uz
Feedback
ግጥም ፍቅር ቅኔ

ግጥም ፍቅር ቅኔ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ለማንኛዉም አስተያየት👉 @hollynba ግጥም ቃላትን በንዝረት በምትሃት በዉበት እና በእዉነት አበጃጅቶ እፈጥርልናል ቁስልን ማከም ተስፋን ማለምለም አቅም አለዉ ፍቅር ዉበት እንደ ተመልካቹ እንደሆነዉ ሁሉ ፍቅርም በዚዉ ሊገለፅ የሚችል በተለያየ አንደበት በተለያየ ትሩጋሜ ሊገለፅ የሚችል ረቂቅ የፈጣሪ ልግስና ነዉ ቅኔ ሐበሻ ቅኔን ያለ ምክንያት አልፈጠረም በወኔ የማይነገሩ ሐሳቦቹን ሊገልጽበት እንጂ።

Ko'proq ko'rsatish
2 328
Obunachilar
-524 soatlar
-127 kunlar
-230 kunlar
Postlar arxiv
እንዴት ነሽ ስላት ሳቅ ታበዛለች ትጫወታለች ፤ < አለሁ ! > ትላለች - እንደሞላላት ቁስሏን የማላውቅ እዬመሰላት ፤ የዐይኗ መደፍረስ የገጿ ሽክረት የአንጀቷ ማረር የልቧ ቁስለት ጥልቅ ስቃይዋን እዬነገረኝ ፤ እርሷ ግን ሁሌም አንድ የምትለኝ ፤ - - - - - - - - - አለሁ ደህና ነኝ ! ልዩ ፍጥረት ናት አይደረሱባትም ፤ ስሟ ሕይወት ነው ካልተሸከሟት አይረዷትም ፤ በሕመሟ መሳቅ በቁስሏ ማጌጥ ታውቅበታለች ፤ ልክ እንደ መሬት ውኃ'ን ከእሳት ጋር ታቻችላለች ፤ ከራስ ቅራኔ ከራስ ጋር ሙግት ቢኖርባትም ፤ ከመሳቅ በቀር በሰው ፊት ማልቀስ አይኾንላትም ፤ ደህና ነኝ ከሚል ከአንድ ቃል በቀር —— ሌላ አይወጣትም ፤ እወድዳታለሁ ፤ ደህና ነኝ ስትል ደህና እንዳልሆነች አውቅባታለሁ።

#ፖለቲካዊ_ኮንትሮባንድ😂 የሩሲያ ዜጋ ነው። አንድ ልጁን ይዞ ወደ አሜሪካ ሊጓዝ፡ ሞስኮ በሚገኘው የሼሬሜቲቮ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የፍተሻ ክፍል ደረሰ። ሻንጣው ተፈተሸ ፡ በውስጡ የሌኒንን ምስል የያዘ ቅርጻ ቅርጽ ነበረው። የአየር መንገዱ የፍተሻ ሰራተኛ፡- "ምንድን ነው ይሄ ?" በማለት ጥያቄ አቀረበ። መንገደኛው ሩስኪ፥- "ጓድ ጥያቄህን ያቀረብክበት መንገድ ስህተት ነው። «ይህ ማነው?» ብለህ እንጂ «ምንድን ነው ይሄ ?» ብለህ መጠየቅ አልነበረብህም። ለማንኛውም ይህ ሰው ለዓለም ጭቁን ህዝቦች ሲል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የታገለ የኮሚዩኒስት ስርዓት አርበኛ ነው፡፡ ለአዲሲቷ ሩሲያ ምስረታ ደግሞ ቁልፍ ሚና የነበረው ታላቁ አብዮታዊ መሪያችን ኮምሬድ ቪላድሚር ሌኒን ነው። የእሱን ገድል ለመዘከርና በረከቱን ለመቋደስ ስል፡ በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ምስሉን በእቅፌ ይዤ እዞራለሁ !" በማለት ምላሽ ሰጠው። . ሩሲያዊው የኢሚግሬሽን ፍተሻና ቁጥጥር መኮንን፡ አጠገቡ ቆሞ በሚናገረው የሃገሩ ዜጋ አስተሳሰብ እጅግ ተደመመ። በግለሰቡ ጽኑ የሌኒን ፍቅርና እምነትም ክልቡ ተደሰተ። እናም፡- "መልካም ! ማለፍ ትችላለህ ጓድ !" ሲል በክብር ሸኘው። * ሩስኪው አሁን USA ደርሷል። የአሜሪካ አየር መንገድ ተርሚናል የፍትሻ ክፍል ውስጥ እየተፈተሸ ነው። የፍተሻ ኦፊሰሩ ሻንጣ ውስጥ ያለውን ቅርጻ ቅርጽ ተመለከተ። . "ምንድን ነው ይሄ ?" በማለት አሜሪካዊው የጉሙሩክ ኦፊሰር ከሩሲያዊው መኮንን ጋር ተመሳሳይ ጥያቄ አቀረበለት። ሩሲኪውም፡- "ይቅርታ ጌታየ ! ጥያቄህን ያቀረብክበት መንገድ ትክክል አይደለም። «ይህ ማነው?» ብለህ እንጂ «ምንድን ነው ይሄ ?» ብለህ መጠየቅ አልነበረብህም። . ለማንኛውም አገሬን ለቅቄ ወደዚች ሰላማዊ ምድር የመጣሁት፡ በዚህ ጠማማና እርኩስ ግለሰብ ምክንያት ነው። የዚህ ከይሲ ሰው ፍልስፍና ነው ዓለምን በሁለት ጎራ ክፍሎ ህዝቦችን ባላንጣ ያደረገው። በዚህም ምክንያት ለበርካታ ሃገራት የብጥብጥና የቀውስ ምንጭ ሆኗል። በዚህ ሰው ርዕዮት-ዓለም አያሌ ዜጎች አልቀዋል። ይህ ሰው የዲያቢሊስ ደቀ መዝሙር ነው። ሌኒን ይባላል ! ቅርጻ ቅርጹን በዞርኩበት ቦታ ሁሉ ከኔ አልነጥለው። ምክንያቱም ሁሌም ስመለከተው ለመርገም እንዲያመቸኝ ብዬ ነው ከጎኔ የማለየው !" ሲል ምላሽ ሰጠው። . አሜሪካዊው የፍተሻ ክፍል ኦፊሰር፡ በሩሲያዊው እንግዳ ቅን እና ስሜት የሚነካ ንግግር ተመሰጠ። እናም፡- . "ጌታየ ! እንኳን በሰላም የአሜሪካን ምድር ረገጡ። አሁን ማለፍ ይችላሉ !" አለው በክብር። . መንገደኛው ሩስኪ ወደ ማረፊያው አመራ። የአረፈበት ሆቴልም ቅርጻ ቅርጹን አውጥቶ አስቀመጠው። ልጁም ቅርጻቅርጹን ከተመለከተ ብኋላ፡- . " አባዬ ይህ ማነው ?" ሲል አባቱ በሚፈልገው መንገድ ጥያቄ አቀረበለት። ሩስኪውም፡- " የኔ ልጅ ! «ይህ ማነው?» ብለህ ጥያቄ ማቅረብህ ስህተት ነው። መጠየቅ የነበረብህ እንደ ሩሲያዊውና አሜሪካዊው የፍተሻ ሰራተኞች «ምንድን ነው ይሄ ?» ብለህ ነበር። ለማንኛውም ይህ የምትመለከተው ቅርጻቅርጽ፡ 10 ኪሎ ግራም ባለ 24 ካራት ወርቅ ሲሆን፡ እኔ አባትህ ያለ አንዳች ቀረጥ ነው ወደዚህ አገር በሰላም ያስገባሁት። ገባህ የኔ ልጅ !" ሲል ብልጠቱን ሳይሆን እውነቱን ለልጁ ነገረው። ፖለቲካዊ ኮንትሮባንድ ! . ብልጥ ሰው የሚሰራውን ሳይሆን መስማት የምትፈልገውን እየነገረህ ነው ፍላጎቱን የሚፈጽመው !! .😄😄😄😄😄

ጥሩ ሴት ሁኚ ​ታማኝ ሴት ሁኚ ​የራስሽ መርህና ክብር ይኑርሽ ​ክብርሽን ጠብቂ ​ሐያእ (ጨዋነት) ይኑርሽ ​ራስሽን በእውቀት አንጪ ​ለራስሽ እንክብካቤ አድርጊ ​በደንብና ጤናማ ተመገቢ ​የአእምሮ ሰላምሽን ጠብቂ ​ሰላትሽን በወቅቱ ስገጂ ​በአላህ ላይ ሙሉ በሙሉ ተመኪ​ንፁህ ልቦና (ኒያ) ይኑርሽ ​የቀረውን ነገር በሙሉ ለአላህ ተይው

ነፃነት ኦሾ ሙሉ በሙሉ ነፃ ለመሆን ሙሉ በሙሉ ግንዛቤ ማግኘት አለብን ምክንያቱም የባርነት ስር መሠረቱ ያለው ባለማወቃችን ውስጥ ነው። ጠልቀን ስንመረምረው ነፃነትህን የሚያሳጣህ ነፃነትን ለማግኘት ያለመፈለግህ ነው። ነፃነትህን የሚያሳጣህ ጥገኝ የመሆን ፍላጎት ነው። ራስህን የመሆን ኃላፊነት ላለመሸከም ያለህ ፍላጎት ነው። ሰው ለራሱ ኃላፊነት ለመውሰድ በፈቀደ ጊዜ በነገራችን ላይ ይህን ማድረግ ሙሉ በሙሉ አስደሳች ነገር አይደለም በውስጡ እሾህና መራር ነገሮች ይገኙበታል። ጣፋጫ ነገር ሁሉ ሚዛናዊ ነገር እኩል በእኩል ተከትለው ይመጣሉ። ጽጌሬዳዎች ያለ እሾህ አይበቅሉም ቀናትን ሌሊትን ተከትለው ክረምቱ አብቅቶም ፀሐይ ትወጣለች። ሕይወት የተቃራኒ ነገሮች  ሚዛን አጣጥማ ትኖራለች። ራስን የመሆን ኃላፊነትን ከውበቱና ከመራርነቱ ፣ከደስታውና ከስቃዩ ጋር ለመቀበል ፍቃደኛ የሆነ ሰው ነፃ መውጣት ይችላል። ነፃ ሊሆን የሚችለው ይህን መሠል ሰው ብቻ ነው።

ዳዊት ኤፍሬም ……ይለበድ ###### አዳምና ሄዋን አይናቸው ሲከፈት       ቀድሞ የተሰጣቸው         የቀለም ትምህርት ምራፍ አንድ ላይ     የራቁት ምንነት በገፅ ሁለት ላይ      በመራቆት ምክንያት የሚመጣ ሃፍረት           በስተመጨረሻ ማጠቃለያው ላይ እራቁትነትን ሸፍኖ ሚደብቅ አይነተኛ መንገድ የሚሉ ነበሩ    ገና ከጅምሩ ያኔም እሱን አውቀው ትምህቱ ገብቷቸው               ቅጠሉን ለበሱት               ላስከፊው በሽታ               እጅ ላለመስጠት ግና የቅጠል ልብስ ዋጋም እንደሌለው የገባው ፈጣሪ የሁላችን ሰሪ                       ወዶ አለበሳቸው                       ከፀሃይ ከውርጩ                          በሚጋርዳቸው ያኔም ተደሰቱ   ከጊዜ በኋላም   ቆዳው በመድረቁ   ስሱ ገላቸውን    እጅግ በመፋቁ ቁርበቱን አስቀምጠው በጨርቅ ደመቁ                     ታዲያ በኛ ዘመን                     ጅንስ በሞላበት ቀበቶ ምናምን    ወገብ ማሳመርያ      ጌጣጌጥ በሆነበት ሃፍረት ሚባል ነገር ጭራሹን ተረሳ ሆኖ ቀረ ዘበት                               እሱም ይባስ ብሎ                               ራቁትነት መጣ                               ፋሽን ተመስሎ የት ሄደን እንጩህ ለማን እንናገር በተንበረከኩ ዝቅ ባሉ ቁጥር                    የማንፈልገውን የምንጠላውን ቻነል እያሳዩን በጣም ተቸገርን                   ልንገርህ ወዳጄ              አድምጠኝ እውነቱን             ስርአቱን ጠልቶ ያፈተለከውን መሸፈን ሰልችቶት የሚያጮልቀውን እባክህ በማምላክ ፈስ-ቡኩን ዝጋልን

#ክባዳም_ትረካዎች . (#ፈይሠል_አሚን) . የአባቴ የጉንጭ ሥርጉድ ከየት የመጣ ነው? እናቱ ሲሥቁ ብዙ ጊዜ ዐይቻታለሁ።አያቴ ጉንጯ እንደ ገብስ ገንፎ የነጣና የሞላ ነው።አባቱም ቢሆኑ ጉንጫቸው የተለመደ አዘቦታዊ ጉንጭ ነው። አባቴ የጉንጭ ሥርጉዱን ከየት አገኘው? . በመሠረቱ የጉንጭ ሥርጉድ የሚገኝ ነገር አይደለም።ሳይንሱ "ጉንጭ ላይ ሥርጉድ የሚፈጠረው ጉንጭን ጉንጭ የሚያደርጉ ጥቃቅን ሴሎች በቁጥር ሲጎድሉ ነው!" ይላል። . አባቴ ጉንጩ የሠረጎደው ሴል አንሶት ነው።ከእናቱም ከአባቱም እንዲሁም ከኔ ውዱ ልጁም በሴል ቁጥር ያንሳል። ምስኪኑ አባቴ! . ግን አባቴ ከእናቱም ከአባቱም እና ከኔ ውዱ ልጁ የበለጠ የሚማርክ ፈገግታ አለው።ፈገግ ሲል ያየ ማንም ሰው ይደነግጣል፣ይደነቃል፣ ጉንጩንም ያደንቃል። በጉድለት ሰው እንደሚያሸበርቅ ያየሁት ከአባቴ ነው። ሰዎች  ያላቸው የሌለው ሰው ካላቸው የበለጠ ውብ እንደሆነ ያስተዋልኩት በወላጄ ነው። . እመኛለሁ። ጉንጬ ላይ ባይሆንም ሕይወቴ ላይ የጎደለ ነገር አለ።እንደ አባቴ ባሸበርቅበት ብዬ እመኛለሁ።ሰዎች ጉደለቴን ዐይተው በአድናቆት ቢመለከቱኝ፣በጎደለኝ ነገር ሰዎች ቢቀኑብኝ. . .እንደ አባቴ. . .እመኛለሁ! . 👇👇❤👇👇 @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM

የባሰ ቀን ሲመጣ . (#ፈይሠል_አሚን) . "ያልፋል!" ብዬ ቻልኩ፤ "ያልፋል!" ብዬ ተውኩ፤ "ባያልፍስ?!" በሚል ስጋት ራሴን ብዙ ቀጣሁ፣ ስብዕናዬን ጥዬ ከሰው ዓለም ወጣሁ! ዛሬ አለፈና. . . ነገ ደረሰና. . . "ይኼም ያልፋል!" ለማለት ብበቃም፤ ካሳደረኝ እንቅልፍ ደርሼ ብነቃም፣ ባላፈኝ ማግስቴ፣መንፈሴ አልረካም! . ያለፈው ምን አለው? መጪው ምን ጎደለው? የዛሬው እንባዬ አሁን እያሣቀኝ፣ ያለፈ ሥቃይ ነው፤ዛሬም 'ሚናፍቀኝ! . 👇👇👇👇 @siletibeb @siletibeb @siletibeb

የማይወዳደር እኩያ የሚያጣ ከልቤ ግርጌ ስር አንዳች ስሜት ወጣ ተሰማኝ ወደድኩህ ያንተን ጣዕም ለየሁኝ ቆዳዬ ቀመሰህ ምላሴን ከዳሁኝ       ከየትኛው አካሌ ፍቅርህ የወደቀው      የሚያርበተብተኝ ጥፍሬን የሚነዝረው      አካልስ አለ ወይ የሚታይ ሚቀመስ      ሴትነት ገላዬን ነክቶ ሚያጎለምስ ንገረኝ አንተዬ ከደጅ እንዳያድር ዳስም ልጣልለት እንዲህ ያለ ፍቅር አያድርም ከኔ ቤት በአዳፋዬ ባያድፍ ንፁህ ጥሩ ፍቅርህ ከቆሸሸ ገላ ከዚህ በድን ይሽሽ እንዲህ ያለ ልመና ሚዛን አያነሳም የፍቅር ባህሪ ዙፋንን አይሻም       የት ጋር ነው የሚሰማኝ ምኔን ነው የያዝከው      የት ጋር ነው ያገኘኸኝ ምኔን ነው ያጣኸው      ብቻ ከልቤ ስር ስሜቴ ይፈልቃል      የደረስክበትን ያልደረስክበትን      ረቂቁ ፍቅርህ እሱ ብቻ ያውቃል ✍ረድኤት ተረፈ

#በሃገሩ_ባዳ ! ዩኒቨርሲቲ የላኩት ልጄ... ሃገሩን አምኜ፥ ምንም አይቸገርም.. ወገኑ ነው ብዬ... "ተደበደበ!" አሉኝ እንዲያው እንደዋዛ! "ሊሞትብሽ ነው፡፡" የሚል - መርዶ አርጂ በዛ። ............................................... ምነው ሆዴም ባባ... አንጀቴ ሳሳብኝ ያጠባሁት ጡቴን ክፉ ጦር ወጋብኝ፥ የምሰማው ነገር ገዳይ መርዝ ሆነብኝ፤ ፍርሃት ... ፍርሃት አለኝ.. ሊማር እንደወጣ - ልጄ እንዳይቀርብኝ፤ ……………………………………………………………. በላቤ ነው ያደገው - በጭስ ውስጥ አልቅሼ - ባነባሁት እንባ እንጀራ ጋግሬ - ቆጮውን ጠፍጥፌ - ጡቶቼን ሳጠባ፥ ነበር መፅናኛዬ - የአይኔ ማረፊያ አይኑ እስኪቀላ - በኩራዝ አንብቦ - ግቢ እስኪገባ፤ ታዲያ ዛሬ... ያለኝን ቋጥሬ - ከሌለኝ ቆጥሬ፥ ስሜ የሸኘሁት ልጄ - ድግሪ ይጭናል ብዬ! ሃገሩን አምኜ! ወገኑ ነው ብዬ! "ተደበደበ!" አሉኝ እንዲያው እንደዋዛ፥ "ሊሞት ነው" የሚል ባለመርዶ በዛ! …እኔን ይደብድቡኝ - ይሁን ለናትህ! …እኔን ከርታታዬ... እኔ ልሙትልህ! ልጄ ላንተስ አይሁን! እኮ እንዴት ተደርጎ? ምንስ አጠፋና... ምስኪን ድሃው ልጄ - ወዶ ባልመረጠው - በብሔሩ ይቀጣ? ምን አይነት ጭካኔ - ጊዜ ያመጣው ጣጣ፤ ለትምህርት የሄደ - ህይወቱን የሚያጣ?! እኔስ አልችለውም - የሃዘኑን ነገር፥ ሌላ ባዕድ ሲሆን በወገኑ ሲገፋ - ሰው በራሱ ሐገር! __( አንድ ሃገር/ቢያ ቶኮ/ ገጽ 33-34 ... በዶ/ር ኤልያስ ገብሩ/ ህይወታቸውን ለመለወጥ ዩኒቨርሲቲ  ሄደው በጎሣቸው ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን በሙሉ መታሰቢያ የተፃፈ፤) @hollypoem

ተገላቢጦሾ       -------------- ሞኝ ነክ ካለህ ሞኝ ነኝ በለው ላንተ የከበደው እርሱ ከናቀው አንተ የጣልከውን እርሱ ካነሣው ላንተ የበራው ከጨለመበት እረፍት ከነሣው እውነት ሞኝነት ይሔ ከሆነ ሞኝ ነኝ በለው፡፡ እውነትን መያዝ ለውነት መታዘዝ ምክንያት ከሆነ ለስር ለመጋዝ ብልጥ ነኝ ያሉት ሞኝነት ካሉት በእውራን መሀል ማየት ባይደላም መዋሸት ከሆነ  ብልጥነት ሞኝነት አይከፋም፡፡ ንቃ ከተኙት መሀል ተለይ ሞኝ ነው ተባል ብልጥነት እንዳይገላቸው ሳትኮንናቸው ሳትፈርድባቸው ቀድመህ ንቃና ከሞት ከብልጥነት አንቃቸው፡፡       ............. ቢንያም ደሳለኝ 🙋‍♂

#ክረምቱ_በዚሁ_ከቀጠለ መስፍን በቀለ ነይ በነሀሴ እንዳደርግሽ የራሴ ያለው ወዶ አይደለም። አንዳች የሚያህል ጉቶ እያነደደም ብርዱን ስላልቻለው ሄዋኑን ተጣራ፣ ከ ይቅርታ ጋር ግን ያኔ መስፍን በቀለ ተ መቅጠኑ የተነሳ ሲያነድ ከነበረው ጭስ ውስጥ ሳየው አፍ ለይ የተሰካ ሲጋራ ነው የሚመስለው። የዘንድሮ ክረምት በግዜ መግባቱን ተከትሎ በግዜ ልጠቃለል በማሰብ እጄን ካፖርቴ ኪስ አድርጌ ከተማውን ቃኘውት፣ ሁሉም ሰው busy ነው። ክረምት መውጫማ ግድ ነው ብዬ እርምጃዬን ቀጠልኩ፣ የማታ እንጀራ ስጠኝ አለ የወለጋ ቅቤ ነጋዴ። በስተመጨረሻ አንዲት ልጅ አየው ሞባይል ቤት መሀል የቆመች ለሞባይሉ ማድመቂያ የበራውን አንፖል ይበልጥ ያበራች። እግሬ ይዞኝ ሄደ.... ሰላም ሞባይል ፈልጌ ነበር... ምረጥ እባክህ... ይይይይሄኛውን አልኳት... ፈገግ ብላ ይቅርታ ይሄ የኔ ነው አለችኝ... ሳጥኑን ጠቁማኝ ከዛ አንዱን መረጥኩ..... ስስስንት ነው??48,000 ትራንስፈር ላርግላችሁ... እሺ አለችኝ... ከፈልኩ ከፍዬ ልሄድ ስል እና ስልክሽን አትመርቂልኝም አልኳት። ያለ ምንም ክርክር በመግዛቴ ቁጥሯን እንደምትሰጠኝ ተማምኜ፤ በባንክ ቁጥሬ ደውልልኝ አለችኝ፣ ጦፍኩ... ለሷ ብዬ ያለ እቅዴ ኪሴን አራቁቼ ወይኔ የሰውየው ልጅ በ 48,000 ብር ስንት በቆሎ ገዝቼ ክረምቱን አይደለም ዘመኑን አላልፍም ነበር? እየተከዝሁ ወደ ቤቴ አቀናው። የበለጠ ቀዘቀዘኝ፣ በማግስቱ አይኗ ውስጥ ብገባ ብዬ በሱቋ ጋር ስመላለስ ዋልኩ በስተመጨረሻ አባት አባት የሚል ድምፅ ስሰማ እንባ ተናነቀኝ ባልሰማ ወዲያም ስንቀባረርባት ዝምብያት ሄድሁ። አንዴ ከ ጠራችኝ ግን ለመዞር ቃል ገባው የታባቷ ያለ ምንም ክርክር ረብጣ የምበጥስላት ሞጃ መሆኔን ባና መሆን አለበት፤ ኧረ አባት... ዞርኩ እና እየተጀነንኩ ወደ ሱቋ ሄድኩ፣ እንደደረስኩ ፍቅረኛ ግን አለችኝ አልኳት ፊቷ ለይ ግድንግድ ድንጋጤ እየጠበቅሁ፤ ይቅርታ ባለፈው ቻርጀሩን ረስተህ ሄደህ ነው።

#በኩር ፍቅሬ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✍sabir ያኔ ልቤን ሳስረክብ እንቺ ብዬ ላንቺ፣ ሳላውቀው ነው ማንነቱን የፍቅርን ፍቺ፤ የውስጤን ሳታየው በእውሩ ስትረከበኝ፣ ምን ተሰምቷት ይሆን ብዬ ጠየቅኩኝ፤ በኩር ፍቅሬ ራስሽ ለኔ ንገሪኝ፣ ከዘመን ባህር በትዝታ ታንኳ ወደ ኃላ መልሺኝ፤ ምንም እነኳ ያንቺን ባላውቀው፣ ልበልልሽ የኔን የውስጤን እወቂው፤ ፈቅጄም አልነበር ልቤን መስጠቴ በእጅሽ፣ ዐይኔ ላይ ቢያበራ እንጅ ጮራው የአይኖችሽ፤ ነብሴን ከነ አካሌ ወዳንቺ እየመራኝ፣ አስገደደው እኔን ማረፊያዬን አሳጣኝ፤ ላይነቀል በአይኔ ዙሪያ ተሰክቷል፣ ነብስ ዘራፊው የመልክሽ ፀዳል፤ የገፅታሽ ወዝ ያመጣብኝ ይህን መዘዝ፣ እንዳይለካ ሆኖ ያንቺ ፍቅር በኔ መመዘዝ፤ እሩቡ ጨረቃ ካፍሽ ላይ ወድቆ እንደቀረ፣ የከናፍርሽ ውበት እኔን እያመራመረ ኖረ፣ ከደቂቅ ሰውነት እኔን ወደ ሊቅ ቀየረ፤ እነሱ በገቡት እኔ አብሮ ዘላቂው፣ ውስጥሽን ከውስጥ ገብቼ ባየው፣ ራሱን ያጣው ከልብሽ ጓዳ ሆነ መገኛው፤ ደግሞ በአፍንጫዬ ሽው ይላል፣ ያ ጠረንሽ ከውሰጤ ላይወጣ ምሏል፤ ላንቺው የጥቅምሽ መምህሬ ነሽ፣ እምቢ እንዳላውቅ ሁሉን እንድልሽ እሽ፤ አይታወስሽምን ያንቺ ና የኔ ከመሬቱ በላይ፣ ያሰርነው ኪዳን አስከወዲያኛው ላንለያይ፣ ላልፈታ ታስሪያለው እኔ ከጣቷ ላይ፤ ቁርጥ ሳባን መሳይ ውቢት፣ ፍጥረት ቀርቶ ግዑዝ እጅ የሰጠላት፤ ስብዕናን ስብዕና ያላበሰች፣ የሴት ሀሁዬ መጀመሪያዬ ነች፤ በሳቋ ወደቀ ስነ ስርዓት አደብ ገዛ፣ አውርሷት ተሰዋና ለሷ ሆነ ቤዛ፤ 'ጃ' ሲያደለኝ ከዙፋኑ አንቺን፣ ለካ ዳግም ሊሰራኝ ነው ሊነቅል አበሳዬን፤ እንደ ጉድ ይዋልላል የሷና የኔ ጊዜ፣ በምናቤ ይመላለሳል የቤ-ጌ ግዕዜ፤ ግን ለምን መውደዷ በዚህ ደረጃ ጠናብኝ፣ የፍቅር አምላክ... አኔን ብቻ መርጦ ለምን ፍስሀ አጎናፀፈኝ፤ እንዲህ ለኔ መሳሳቱስ ምን ቢያይ ነው፣ ፍቅር በእኔ እንዲህ የጨከነው፤ ፈልቅቀሽ ከኔ አውጥተሻል ቀልቤን፣ ከአካሌ እንደሰለብሽው ልቤን፤ ሲዘረፍ ገባው የፍቅር ትርጉም፣ አይበርድ፣አይጠማው አያሻው ልጓም፤ ይቅር ብዬሻለው ላሁኑ ታልፈሻል፣ ግን አትመልሻት ተያት ታውቆኛል ደልቷታል...፤ አካሌ እንዳሻው ልብ አልባ ሆንኩ ቢል፣ ቅሪቴ ግን እስከወዲያኛው ያፈቅርሻል፤ አያታለው በድቅድቅ በጠሀዩ ጠራራ ባላያት፣ በህልሜ ዓለም ሌት ከአፍቃሪዋ ጋር ናት፤ በኩር ፍቅሬ ሆይ የልቤን ነገር አደራ፣ እንደወሰደኝ እስኪመልሰኝ አቆዪልኝ ካንቺ ጋራ፣ የልብሽ ዙፋኑ ላይ ሌላ እንዳይነግስበት አደራ፤ 👇👇❤👇👇 @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM @HOLLYPOEM

ግጥም ፍቅር ቅኔ - Telegram kanali @hollypoem statistikasi va tahlili