uz
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Kanalga Telegram’da o‘tish

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Ko'proq ko'rsatish
1 719
Obunachilar
-124 soatlar
-37 kunlar
-1130 kunlar
Postlar arxiv
Dear Feminist Fighters, Let us make something romantic this February 14th - the safety and protection of female bodies. Feminist Front is planning to publish a V-Day monologue based on your experiences with love, sexuality, and abuse. V-Day is an event aimed at ending violence against women and girls everywhere – and Feminist Front wants to co-create a monologue out of all the personal experiences you send to us. The stories you send can be anonymous – but will undoubtably show the beautiful, gruesome, scary, and sad experiences we have as Ethiopian women and help us love and heal collectively. There are three guiding questions under the shared link and you are only expected to answer one. Your stories will go through an editorial process that will not affect the content in any way. As our V-Day monologue will be published on February 14, make sure to submit your story before February 11. Be part of this highly confidential valentine’s day project. The Writer in you can save other women! V-Day Monologue

The absoluteness of one's state Expresses itself through contradiction.. የሚነካሽ አንድ ቃል አጣሁ ብዙ ሐረግ አወጣሁ.. ሁሉም ነጠፈ ሳይነካሽ አለፈ! ብዙ
The absoluteness of one's state Expresses itself through contradiction.. የሚነካሽ አንድ ቃል አጣሁ ብዙ ሐረግ አወጣሁ.. ሁሉም ነጠፈ ሳይነካሽ አለፈ! ብዙ የምልሽ ነበረኝ ዝም አልሁ! ተገለጠልሽ? ©ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል

❖ንጋት እና ንቃት ❖ አይነፃፀሩም ቅድም ከ አሁን ጋራ ቅፅበት ነበርና ምስሉ ያልረጋ -ገፅታው ያልጠራ:: የማይጨበጥ ነው በምኞት ተጠምዶ ከምናብ ተዋዶ ከህልም ተላምዶ በአጉል አምሮት መብረር በሃሳብ ግዞት ሰፎ ወድቆ ክንፍን መስበር :: ርግጥ ነው አልክድም! መልካም ህልም ነበር .. ጣፋጭ ዓለም ነበር .. ልዩ ነገር ነበር ... ሌሊቱ ባይነጋ ! አይኖቼን እያሸሁ ባልቀር ከራሴ ጋ :: በመስኮቴ በኩል የረፋዷ ፀሓይ ከአይኔ ቆብ ስር አርፋ ባትቀሰቅሰኝ ሕይወት በብርሃን ጨረሯ ባትጠቅሰኝ እውነት በሌለበት በሰመመን ነበር ስንት አዱኛ የሚያልፈኝ ! ©መቅደስ ሞገስ

የብርሃን ጥላ ነግቶ ፀሀይ ወጣች ሲመሽ ጨረቃይቱ አንድ ዕለት ተባለ የጊዜ ግምቱ ጨረቃና ፀሀይ እነዚ'ም ሁለቱ በብርሃን ስም ነው የሚጠሩበቱ ብ ር ሃ ን ጊዜ በብርሃን እኛም በጊዜ ፊት እንደ'ማለፋችን መተላለፍና መገናኘት አለ በእግረ - መንገዳችን አሁን መንገድ ላይ ነን ... እንዴት እንቃኘው ትናትን ከዛሬ ዛሬን ከነጋችን በነዚህ መካከል ዞሮ ይዘከራል መገናኘትና መተላለፋችን ጊዜ ግን አይገርምም ቀድሞ መፈጠሩ ከእኛነቻን እኛስ ግን አንገርምም ጊዜን ልናዝበት መንፈራገጣችን እላለሁ... በብርሀሃን ጀምሬ በጌዜ አልፌ ከኛ እደርሳለሁ ቃል እንደሁ ሎሌ ነው ይሄንን አውቃለሁ አዎ ቃል እናገራለሁ ቃል አበጃጃለሁ የቃል ፅኑነቱን በምድርና ሰማይ አረጋግጫለሁ ቃ ል ቃል ከእውነት እዲወለድ ከእመምነት ጋር እንዛመድ እንደ ጨረቃ እንደ ጣይቱ ምንም ቢጨልም ቢነጋ ሌቱ ልባችን ይብራ እንደ ሁለቱ በተስፋ ለተስፋ... እ ስ ከ መ ድ ረ ስ . . . © መንበረ ማርየያም ሀይሉ መንቢ የ ሎዛ

ክበባዊነት . . ያ'ለሚቷን ክበብ ያስገኘን ነጥቦች ተቋልፈን ተሳክረን የሰራናት 'ዶቶች' ፤ (ክምር የህዋሶች) .. በበቃን ተላ'ቀን አንዳችን የሸሸን ያፈነገጥን ለታ... ፤ ዓለም ትሞታለች ከዛጎሏ ወጥታ፡፡ .. በጦስ ጥንቡሳሷ እኛንም ቀላቅላ ፣ ክበብ በነጥቡ ነጥብም በክበቡ ይገለጣል ብላ፡፡ .... (ቀለም ሰው አምላክ) ©ዮሐንስ ኃብተማርያም

በዲበኩሉ ጌታ 'ራስ'ነት በምድር ዘላለም ቀዳሚነት ደምቆ እና ጥሞ ተጣጥሞ ያለፈው ግጥም ሲጥም 3 በጨረፍታ ይህን ይመስል ነበር። ከመደበኛ አጣሚዎቻችን በተጨማሪ በታዳሚነትም በአቅራቢነትም በድንገቴ
+8
በዲበኩሉ ጌታ 'ራስ'ነት በምድር ዘላለም ቀዳሚነት ደምቆ እና ጥሞ ተጣጥሞ ያለፈው ግጥም ሲጥም 3 በጨረፍታ ይህን ይመስል ነበር። ከመደበኛ አጣሚዎቻችን በተጨማሪ በታዳሚነትም በአቅራቢነትም በድንገቴ ተገኝተው መሰናዶውን ካጣሙሉን ውስጥ ዮሐንስ ሃብተማርያም (ጨበሬው)፣ Kal's T (The Wordsmith) እና ማሕሌት ማይረጉን እንዲሁም የተገኛችሁትን ሁሉ ምስጋና ልናቀብላችሁ እንወዳለን። ለተሻለ ከፍታ እየተጋን ነውና አሁንም ብርቱ እገዛችሁ አይለየን! እስቲ ደሞ ቀጣዩን 'ራስ' ገምቱ. . . ማን ሊሆን ወይም ልትሆን ትችላለች? #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers

በዲበኩሉ ጌታ 'ራስ'ነት በምድር ዘላለም ቀዳሚነት ደምቆ እና ጥሞ ተጣጥሞ ያለፈው ግጥም ሲጥም 3 በጨረፍታ ይህን ይመስል ነበር። ከመደበኛ አጣሚዎቻችን በተጨማሪ በታዳሚነትም በአቅራቢነትም በድንገቴ ተገኝተው መሰናዶውን ካጣሙሉን ውስጥ ዮሐንስ ሃብተማርያም ()፣ Kal'sT (The Wordsmith) እና ማሕሌት ማይረጉን እንዲሁም የተገኛችሁትን ሁሉ ምስጋና ልናቀብላችሁ እንወዳለን። ለተሻለ ከፍታ እየተጋን ነውና አሁንም ብርቱ እገዛችሁ አይለየን! እስቲ ደሞ ቀጣዩን 'ራስ' ገምቱ. . . ማን ሊሆን ወይም ልትሆን ትችላለች?

do you wanna know how it feels to let go Hold a rose smell the fragrance Embrace it Just cuddle the beauty dance with the scent laugh with life fell in love Hold it day and night and day and night till day passes And become amonth did you see her dying Okay I think Now you'e got it The pain of letting go! © Mekdes Moges

አምላክ ሰውን ሳያውቅ ሰው አምላክ ሳያመልክ የነበረው ዓለም ዳር ይዘት'ና መልክ፣ ጥበብ ጽንስ ነበር ይዞ አይደርሱት ተምኔት። ©ዲበኩሉ ጌታ