Firibgarlarga uchmang! Telemetrio bunday kanallarni topadi va belgilaydi 👉 Belgini ko‘rmoqchi bo‘lsangiz, obuna bo‘ling 👈
3 584
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-87 kun
-4930 kun
Ma'lumot yo'q
Post ko'rishlar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q48 soatlar
Ma'lumot yo'q
Muloqot nisbati
Ma'lumot yo'q
Kuniga postlar
Postlar arxiv
3 584
ደስታ ላካፍላችሁማ! 😍
የዛሬ 6 ዓመት 98 ሺ ዶላር ለህክምና በእኔ አስተባባሪነት የሰበሰብንለት ዮናስ ጋሻቅ፣ ሁለቱንም ክራንቾቹን ትቶ ቆሞ መሄድ፣ ወጥቶ መግባት፣ ሰርቶ ቤተሰብ ማስተዳደር ጀምሮ እናንተን ለማመስገን ቆሟል። እግዚአብሔር የፈቀደው በለጠና፣ ልጅም ወልዷል። እግዚአብሔር ይመስገን።
እናመሰግናለን ብለው ከባለቤቱ ጋር የእምዬ ማርያምን ምስል ስጦታ ሰጥተውኛል። ❤️ ማመስገን። ወክዬ ተቀብያለሁ።
በወቅቱ ከአምስት ብር ጀምሮ ያዋጣችሁ፣ መልእክቱን በማጋራት ያገዛችሁ ሁሉ ምስጋናው ይድረሳችሁ። ደስታውም ለተጨነቁት፣ ከማዋጣት አንስቶ በሀሳብና በጸሎት ላሰቡት ሁሉ አድርሱት።
ሙሉውን ዝግጅት ከምንጊዜም ሚዲያ የዩቲዩብ ቻናል ላይ እዩትማ። link: https://youtu.be/ixnGiL2cox4?feature=shared
አስተዋጽኦ ላደረጉት ሁሉ ምስጋናው እንዲደርስ እባካችሁ ሼር በማድረግ አግዙ። እኔን እንኳን ደስ አለህ ማለት ከፈለጋችሁ ደግሞ ሜዳውም ይኸው ፈረሱም ይኸው፣
“አንድ ስኒ ቡና ለአመሌ በቂ ነው
ሱሰኛ ነህ ካልሽኝ መደጋገሜ ነው” እንዲል ዘፋኙ፣ የልደት ቀኔን ቡና ጋብዙኝ።
ለ"እማሆይ ፓኬጅ" 💛💛💛
ዓላማው በተለያዩ ገዳማት ውስጥ የሚኖሩ መነኮሳይያት (ሴቶች መናንያን) የንጽህና መጠበቂያ ፓድ ራሳቸው ማምረት እንዲችሉ የተጀመረውን እገዛ በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ጃን ሉቃስ በኩል ለመደገፍ ነው።
አገር ውስጥ ያላችሁ እነዚህን አካውንቶች ተጠቀሙ፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
አካውንት ቁጥር 1000524918629 ወይም 8261
አቢሲኒያ ባንክ
አካውንት ቁጥር 8261
የምታዋጡ screenshot ላኩልኝ።
የጎፈንድሚ ሊንክ https://gofund.me/bb7a4f51
SHARE! Spread the word!
❤️
3 584
It’s that time of year again—my birthday! 🎉😍 This year, I’m excited to support a meaningful cause: the “Emahoy Project,” which helps Christian mothers (nuns) produce sanitary pads. This initiative operates under the Ethiopian Jandereba Generation and aims to empower mothers in monasteries by providing them with the resources to produce menstrual pads for their own use and for other nuns.
The fund will be used to purchase raw materials, and potentially, establishing a supply chain from other monastery textile productions, and acquire production tools. The nuns will receive essential assistance and training, enabling them to produce sanitary pads and support their community.
As always, consider this like buying me a birthday coffee, or cake. Your contribution will go to the nuns through me, through the Ethiopian Jandereba Generation, Emahoy Project.
Let’s make this another successful year together!
To support the project through local banks:
Commercial Bank of Ethiopia 8261
Abissinia Bank 8261
Please send me a screenshot of your transfer if using local banks.
Thank you!
Spread the word and support if you can!
https://www.gofundme.com/f/wish-me-in-action-support-emahoy-project?utm_campaign=fp_ss_icons_ai&utm_content=amp1v4&utm_medium=customer&utm_source=copy_link
3 584
ቃና ዘገሊላ መጽሐፍን የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ከቁጥር 1 እስከ 11 ድረስ ያለውን የቃና ዘገሊላ ሰርግ ታሪክ በመረጃና ዋቢ መጽሐፍት አዳብሮ፣ በሰርጉ ቤት እያመላለሰ፣ አንዴ ከእናቱ ጋር አንዴ ከአሳላፊዎቹ ጋር እያጋጠመን፣ አግዳሚ ወንበሮቹ ላይ አስቀምጦን ከመልካሙ ወይን እያስጎነጨን ቆይቶ፤ ወደ ሰማያዊው ዕለተ አርብ ሰርግ ሸኝቶን....
“ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን።” ብሎ ሲያበቃ “አሜን” ብለው ተደንቀው፣ ከቃና ዘገሊላው ሰርግ ቤት እንደወጡ ሰማያዊውን ሰርግ እታደም ይኾንን በሚል ተስፋ እና ጉጉት መቆዘም ቢቀር እንኳን፣ በአጻጻፉ ለዛ እና በመረጃ አደረጃጀቱ ተደንቀው አመስግነው የሚጨርሱት መጽሐፍ ነው።
የብርሃን እናት
ስለ “የብርሃን እናት” ለማውራት ቃላት የሉኝም። እያንዳንዱ ገጾች ሲገለጹ ነፍስ እንዳላቸው ሁሉ የሚንቀሳቀሱ፣ አረፍተ ነገሮቹ ሁሉ ልብን አፍነው የሚይዙና በስሜት የሚወዘውዙ ናቸው። እንደው በአጭሩ ተናገር ብባል፥ ለእኔ የብርሃን እናት የብዙ ነገር መጽሐፍ ሆኖብኛል፤ የትምህርት መጽሐፍ ነው። የምርምር መጽሐፍ ነው። የጸሎት መጽሐፍ ነው። የውዳሴ እና የመዝሙር መጽሐፍ ነው። የሕይወት መጽሐፍ ነው። የትህትህና እና የጥበብ መጽሐፍ ነው። የታላቅ እውቀት መጽሐፍ ነው። የንጽጽር መጽሐፍ ነው። የእቅበተ እምነት መጽሐፍ ነው። የቋንቋ፣ የስነጽሁፍ መጽሐፍ ነው። የመነቃቃት መጽሐፍ ነው። የጥበብ መጽሐፍ ነው።
የማርያም ጸሎትን ተንትኖ ሲጽፍ ሳይ፣ ተደንቄ ተደንቄ ልሞት። ምን ትዝ አለኝ? አርጋኖን ሚዲያ ላይ በ10 ይኹን በ11 ክፍል የተላለፈው “የአባታችን ሆይ” ትምህርቱ። ይኽንን ከቃና ዘገሊላ አንድ ምዕራፍ፣ 11 ቁጥር ጉዳይ ወደ 178 ገጽ የመለወጥ አቅም ጋር ሳያይዘው፣ እንደ ሄኖክ ብቻ የሚባል አጻጻፍ እና አቅም አለ ለማለት ድፍረት ይሰጠኛል። ምን ሲሆን እንደዚያ ዓይነት የስሜት ባህር ውስጥ ገብቶ እንደጻፈው ለመመራመር እድሉን ሳናገኝ፣ እኛም እዚያው ባህሩ ውስጥ ሰጥመን አብረን ስንቃትት፣ ስንወጣ ስንወርድ እናገኘዋለን።
አቅም ባገኝ የብርሃን እናትንም ለሦስተኛ ጊዜ አንብቤ የተሻለ ዳሰሳ ለመጻፍ እሞክራለሁ። ይኽንንም ከቃል አትቁጠሩብኝ። እስከዚያው ግን መጽሐፉ ላይ የተጠቀሰ ቅዱስ ባስልዮስ፣ አምፊሎኪዮስ ለተባለ ተማሪው በጻፈው ደብዳቤ ቅርጽ እኔም ይኽንን ልጻፍ፥
ዲያቆን ሄኖክ ለማስተማር ያለው ፍላጎት የሚያውቁትን ለማካፈል ዳተኞች የሆኑ ሰዎችን ሳይቀር የሚያነቃቃ ነው። “እናውቃለን” ብለው የሚታበዩትን፣ “አይ ይኽን ማወቅ አንፈልግም” ብለው የሸሹትን፣ “ይኽን ሳናውቀው አንቀርም” ብለው የሚመጻደቁትን ሁሉ የሚጠራ ነው። ቆይ እንዴት እንደምናውቅ እናሳያቸው ብለው የሚታበዩትንም የሚያራራ ነው። ከሄኖክ አብልጬ የማደንቀው ግን፣ ትምህርቶቹ በዚህ ዘመን እንደምናያቸው ብዙ ሰዎች ሰውን ግራ ለማጋባት ወይ አውቃለሁ ለማለት (ማወቅን ለማሳወቅ) የተዘጋጁ ሳይሆኑ፣ በቅንነት እውነትን ለማሳወቅ ከመጓጓት ብቻ የመነጩ መሆናቸው ነው።
እግዚአብሔርን፥ Henok Haile እነዚህን ድንቅ መጽሐፍት እንዲጽፍ ስላበረታው፣ አነሳስቶ ስላስጀመረው፣ አስጀምሮም ስላስጨረሰው በታላቅ አንክሮ አመሰግነዋለሁ። "አቤቱ፥ ሥራህ እጅግ ብዙ ነው፤ ሁሉን በጥበብ አደረግህ፥ ምድርም ከፍጥረትህ ተሞላች።" ~ መዝሙር ፻፬: ፳፬
እውነት አቅም ቢኖረኝ ሦስቱንም ገዝቼ ለማውቃቸው ሁሉ በሰጠሁ የምላቸው ናቸው። እንዳልኩትም የሌላ እምነት ተከታዮች ወይም እምነት የለንም የምትሉ ሰዎችም ብታነቧቸው አንዳች ቁም ነገር አታጡም። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያን ከሆናችሁ ደግሞ፥ they are must-reads!
ለሁላችሁም ብሰጥ ብዬ ፎክሬማ አልቀርም! 😉
20 መፅሐፍት ለመስጠት ፈልጌያለሁ። 10 የብርሃን እናት ወይ ቃና ዘገሊላ (ቃና ዘገሊላ ገበያ ላይ ይኑር አይኑር ስላላወቅኹኝ ነው) እና 10 ሕማማት፥ በድምሩ 20 መጽሐፍት ለ20 ወዳጆች ለመስጠት ፈልጌያለሁ። መስፈርቱ ቀላል ነው፤ የልብን እውነት ማወቅና ሳይዋሹ ይገባኛል ማለት ነው። ከዚያ አንብባችሁ የተሰማችሁን ብትነግሩኝ ደግሞ ደስታዬ ልክ አይኖረውም።
▪︎ ሕማማትን “እግዚአብሔር አለ/የለም” በሚል ትኩስ ውዝግብ ውስጥ ላላችሁ 10 ወዳጆች።
▪︎ እንደዚሁ ደግሞ የብርሃን እናትን (ወይም ቃና ዘገሊላን ከሁለት አንዱን) ሀይማኖት ለመቀየር ውዝግብ ውስጥ ላላችሁ፣ ወይም በቅርቡ ቀይራችሁ ነፍሳችሁ ላላረፈች፣ ወይም ፕሮቴስታንት ውስጥ ሆናችሁ ውዝግብ ውስጥ ለሆናችሁ 10 ወዳጆች።
P.S.
አጠያየቃችሁን አሳምራችሁ ብትጽፉ ደግሞ ሰው ቢበዛ ለመለየት ያግዛል። 😉
አማኝ ሆነው ለስጦታ መዋሽት ተገቢ አለመሆኑ የእኔ ወዳጆች አይጠፋችሁም መቼ ም። እንደውም ብትችሉ አብራችሁ መስጠት ነው። 😉
3 584
የአንድ ጸሐፊ ሦስት መፃሕፍት፥ በወፍ በረር!
መቼም የመፃሕፍት ቀን ሲዘከር፥ ለመፃሕፍት ወዳጆች ቢሆን ስጦታ ይሰጥ ነበርና አቅም ቢኖረኝ ኖሮ ለሁላችሁም ገዝቼ ብሰጣችሁ የምወደውን፣ ለሁለተኛ ጊዜ አንብቤ የጨረስኩትን የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ሕማማት መጽሐፍ "ለመጽሐፍ ቀን" ስጦታ እንድታነቡት ልጋብዛችሁ። በድፍረት ብናገር፥ እስከዛሬ ድረስ እንዴት ሳላነበው ቆየሁ ብላችሁ ትጸጸቱ ካልሆነ፣ አትቆጩበትም።
(ትናንት በግርግር ሳይነበብ እንዳይቀርብኝ ያደረ ነው። 😉 )
በርግጥ ሳነበው ከነበረኝ ደስታ እና ከጨረስኩትም በኋላ እስካሁን ድረስ ከቆየሁበት ፈንጠዝያ አንጻር (ጭራሽ ለሦስተኛ ጊዜ ለማንበብ ያለኝን ውስዋስ 'ወዳጅህ ማር ቢሆን ልሰህ አትጨርሰው' ነውና፣ ለማብላላቱም “ዮሐንስ ቆይ ፋታ ውሰድ” በሚል ቁጣ፣ ራሴን አደብ ለማስያዝ እየታገልኩ እንደመሆኔ) "አንብቤ የጨረስኩት" ከማለት ይልቅ "ያለቀብኝ" የምለው ዓይነት ነው። መጽሐፉ ከስያሜውም አንጻር ከጾም ወቅት እና ከቀጣዩ ሳምንት ሕማማት ሳምንት ጋር ይግጠም እንጂ፣ በሕማማት ወቅት ብቻ የሚነበብ አይደለም።
ሌላ ሀይማኖት ውስጥ ያላችሁ፣ ወይም እምነት የለንም የምትሉ፣ ያላነበባችሁት ብታነቡት አንዳች ቁም ነገር ታገኛላችሁ። ቢያንስ አጻጻፉ ያማረ፣ በትህትና፣ በእውቀት፣ በእርጋታ፣ በመረጃ እና በንባብ የዳበረ ትልቅ መጽሐፍ ታነባላችሁ። ቅጣቴን በምን እንደምናወራርደው እንጃ እንጂ፣ ለወዳጆቼ፥ ወዳጅነታችንን ምስክር አድርጌ ሀላፊነት እወስዳለሁ! ;) ከፍ ሲል ደግሞ፣ ቆም ብላችሁ እንድታስቡና፣ 'ከየት ተነስተን እዚህ ደረስን' የሚለውን እንድትመረምሩ ዕድል ይከፍትላችኋል መሰለኝ። የእውነት “ቆይ እንከን ልፈልግ፣ አቃቂር ላውጣ” ብሎ ለሚያነብ ሰው እንኳን በማያመች መልኩ እጅግ በጣም አስደናቂ መጽሐፍ ነው።
ክርስቲያን ለሆናችሁ ደግሞ “እናውቀዋለን” ብላችሁ የምታስቡትን ጉዳይ፣ በተለየ መልኩ አቅርቦ፣ ወይ "አናውቀውም ነበር እንዴ?" እንድትሉ ያደርጋችኋል። የተከፈለላችሁን ዋጋ ያስቆጥራችኋል። ራስንን እና ቤተክርስቲያንን በቅርብ ለማየት ዕድል ይሰጣል። ወይም ቢያንስ የኢየሱስ ክርስቶስን የሕማማት ጉዞ ኦዲዮ ቪዧል በሚመስል ረቂቅ፣ ዝርዝር እየገለጸ ምስል እየከሰተ በጽሁፍ ይተርክላችኋል።
እያንዳንዱ ገጽ ሲገለጽ ዐይን ላይ አብሮ የሚገለጽ፣ ልብ ላይ ታትሞ የሚቀር ምስል አለ። እያንዳንዱ ገጽ ሲገለጽ የሚዳሰስ ሕመም፣ ወይም ራስን እያሳየ የሚያሸማቅቅ እና የሚቆረቁር መስታወት አለ። "እኔስ የት ነኝ? ግብሬስ ምንድን ነው?" እንድንል ያደርገናል። በዋጋ የተገዛን መሆናችንን ለምንቀበል ደግሞ፥ ስለትናንታችን እየተጸጸትን ደግሞ ስለ ነገ እንጨነቃለን።
ገና ለንባብ ሲያንደረድረን “ወዳጄ ሆይ እባክህን ጌታችን ከተያዘበት ሐሙስ ማታ እስከ ተቀበረበት ዓርብ ያለው ክስተት ውስጥ ራስህን ፈልገው። በዚያ ከነበሩት ሰዎች አንተ ማንን ትመስላለህ?...” ብሎ እየጠየቀ። ጉዞው ላይ የምናገኛቸው ጌታችን ላይ የጭካኔ ጠጠር ያዋጡትን ሁሉ ስናይ ገና ከመቅድሙ ማሳሰቢያ “እኔስ ብሆን” እያስባለን፣ ከዚያ በንጽጽር ከእኛ ምግባር የትኛው ስሞ መሸጥ፣ የትኛው ጥፊ፣ የትኛው ሀሞትና ከርቤ ቀላቅሎ መስጠት፣ የትኛው ጲላጦስነት፣ የትኛው ይሁዳነት፣ የትኛው ጴጥሮስነት የትኛው ጥጦስነት እንደሆነ እንድናስብና ስለራሳችን ተጨንቀን “አቤቱ በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስበን” እንድንል ያስታውሰናል።
በተለይ ጸሐፊው መቅድሙ መዝጊያ ላይ “…የምታውቃቸውን ሌሎች ሰዎችን ጠባይ ለማመሳሰልና 'ይኸማ እገሌን ለመንካት ነው!' እያልክ ከመንፈሳዊ መጽሐፍ ውስጥ ሥጋዊ ቅኔ ለማውጣት አትሞክር፣ እባክህ ራስህን ብቻ ፈልገው፣ የእግዚአብሔር ቃል መስታወት ነው። በመስታወት ደግሞ የራስን እንጂ የሌላ ሰው ፊት አይታይም” ያለውን ከግምት ከተን ራሳችንን ልናይበት ብቻ ካነበብነው።
መቼም መፃሕፍት በተለያዩ ምክንያቶች ተጽፈው የተለያዩ ውጤቶች ያመጣሉ።
ቆይ ማወቄን ላሳውቅ ብሎ የሚጽፍ አለ። ቆይ ለአንክሮ ለተዘክሮ ጽፌ ላስደንቃቸው ብሎ የሚጽፍ አለ። የሚያውቀውን ውበትም ሆን እውቀት ለማሳየት የሚጽፍ አለ። ቆይ የአቅሜን ጠጠር ልጣል፣ ላሳውቅ ከአንባቢ ጋር ስምረት (harmony) ፈጥሬ አብሬ ይዣቸው የሆነ ቦታ ደርሰን እንመለስ ተብሎ የሚጻፍ አለ። ሌላም ሌላም ብዙ ምክንያት ይኖራል። ሄኖክ ከአንባቢ ጋር ስምረት ፈጥሬ አብሬ ልቆይ ብሎ ይጽፋል።
ለመጻፍ ብዙ ሲነበብ፣ አንባቢን አግዞና የአንባቢን ትግል አቅልሎ፣ ጽሁፍን በሚገባ መልኩ ለማስረዳት ተጨንቆ ማቅረብም፣ በብዙ “አዋቂ ነን” ባዮች ችላ የሚባል፣ ታላቅ ስልጣኔ ነው። “Simplicity is the most difficult thing to secure in this world; it is the last limit of experience and the last effort of genius.” እንዲሉ። አንዳንዴ ግን ይኼ እየተዘነጋ፣ የመፃሕፍት ግብ፥ ማስደነቅና ረቂቅ መምሰል ብቻ እየመሰለ፤ ባልተረዳነው እና ለነፍስ ወይ ለስጋችን ምንም ረብ ባላገኘንበት ሁኔታም “ፓ” ብለን የጨረስናቸው መጽሐፍ አሉ።
የሕማማት አጻጻፍ እስካሁን ባየሁት እንደዚያ አይደለም። አብዛኛውን ሥራ ጸሐፊው ለፍቶ፣ በዝግጅት ደክሞ፣ በተቻለ መጠን ለሰዎች አእምሮ እንዲስማማ፣ ምሁራዊ እና ትውፊታዊ ለዛውን ሳይለቅ፣ “የእኔ አጻጻፍ” ብሎ ሳይታበይ፣ በትህትና የተነሳበትን ነገረ ጉዳይ ሳይለቅ ይዞ የሚሄድ ነው። ንባብ እንደ ተግባቦት (communication) ሁሉ የፀሐፊን ብቻ ሳይሆን የአንባቢንም ትብብር እና ቅንነት ይጠይቃልና፣ ጸሐፊው ያንን እገዛ በትህትና ጠይቆ ስለሚሄድ ነገሩንም ቀላል ያደርገዋል። ምን ንግግር ቢያምር ደም ግባት የሌለው ጆሮ ካልገጠመው እንደሚበላሽ፤ እንዲሁ ጽሁፍ ቢያምር ቀና አንባቢ ሲኖር ይበልጥ የልብ ይደርሳልና!
ይኽንን ሲይሳይም፥ ከሀምሳ በላይ ዋቢ መፃሕፍትን ከሶስት መቶ በላይ የእግርጌ ማስታወሻ ያጣቀሰበትን ሕማማት መጽሐፍ መግቢያ ላይ እንኳን፥ “...ስላላካተትኳቸው ጥቅሶች፣ ስላላነበብኳቸው መፃሕፍት፣ ምስጢር እንደ ጅረት በሚፈስባት ቤተ ክርስቲያን ስላልሰማዋቸሁ ቅኔዎችና ስላልጨረስኳቸው ብዙ አሳቦች እየቆጨኝ መጽሐፉን እንዳጠናቀቅሁ ይታወቅልኝ።” ሲል እናገኘዋለን።
በተለይ መንፈሳዊ መጽሐፍ ግቡን ሲመታ ደስ ይላል። ሕማማት በንባብ ወቅት ብቻ ሳይሆን ተነቦ ከተጨረሰ በኋላም ሰበርበር አድርጎ፣ ትሁት አድርጎ ይዞ የማቆየት አቅም አለው። ድጋሚ እስካነበው እናፍቃለሁና፣ ምናልባት ቃል ተደርጎ ካልተቆጠረብኝ ዘለግ ያለ ዳሰሳ ለመጻፍ እሞክራለሁ።
አጋጣሚ ሆኖ “አበረታች መድኃኒት እና ሌሎች ታሪኮች”፣ “ቃና ዘገሊላ” እና “የብርሃን እናት”ን አሁን ደግሞ ሕማማትን በተከታታይ አንብቤያቸው ነበርና (የብርሃን እናትን ድጋሚ)፣ ፀሐፊውን ለማድነቅና ለማመስገን ቃላት የሉኝም። የራስ ነው ተብሎ ሊቃለል (for granted ለመወሰድ) የማይቻል፤ በተለይ ከቤተክርስቲያን አገልጋይነቱ አንጻር ሲታይ ደግሞ 'ከዕድሜዬም ቆንጥሬ በሰጠሁትና ብዙ ባገለገለ፣ ምቹ ሁኔታዎች በተፈጠሩለትና ብዙ በጻፈ' የሚያስብል ነው።
ቃና ዘገሊላ
3 584
ሦስት መጽሐፍት ምረጡ ሲሉን፣ ሦስት መደርደሪያ መርጠን የነበረ ቢሆንም ቅሉ (ተሰበረ). ወደ አንድ መደርደሪያ ለማውረድ፣ የሦስት መጽሐፍ ይምረጡ እርስዎም ይሞክሩትን (challenge) እንደዚሁ በደፈናው ከሚሆን፣ በየዘርፉ ለማድረግ ሙከራ 😉
Kontent 18 yoshdan oshgan foydalanuvchilar uchun mavjud
Xizmatga kirish orqali siz 18 yoshdan oshganingizni tasdiqlaysiz.
