cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)

ሐበሻ ቅኔን ያለ ምክንያት አልፈጠረም፤ በወኔ የማይነገሩ ሐሳቦቹን ሊገልጽበት እንጂ! . ዳገት አቀበቱን በወኔው አለፈ፤ ወኔውን ሲነጥቁት ቅኔ ፈለሰፈ!😉

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
9 623
Obunachilar
-624 soatlar
-387 kunlar
-3730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

እስካሁን ግን ስንቶቻችሂ ናችሁ ቲኬት የገዛችሁት? ማበረታታት ላይ እንዴት ናችሁ?🙄
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የቲኬት ሽያጭ ተጀምሯል! 🎫 . በጉጉት የሚጠበቀው የሊቀ-ቀንበር የወግና የመዝናኛ ድግስ የመግቢያ ቲኬቶች ለገበያ ቀርበዋል። ቲኬቶቹ የት ይገኛሉ? 1. ቤተል ሚስተር ኮፊ፣ ፋሚሊ ታወር 4ኛ ፎቅ 2. ዋልያ ቡክስ (4 ኪሎ ኢክላስ ህንጻ) 3. the hungout cafe (አዶት ሲኒማ ህንጻ ground ላይ) . ባሉበት ኾነው ቲኬቱን በሞባይል ባንኪንግ ለመቁረጥ :- 1000413125654 Feysel በዚህ አካውንት በመቁረጥ ስክሪንሾቱን የዝግጅቱ ዕለት መግቢያ ላይ እያረጋገጡ መታደም ይችላሉ። . የቲኬቱ ዋጋ:- መደበኛ :- 200 ብር ቪ.አይ.ፒ:- 300 ብር . መሠናዶው የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 24 ብስራተ-ገብርኤል አካባቢ በሚገኘው አዶት ሲኒማ ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ይካሔዳል። . @huluezih @huluezih
Hammasini ko'rsatish...
ና! . (#ፈይሠል_አሚን) . ና ወደ አምላክህ! ተጠጋ ከደጁ! ምን አጥተህ ታውቃለህ፣ ከዚያ ለምለም እጁ?! ከአዱኛው ግርዶሽ፣ከማይከስመው ጣጣ፤ ከእልፍ ሕዝብ መሐል. . . አንድ "ሰው" ስታጣ፣ አምላክህ ብቻ ነው የመዳንህ ዕጣ፤ እንደ ሰው አይልህም. . . "ለጥቅሙ ሲል መጣ!" . @huluezih @huluezih
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ቀላል አይደለም፤ ነገር ግን ክብደቱ ጅማሬው ላይ ነው። ሲጀመር ከጥቂት ወዳጆችህና ቤተሰቦችህ ውጪ ከጎንህ ላይቆሙ ይችላሉ። ነገ የምትደርስበት ሥፍራ ዛሬ ላይ ለማንም አይታይ ይኾናል። ለዚያ ነው....በምትተማመነው ነገር ቁማር መጫወት ግድ የሚኾነው። እነሆ የመጀመሪያ ቁማሬ😁 . የአዳራሽ የቀን እና ሌሎችም ከባድ ውሳኔዎች መዘግየትን ፈጥሯል። እንደምታስተዋውቁልኝና እንደምትመጡ ተስፋ አደርጋለሁ። there is stg special.
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
በቅርብ ቀን በመድረክ ላይ እንገናኛለን! እስከዛ ድረስ ባላችሁ የሶሻል ሚድያ አካውንቶች በማስተዋወቅ እንድትቆዩኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ!🙏 . @huluezih @huluezih
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
. . . of the day!😎
Hammasini ko'rsatish...
የሙዓዚኑ ድምጽ! . (#ፈይሠል_አሚን) . ምቹ ፍራሼ ላይ. . . ስክነት አልሰፈረም፤ ከላባው ትራሴ፣ ከሐር መከዳዬ፣ሰላም አልነበረም! እጋላበጣለሁ! . ልብ ወደ አምላኩ አዘውትሮ ሲያምጽ፣ ከመስጊድ ተሰማኝ የሙዓዚኑ ድምጽ! "ጸሎት ከእንቅልፍ ይሻላል" እያለ ደጋግሞ ይጣራል! . ሳይጸልይ ያነጋው ልቤ አመጸኛው፣ ድርብርብ ኩኔነው ፊትስ መች አስተኛው? . ከሁለት አንድ አጥቶ፣ እንዲህ ከመቀጣት፤ መጸለይ ይሻላል እንቅልፍም ከማጣት! . መልካም ጁምዓ!❤ . @huluezih @huluezih
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
. . .of the day!😎
Hammasini ko'rsatish...
ስለ መጽሐፍት ቀን ሲነሣ. . . . አንዳንድ በተለያየ መልኩ የተበደሉ መጽሐፍት መደርደሪያችን ውስጥ አይጠፉም። ከየት እንዳመጣናቸው የማናውቃቸው፣ ሀፍረት ይዞን የገዛናቸው፣ መርጠን ገዝተናቸው የመነበብ ዕጣ ያልሠጠናቸው. . .በብዙ መንገድ የተበደሉ መጽሐፍት ይኖሩናል። . "ስለ ትናንሽ አለላዎች" መደረደሪያዬ ውስጥ ካሉ እጅግ ከሚያሳዝኑኝ መጽሐፍት በቁንጮነት ይቀመጣል። መጽሐፉን ከገዛሁት ከብዙ ጊዜያት በኋላ አማራጭ ሳጣ ነበር ያነበብኩት። አንብቤ ስጨርሰው በእጅጉ ተቆጨሁ..."እስከዛሬ ለምን አባቴ ነው ያላነበብኩት?" የሚል ፀፀት ወረረኝ። . ዮናስ አ.(አ ማንን እንደሚወክል አላወቅኩም) ይባላል ደራሲው። ሥሙንም ሠምቼው አላውቅም። ወጣትም ጎልማሳም ሊኾን ይችላል(አጻጻፉ ወጣትነትን ቢያስገምትም)፣ ማንም ሲያወራለት አልገጠመኝም። ግን በጣም የሚደነቅ የሥነ-ጽሑፍ ችሎታና ዕውቀት እንዳለው መጽሐፉን ያነበበ መረዳት ይችላል። ቋንቋው፣ ገለጻው፣ "በድንገተኛ መገለጥ (instant realization) በኩል የሚነግረን ንዑስ ታሪኮች...ለዛ አላቸው። በርግጥ አጻጻፈ-ዘይቤውን የዚህ ዘመን ደራሲዎችን የሚያጠቃው የአዳም ረታ ሕፅናዊነት ያጠቃዋል። መጽሐፉን ሳነብ በተደጋጋሚ "ግራጫ ቃጭሎችን" በትውስታ አነፈንፍ ነበር።ቢኾንም ንባብ ወዳጅን በሚመጥን ደረጃ የተጻፈው መጽሐፍ ነው "ስለ ትናንሽ አለለዎች" . @huluezih @huluezih . ያልተወራለት፣ብዙ ማሕበራዊ ገፆች ያላስተዋወቁትን መጽሐፍ የማመን ችግር ስላለብን ነው እንጂ አንገታቸውን ደፍተው ሲሠሩ ከርመው እንዲህ ድንገት ብቅ የሚሉ ገሞራ ጸሐፊዎች አሉ። ያላነበባችሁት ሰዎች ይኽን መጽሐፍ አንብቡት። ከታተመ 5 ዐመት ሊኾነው ነው...ጃዕፈር ጋር አይጠፋም። ደራሲውን የምታውቁ ካላችሁ አመሥግኑልኝ...ሥነ-ጽሑፍ ላይ ተስፋ እንዳንቆርጥ ስላደረግከኝ! እናንተስ underated ወይም ብዙ ያልተባለላቸውን ምርጥ መጽሐፍት ታውቃላችሁ? እስቲ ንገሩኝ!
Hammasini ko'rsatish...