸሀይን ያወጣል ይቀጥላል .......

🔴"ጥቂት ማቁሰል" 👉 በመምህር እዮብ ይመኑ 👈 | አስደናቂ ዐውደ ስብከት | ቅዱስ ዘተዋሕዶ

🔴"ጥቂት ማቁሰል" 👉 በመምህር እዮብ ይመኑ 👈 | አስደናቂ ዐውደ ስብከት | ቅዱስ ዘተዋሕዶ

#የት_ነው_የምገባው? በክርስቶስ ኢየሱስ  የተወደዳችሁ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ከሞት በኋላ ባለን ህይወት መግቢያችን የት እንደሚሆን እናያለን። በዚህ ጥያቄ ውስጥ ዋናው ቁምነገር መልሱ ገነት ወይንም ሲኦል ማለት አይደለም። ይህን ጥያቄ በምንመልስበት ልኬት ውስጥ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር  ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሥራ ለእግዚአብሔር  መንፈስቅዱስ ያለንን እምነትና ንጻሬ እናሳያለን። በመጀመሪያ  የሰው ልጅ የተፈጠረው የእግዚአብሔርን ስም እንዲቀድስ ብሎም የእግዚአብሔርን ክብር ይወርስ ዘንድ ነው።ይሆንንም በእምነት እና በቅድስና ውስጥ በመሆን ያገኘዋል። እምነቱ በእግዚአብሔር  ላይ ፍጹም የሆነ ትውክልት (እምነት)በመጣል ሲሆን በቅድስና ማለት ደግሞ በምድር በሚኖረን እድሜ  ቅዱስ አምላካችንን እግዚአብሔርን  እያከበርን እርሱን እየመሰልን ወደ የጸጋ ቅድስናን ማግኘት ነው። ማንም ቢሆን የባህርይ ቅድስና  የለውም። ቅድስናን በጸጋ(በስጦታ) ልንቀበለው ወይም ልናገኘው እንችላለን። አንድ ሰው ከእናቱ ማህጸን ከተወለደ በኋላ ዳግመኛ #ከማህጸነ_ዮርዳኖስ #ከአብራከ_መንፈስቅዱስ  ይወለዳል።  በኢየሱስ  በማመን ፍጹም ክርስቲያን ይሆናል።በክርስቶስ  ስም የሚያምን እርሱን አምላካችንን #ወልደ_እግዚአብሔርን የሚቀበል ደግሞ የእግዚአብሔር  ልጅ የመሆን ሙሉ ሥልጣን አለው። ትውልዱም ከሥጋና ከደም ያይደለ ከመንፈስ ነው። ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ¹³ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። ሰለሆነም አንድ ሰው ክርስቶስን ሲያምን ፣ሲቀበል የእግዚአብሔር የጸጋ ልጅ ይሆናል። ልጅ ከሆነ ደግሞ በቤት ውስጥ ወራሽ እንጂ ባሪያ የሚሆን የለም። ቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ እኛ እግዚአብሔርን አባት ብለን የምንጠራበትን መንፈሰ ልቦና አድሎናል። ከዚህም አልፎ በእውነተኛ ድምጽ ይመሰክርልናል። ከላይ እንዳነሳነው ልጆች ከሆንን #በእርግጠኝነት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን። የምንወርሰው እንደ ዓለም ሀሳብ ቁስ አይደለም ክቡር መንግስቱን እንጂ ስለዚህም በምድር ባለን ህይወታችን ከክርስቶስ ጋር ሁነን ተጣብቀን በስሙ የሚመጡትን መከራዎች ፈተናዎች ካለፍን እንወርሳለን። ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና። ¹⁶ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ¹⁷ ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን። በመላው ዘመናችን የክርስቶስ ከሆንን በመንፈስ የአብርሃም ልጅ በመሆን የተስፋውን ቃል ሰማያዊቷን ከንዓንን እንወርሳለን። “እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።” — ገላትያ 3፥29 እኛም ጸድቀን ወራሾች እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስም በክርስቶስ በኩል ወደ እኛ ሞልቶ ፈሷል። ይቀጥላል ..... ክፍል 1 ዲያቆን የኋላሸት 28/12/2015 ዓ.ም