cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Gospel

ትክክለኛውንና እውነተኛውን ወንጌል የምስራች ለአለም ሁሉ የሚያበራውን #ኢየሱስ ብቻ ሚሰበክበት contact us @tsegamulat

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 224
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-17 kunlar
-330 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል የወጣቶች የድራማና የስነፅሁፍ ህብረት የተሰናዱ ሁለት ዝግጅቶች #ብኤርለሃይሮኢ ቀን: ነገ ማክሰኞ ሚያዚያ 29 ቦታ:በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል ሰዓት: 11:00 #ሎዶቅያዊት ቀን: ግንቦት 02 ቦታ:በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ሰዓት: 11:00
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
እዩ ተመልከቱት ፤ የክርስቶስን መስቀል ዛሬም ሲፈውስ ፤ የነፍስን ቁስል። © ቢቶ
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የዛሬ ሳምንት በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
እንደምን ጨካኝ ነው በልጁ ይሉኻል፣ ኃጢአትን ሰቅለው ወንበዴዎች መኻል! . ደካማ ነው አሉ ልጁን ካላዳነ፣ ሕዝብን ባንድ አድኖ ደም እየከደነ! . ይህ ተርታ ሕዝብ ኹሉ ተባብሮ ባንድ ቃል፣ "ራስህን አድን" ብሎ ይሣለቃል፣ ነገ በሱ ሊድን መኾኑን መች ያውቃል? #ሰሙነ_ሕማማት © Abere Ayalew
Hammasini ko'rsatish...
<<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?>> <<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።>> ዩሐ.13፥12-17 ~~~~ [ትህትና ሊያስተምረኝ ወዶ እግር አጠበ ባሪያውን ወርዶ እራሱን አዋርዶ] ~~~ በአቧራማዋ እስራኤል በነጠላ ጫማ (Sandals) መንቀሳቀስ የተለመደ ነበር። የጋራ ምግብ ከመቅረቡ በፊት ደግሞ ሰው እግሩን ታጥቦ ነው የሚቀመጠው፣ እጅ መታጠብ በኛ ዘንድ እንደተለመደው። ምክንያቱ ደግሞ ጠረጴዛው ዝቅ ያለ (low table) ስለሆነ ነው። ኢየሱስ ተነስቶ እግራቸውን ሲያጥብ የመጨረሻው ተራ ሎሌ ባሪያ የሚያደርገውን እየከወነ ነበር። ደቀመዛሙርቱም ራሱን 'በማዋረዱ' ሳይገረሙ አይቀሩም። የነፍሳችን ጌታና መሲህ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ፣ የአለምን ኅጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ... ሲሉት የከረሙት ሰዎች እግሩን ማጠብ ሲጠበቅባቸው እሱ ቀድሞ እግራቸውን ለማጠብ ማበሻ ማንሳቱ ባያስደንቃቸው ነው የሚገርመው። ምንም እንኳን እንደ ምድራዊ ንጉስና ነፃ አውጪ መጠበቃቸው የሚያደርጋቸውን እያንዳንዱን ድርጊቶቹን በአግባቡ ለመገንዘብ ቢከብዳቸውም፤ እንደ ስቅዩ-ሎሌ (suffering Servant) መምጣቱን አርፍደው ነው የተገነዘቡት (ኢሳ. 53)። ~~~~~~~ [ደቀመዛሙርቱ እግራቸው ቆሸሸ አደፈ ጎደፈ ፍጹም ተበላሸ ሁሉን የፈጠረ ሰውን የወደደ ጭቃውን ሊያስወግድ ወደ ታች ወረደ] ~~~~~~ ምጡቅ የሆነ፣ ሁሉን የሚገዛና ሁሉ በሁሉ የሆነ አምላክ እግር ሊያጥብ ዝቅ አለ፣ ከአቧራማ እግሮች ስር ተገኘ። "ፍጹም የቆሸሸን" ሰው ለማንፃት ፍጹም ንፁህ የሆነው ወልድ ራሱን ባዶ በማድረግ ወደ ታች ወረደ (ፊል. 2፥6-11)። ቃል መገለጡና በውርደት መንቀሳቀሱ አስደናቂ ነበር። የእግዚአብሔር ልጅ የህማም ሰው በመሆን፣ ቤት አልበኛ በመሆን፣ የድኻ ወዳጅ በመሆን፣ የኅጢአተኛ ወዳጅ በመሆን የተሰበረውን አለም ራሱን በመስቀል ለመስበር ተገኘለት። እንዴት ያለ የትህትናና የፍቅር ጥግ አሳየን! የእግራቸውን ቁሻሻቸውን ሲያፀዳ፣ አደፋቸውን ሲያጠራ ፈለጉን እንድንከተል ይመስላል "ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?" ብሎ የጠየቀን። አለሙ በኅጢአቱ ሲዳሽቅ ራሱን ለመላ አለሙ የቆረሰው ጌታ፣ ከአለሙ ድካምና ደዌ ራሱን ሳይሸሽግ የተገመሰለት አምላክ በድርጊቱ የምንቆርሰው እውነትን ችሮናል። ~~~ [እሱ ያላጠበው ከእርሱ ጋር አይኖርም አይቆርስም ከአምላክ ጋር አንድነት የለውም ጴጥሮስ ይህን አይቶ ሰውነቴን ደሞ እጠበኝ ጌታ ሆይ አለውም ተማጽኖ] ~~~~~ ኢየሱስ ስለራሱ ከነበረው ግንዛቤ አንዱ የሚያደርገውን የሚያደርግበት ምክንያትን ጠንቅቆ ማወቁ ነው።በኢየሱስ ያደረገው ስለራሱ በማቴ. 20፥28 እንዳለው "ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።" ራሱን ዝቅ አድርጎ ሌሎችን ሊያገለግል ነው የመጣው። ከግዞት በኋላ እስራኤል ያጣችውን ፖለቲካዊ ነፃነትን ለእስራኤል ለመቸር ሳይሆን በኅጢአት ግሳንግስ የታፈነውን አለም ከህማሙ ለመፈወስ ነው የመጣው። እግዚአብሔር ለእስራኤል ብሎም ለአሕዛብ የሰጠውን ተስፋ በእርሱ የሚፈጸምበት እግዚአብሔር "ምርጤ፣ ባሪያዬ" ያለው መሆኑ በአግልግሎቱ ቁልጭ ብሎ ይታይ ነበር። ለዚህ ነው የገዛ የራሱን ዐለም ከውልደቱ ጀምሮ በትህትና፣ በዝቅታ፣ በመዋረድ፣ በመከራና ፍዳን በመቀበል ያናገረው። ብቸኛው ቋንቋ መስቀል የሆነው። ከማገልገሉም ባሻገር ሕይወቱ እንደሚነግረን በትህትና መሞላቱን ነው። ከአመጣጡ እስከ አሟሟቱ ድረስ ድንቅ በሆነ ትህትና የተሞላ ነው። ~~~~ [በሚደነቅ ብርሃን የሚኖር ፈጣሪ አልፋና ኦሜጋ የፍጥታት ሰሪ ማበሻ ጨርቅ ወስዶ እግር ሊያጥብ ወረደ ዝቅ አ'ረገ ራሱን ለሰው ተዋረደ] ~~~~ የኢየሱስ ዝቅ ብሎ እግር ማጠቡ ዘማሪ ደረጄ ከበደ እንዳለው "ትህትናን ሊያስተምረኝ ወዶ" ነው። ያደረገልን ራሳችንን በትህትና ዝቅ አድርገን የባልንጀራችንን እግር እንድናጥብ ነው። ጉድፉን እንድናጠራ፣ ከክፉና እኩይ እንድንከላከለው እንዲሁም ራሳችን ለባልንጀራችን አሳልፈን እንድንሰጥ ነው። "በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረው ያ አስተሳሰብ" በእኛ እንዲኖር ነው። እግር ጉድፍ ሲያነሳ እንድንጠርገው በዚያም ትህትናችን እንዲታይ ተጠርተናል። ~~~~~~~ [የሁሉ ማሰሪያ አላማ ያለው ነው ጌታ ይህን አድርጎል እኔስ እንደምን ነው? የወንድሜን እግር እስካጥብ ዝቅ ካልኩ እውነትም 'የሱስን በእርግጥ ተከተልኩ] ~~~~~ ኢየሱስ የደቀመዛሙርቱን እግር አጥቦ ሲጨርስ "እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና" ብሏቸዋል። በሚደንቅ ብርሃን የሚኖር ምጡቅ አምላክ እግር ለማጠብ ማበሻ ጨርቅ ወስዶ የታናናሾችን ስራ ከሰራ እኛማ እንዴት ፈለጉን አንከተል?! እንደ ክርስቶስ ተከታይ እሱን በህይወቱ ልንመስል ይገባልና፣ ትሁት መሆን አለብን። የክርስቲያን መለኪያው ክርስቶስን መምሰል ነው። ዝቅ ማለት፣ ራሱን ማወረድ፣ ራሳችንን የሚጠቅመውን ብቻ ሳይሆን ሌሎች የሚጠቅመውንም ማድረግን ከጌታ ልንማር ይገባናል።የዝቅታን መንፈስ ይስጠን! ~~~~~~~ [ባሪያ ከሚያኖረው አይበልጥም አላቸው መልክተኛም አይበልጥ ይልቁን ከላከው እንግዲህ ጌታችሁ እኔ ይህን ስፈጽም አድርጉት ለሁሉም ዛሬ ሁኑ እናንተም] ~~~~~~ ባሪያ ከጌታው እንደማይበልጥና እኩልም እንዳይደለ ሁሉ ጌታ የፈፀመው ድርጊት እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች ልንከተለው የተገባ ነው። እግር ማጠብ ግዴታ እግር ማጠብ አይደለም። ክብርን መተው፣ ራስን ዝቅ ማድረግ፣ ራስን ማዋረድ፣ ራስን ለሌሎች መቁረስ፣ ትህትና ነው። ጌታ ያደረገውን እርስ በእርስ እያንዳንዳችን እናደርገው ዘንድ የተገባ ነው። የክርስቲያን መለያው፣ የአማኝ መታወቂያው የክርስቶስን ፈለግ መከተሉ እስከሆነ ድረስ አንዳችን ለሌሎቻችን ራሳችንን ዝቅ በማድረግ ማገልገል ይገባናል። Every good thing in the Christian life grows in the soil of humility. Without humility, every virtue and every grace withers. That's why Calvin said humility is first, second, and third in the Christian faith. John Piper እዚህ ጋር አንድ ዝማሬን እንዘምራለን፣ አብረን በፀሎት እንቃትታለን :- [ከከበረው እንቁ ሰው ከሚሻማበት እኔስ ትህትናን ባገኝ በዚ'ች ዕለት ጥማቴም ፀሎቴም ዝቅ ዝቅ ማለት] ~~~~~ <<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?>> ዩሐ. 13፥12 መልካም ፀሎተ ሐሙስ! መልካም ቀን! © አማኑኤል አሰግድ
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
Hammasini ko'rsatish...
"በተራራው ጫፍ ላይ" ድንቅ መንፈሳዊ ግጥም በዶ/ር ጌዴዎን ጡሚሶ/New Amazing Spiritual Poem by DR. Gedion Tumisso/2024_2016

Hammasini ko'rsatish...
ሰቆቃ ኑኃሚን አዲስ መንፈሳዊ ግጥም/በቢቶ/Seqoqa Nuhamin_New Protestant Poem/bito/Senpare Media_2024_2016

መንፈሳዊ ፊልሞች፣ ተከታታይ ድራማዎችን እና ሲትኮሞችን፤ የመድረክ ድራማዎች እና ተውኔቶች ፣ አስደናቂ ታሪኮችን እና ትረካዎች፤ ግጥሞች፣ የስነፅሁፍ ምሽቶችና ሌሎች አስደናቂ መንፈሳዊ የስነፅሁፍ ስራዎችን የሚቀርቡበት መንፈሳዊ የኪነጥበብ ቻናል ነው፡፡ "ትውልድ ሆይ ወደ እግዚአብሔር ቃልና ወደ ተሰቀለው ክርስቶስ ተመልከቱ!!!

https://www.facebook.com/profile.php?id=100069721774543

http://Instagram.com/sapphiremedia4god tiktok.com/@sapphiremedia1

"እኔ ላይ የተላከው ሰይጣን ረቂቁ ሳይሆን መሃይሙና ጨቋኙ ይመስለኛል"                            * * * ከጉራጌ ገጠር የተገኘ ነው።  ቤተሰቦቹ የተፈሩ ባለውቃቢ ነበሩ። ይህ ብቻ ሳይሆን ገና የሰባት አመት ልጅ ሳለ የወደፊቱ ታላቅ ባለውቃቢ እንደሚሆን ተነግሮለታል።  "የትልቁ ውቃቢ ተሸካሚ የሆኑት ባለውቃቢ  ሲሞቱ መንፈሱ እርሱ ላይ ያርፍና ታላቅ ባለውቃቢ ይሆናል" ተብሎለታል። በዚህም ሰበብ ገና ጨቅላ ሳለ ጀምሮ 'ወሰድ መለስ' የሚያደርገው 'ወፈፌ' ሊሆን ችሏል። ህፃን ሳለ በባዕድ አምልኮ የታሰሩ ወደ ባዕድ አምልኮ ስፍራ ሲመጡ እርሱ ብርቱ አገልጋይ ሆኖ ይሰለፋል። እንጨት ይፈልጣል፥ ወንዝ ወርዶ ውሃ ይቀዳል፥ በማምለኪያ ግቢው ከሚገገኘው የጫት ዛፍ ጫት ቀንጥሶ ያቀርባል፥ በርከክ ብሎ 'የአምላኪዎቹን' እግር ያጥባል፥ ቡና አፍልቶ ለተሳታፊው በማደል ስራ ይሰማራል። በብርቱ መታተር ውቃቢውን ቢያገልግም በውቃቢው የሚመሰገን አይደለም። ሲመሻሽ የጭንቅ ለሊት ይጀምራል። በብዙ  ይሰቃያል፥ ያውጓል፥ ደግሞም ይቃዣል። "ታዛዥ አገልጋይ ሆኖ ሳለ እንዲህ መሰቃየቱ ለምን ሆነ?" የሚል ጥያቄ በቤተሰቡ አእምሮ ቢፈጠርም ልጃቸውን ለማፅናናት የሚሆን ቃል አያጡም። "ትልቅ ሰው እየሆንክ ስለሆነ ውቃቢው ሊዋረስህ ነው፥ ስቃይህ በዚህ የተነሳ ነውና ታገስ" ይሉታል። ከቀናት በአንዱ ፥ እንደማንኛውም አዳጊ ልጅ አጎቶቹ ዘንድ ተልኮ  ሲሄድ ለየት ያለች ሴት ተመለከተ። ሴቲቱ ጭንቅላቷ አነስተኛ፥ አንገቷ አጭርና ወፍራም ፥ከትከሻ እስከዳሌዋ ወፍራምና ቅርፅ አልባ ነች። ከቀኝ ትኬሻዋ ወደ ግራ ዳሌዋ አሮጌ ጨርቅን አሸርጣለች። ማንኛውም ሰው ሲራመድ በእጆቹ አየር ይቀዝፋል። ይቺ ግን እጆቿ አይንቀሳቀሱም። መላ ነገሯ ያልተለመደ ነው። ታዳጊው ሴትየዋን በአስተውሎ ከተመከተ በኋላ ተሸበረ። በፍርሃት ወደመጣበት ሊመለስ እያሰበ ሳለ ሴቲቱ ድንገት ተሰወረች። ደግሞ ሌላ ቀን፥ ከእኩያ ጓደኞቹ ጋር ከብት ሊያግድ ተሰማራ። ይሄኔ ለሱ ብቻ አንድ ሰው ታየው። ሰውዬው ለመግለፅ በሚከብድ ልክ ቀጫጫ ሲሆን ወንዝ መሃል ሹል  ድንጋይ ላይ ተቀምጦ ሰውነቱን እያከከ ይታጠባል። በነገሩ ግራ የተጋባው ብላቴና የተመለከተውን ለጓደኞቹ ሊያሳይ ዘወር ከማለቱ  ሰውዬው ተሰወረ። በተደጋጋሚ የሚሆነው ክስተት ቤተሰቡን በማስጨነቁ መፍትሔ ተፈለገ። መላ ለማበጀትም በአባቱ መኖሪያ ካለ ወንዝ እንዲወሰድ ተወሰነ። ዘወትር ረቡዕ ከለሊቱ 11 ሰኣት ሲሆን ማንም ወንዙን ሳይሻገር ወደ ወንዙ ይደርሳሉ። ታዳጊው ልጅ አንዴ ወደ ወንዙ ከተነከረ በኋላ ወደ ዳር ይወጣና በአሻዋ ሰውነቱ ይታሻል። ከአሸዋ መታሸት ቀጥሎ ድጋሚ ይነከራል፥ መልሶም  በአሸዋ ይታሻል። ለሦስት ዙሮች በውሃው እየተነከረ በአሸዋ ከታሸ በኋላ በውሃ ይለቀለቃል። ይህ ሲሆን ከአሸዋው ጋር የሚቀላቀሉ ጥቃቅን ሹል ድንጋዮች የታዳጊውን ገላ እየሸነታተሩ ቁስል የሚፈጥሩ ሲሆን ወደ ውሃው በተነከረ ቁጥር ለከፍተኛ ስቃይ ይዳረጋል። ድርጊቱ የአንድ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ጊዜ የሚደረግ አይደለም!  ለ 49 ተካታታይ  ሳምንታት ሳይታጎል ይቀጥላል። 49 ሳምንታት በውሃ መነከርና በአሸዋ መታሸቱ ከተከወነ በኋላ በ50ኛው ሳምንት የመደምደሚያ ስርኣት ተከወነ። በ50ኛው ረቡዕ ዥንጉርጉር ነብር መሳይ ፍየል ተፈልጎ ከተገኘ በኋላ የ10 አመቱ ብላቴና ፍየሉን ተሸክሞ ወደ ወንዝ ወረደ። ቀጥሎ የፍየሉን ደም ስር በጥሶ እንዲያደማ ታዘዘ። የፍሉን ደም ስር ለመበጠስ ስለት መጠቀም አይፈቀድለትም፥  መበጠስ ያለበት ጥርሱ ነው። በበርቱ ትግል ፍየሉን ማድማት ተሳካለት። ፍየሉ እንዲታረድ ከተደረገ በኋላ በአሸዋ የመታጠብና በውሃ የመነከር  ትርዒቱ ቀጠለ። ከአሸዋና ውሃ መነከር ድርጊት ቀጥሎ በፍየሉ ደምና ፈርስ ታጠበ። ከጠቦቱ ስጋ አንዳች አልቀመስም። የዚህ ሰበቡ መናፍስታዊ እምነት ነበር። ፍየሉ የብላቴናውን ልክፍት ስለወሰደለት ስጋዋን ቢበላ ልክፍቱ ዳግመኛ ያገኘዋል በሚል እምነት ነበር ከመብል የተከለከለው። ታዳጊው ልጅ ከገደል ራሱን ወርውሮ ስለመግደል ያሰበበት ወቅት ነበር። ሆኖም ከገደሉ ከወደቀ በኋላ ሳይሞት ቢቀር ለዘመናት በአካል ጉዳተኝነት ሊሰቃይ እንደሚችል በማመን ሃሳቡን ሰርዞታል። ከሐገር ቤት ወደ አዲስ አበባ ካቀና በኋላ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፏል። በሰው ቤት በአሽከርነት በሚሰራበት ወቅት ተደብድቧል፥ ደግሞም የላቡን ውጤት ተከልክሎ ያውቃል። ይህ ብላቴና ከአመታት በኋላ ይህን ሁሉ  ውጣ ውረድ አልፎ ታላቅ የወንጌላውያን አገልጋይ ሆኗል። ያለፈ ስቃዩን ሲያስታውስ "ልጅ ሳለሁ ለኔ የተመደበው ሰይጣን ረቂቁ ሳይሆን ጨቋኙና አምባገነኑ ይመስለኛል" እያለ ይቀልዳል። ይህ ታሪክ የስመ ጥሩው አገልጋይ ፓስተር ታምራት ሃይሌ የልጅነት ህይወት ነው! ማጣቀሻ መፅሐፍ ፥ ፓስተር ታምራት ሃይሌ "የታምራት አምላክ ታምረኛ" © ተስፈኣብ ተሾመ
Hammasini ko'rsatish...