uz
Feedback
Law studies ⚖️

Law studies ⚖️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
347
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
+330 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

O'xshash kanallar
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Iyul '26
Iyul '26
+348
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
08 Iyul0
07 Iyul+2
06 Iyul+1
05 Iyul0
04 Iyul0
Kanal postlari
ዕለታዊ🛎 ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች ⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖ ✍ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች የምንላቸው በወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 84 ስር የተዘረዘሩት ናቸው፡፡ ሀ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በከሀዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በወራዳነት ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኝነት፣ጥላቻ፣ ስግብግብነት፣ መጥፎ ነገርን ለመስራት ወይም ሰውን ለመጉዳት ፍጹም ፍቃደኛ በመሆን ወይም በተለየ ክፋት ወይም ጨካኝነት እንደሆነ ፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት ቅጣትን ለማክበድ ከመካከላቸው የአንዱ መሟላት በቂ ነው፡፡  ለ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ስልጣኑን፣ ተግባሩን  ወይም የተጣለበትን እምነት ወይም ሀላፊነት ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ የመንግስትን ስራ ለመስራት ወይም ለመምራት ስልጣን የተጣለበት ሰው ስራውን በታማኝነት እና በቅንነት መፈጸም አለበት፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ስልጣን ተገን በማድረግ ለራሱም ሆነ ለሌላው ጥቅም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ አንድን ወንጀል ከፈጸመ ቅጣት ሊከብድበት እንደሚገባ የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡ ሐ.ወንጀለኛው በቀድሞ ጥፋተኛነቱ ወይም ወንጀልን ማድረግ ሙያ ወይም ልማድ አድርጎ መያዙ፣ ወይም የወንጀሉ አፈጻጸም ዘዴ፣ ጊዜ፣ ቦታና የአፈጻጸም አኳሀን፣ በተለይም በሌሊት ወይም በሽብር ወይም በሁከት ለአደጋ ሽፋን ወይም በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ ወንጀሉን በማድረግ የተለየ አደገኝነቱን አሳይቶ እንደሆነ :: በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ እነኚህም፡- 1.ወንጀልን ማድረግ ሙያው ወይም ልማዱ አድርጎ መያዝ 2.የወ/ል አፈጻጸም ዘዴ፣ጊዜ፣ቦታ እና የአፈጻጸም አኳሀን 3.ወንጀልን በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ መፈጸም ናቸው፡፡ በተጨማሪም ሌሊት የሚለው ሀረግ ከስንት ሰዓት ጀምሮ እንደሆነ አሻሚ ቢሆንም በተለምዶ ፍርድ ቤቶች ከሌሊቱ 6፡00-12፡00 ድረስ ያለውን የጊዜ ገደብ በሌሊትነት ወስደው ቅጣት ያከብዱበታል፡፡ በእጅ ወይም በዱላ የውንብድና ወንጀልን የፈጸመ ሰው እና የስለት ወይም የጦር መሳርያዎችን ተጠቅሞ ይህንኑ ወንጀል የፈጸመ ሰው የወንጀል ማድረግ አደገኛነቱ እኩል ሊሆን አይችልም፡፡    መ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ወንጀል ለመፈጸም በተደረገ ስምምነት መሰረት ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ወይም ወንጀል ለመፈጸም ከተቋቋመ ቡድን ጋር በመስማማት ወይም አባል በመሆን ይልቁንም እንደ ወንጀል ቡድን ሹም ወይም አደራጅ ወይም መሪ በመሆን እንደሆነ :: ወንጀልን ለመፈጸም ከሌላው ጋር ወይም ለዚሁ አላማ ከተደራጀ ቡድን ጋር በአባልነት በመስማማት ወንጀልን ማድረግ ቅጣትን ሊያከብድ የሚችል በቂ ምክንያት ነው፡፡   ሠ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በዕድሜው፣ በጤንነቱ፣ በኑሮው ወይም በስራው ሁኔታ ልዩ ጥበቃ በሚያሻው ሰው ላይ በተለይም ለመከላከል አቅም በሌለው፣ መንፈሰ ደካማ፣ በሽተኛ ወይም አካል ጉዳተኛ ፣ እስረኛ ወይም በቅርብ ዘመዱ ላይ ወይም የበላዩ ወይም የበታቹ በሆነ ሰው ላይ፣ በህግ በተቋቋመ ባለስልጣን ወይም የስራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንድ የህዝብ አገልጋይ በሆነ ሰራተኛ ላይ እንደሆነ  ቅጣቱ  ሊከብድበት  ይችላል ::

2
ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ። ሚያዝያ 23
ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ። ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት በድሬዳዋ ከተማ ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን አሊዬ ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከግብረ አበሩ 2ተኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን የወላጅ አባቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋሉ። ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ዱካቸውን ለማጥፋትና በከተማዋ እንዳልነበሩ ለማስመሰል ወዲያውኑ ወደ አዲስ አበባ በያዙት የግል ተሽከርካሪ ይኮበልላሉ። ነገር ግን ወንጀለኞቹ ከህግ ማምለጥ አልቻሉም። የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወንጀለኞቹ ጥለውት የሄዱትን አነስተኛ ፍንጮች በመከተል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል። ፖሊስ ያደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተረከበው የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት (አቃቤ ህግ)፣ የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በመተንተን ክሱን በፍርድ ቤት ሲከታተል ቆይቷል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፦ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን የወላጅ አባቱን ህይወት በመቅጠፉ በሞት ቅጣት እንዲቀጣ 2ኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን በቅንጅት በመሳተፉ በ 20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖባቸዋል። ይህ የሞት ፍርድ ቅጣት የሚፈጸመው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ርዕሰ ብሔር ፍርዱን ሲያፀድቁ ብቻ ነው። የመዝግቡ ግልባጭም ለርዕሰ ብሔሩ ጽ/ቤት እንዲላክ ፍርድ ቤት አዟል። ቪድዮ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ
126
3
ስለ የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ አጭር ማብራሪያ *** 1.የቁጥጥር እና የአስተዳደር ማዕቀፍ ማሻሻያ የስልጣን ሽግግር፡ በነባሩ አዋጅ የነበሩ የ"ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ" ስልጣኖች በሙሉ ወደ "ፍትሕ ሚኒስቴር" ተላልፈዋል። ይህም የሕግ ባለሙያዎችን አስተዳደር ከፍትሕ አስተዳደር ጋር በማዋሃድ የአሠራር አንድነትን ለመፍጠር ያለመ ነው። የውጭ ሀገር ጠበቆች፡ በውጭ ሀገር ፍቃድ ያላቸው ጠበቆች ኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉት በፍትሕ ሚኒስቴር ተመዝግበው እና ከአገር ውስጥ ጠበቃ ወይም ድርጅት ጋር በመሆን ብቻ እንዲሆን ተወስኗል። 2. የብቃት መመዘኛዎች እና የሥራ ልምድ ማሻሻያው ለጠበቃነት ፍቃድ የሚጠየቀውን የትምህርት ዝግጅት እና የሥራ ልምድ በዲግሪ ደረጃዎች (ዲፕሎማ፣ የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ) ከፋፍሎ አስቀምጧል። የሙያ መግቢያ ፈተና እንዲኖር የተደነገገ ሲሆን፣ በዳኝነት ወይም በዐቃቤ ሕግነት ረጅም ዓመታት ላገለገሉ ባለሙያዎች ያለፈተና የጥብቅና ፍቃድ የሚሰጥበት ሁኔታ በሕግ መርህ መሰረት ተቀምጧል። 3. የጥብቅና ድርጅቶች አስተዳደር የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance): ጠበቆች ወይም የጥብቅና ድርጅቶች በሥራ ላይ ስህተት ቢፈጽሙ ለደንበኛ የሚከፈል ካሳን ለመሸፈን የግድ መድን ሊኖራቸው እንደሚገባ ተደንግጓል። ይህ የደንበኛ መብት ጥበቃን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሕግ መርህ ነው። የአደረጃጀት መፍረስ፡ የድርጅት መፍረስን የሚያስከትሉ ምክንያቶች በግልጽ የተቀመጡ ሲሆን፣ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ ይህን መረጃ ለሚኒስቴሩ የማሳወቅ ግዴታ ተጥሎበታል። 4. የዲስፕሊን ሥርዓት እና ቅጣት ሰነዱ የዲስፕሊን ጥፋቶችን ወደ "ቀላል" እና "ከባድ" በመክፈል ለቅጣቶች ግልጽነት ፈጥሯል፡ የቅጣት አወሳሰን፡ የገንዘብ መቀጮ፣ የፍቃድ ዕግድ እና የፍቃድ መሰረዝ እርምጃዎች እንደ ጥፋቱ ክብደት ይወሰናሉ። ለምሳሌ፣ የሀሰተኛ ማስረጃ ማቅረብ ወይም ሙስና እንደ ከባድ የዲስፕሊን ጥፋት ተቆጥሮ የፍቃድ መሰረዝ ቅጣትን ያስከትላል። የመሰየም አቤቱታ (Rehabilitation): በከባድ ጥፋት የተቀጣ ጠበቃ፣ ቅጣቱ ከተፈጸመ ከሁለት ዓመት በኋላ የዲስፕሊን ሪከርዱ እንዲሰረዝለት ለዲሲፕሊን ጉባኤ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው። 5. የአሠራር ግልጽነት የጠበቆች ማህበር አመራሮች ከአባላት መካከል በምርጫ እንዲሾሙ መደረጉ እና ተጠሪነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤ መሆኑ፣ የአመራር አባላትን ተጠያቂነት የሚያረጋግጥ የዴሞክራሲያዊ አሠራር መርህ ነው። ፍትሕ ሚኒስቴር ማህበሩን የመቆጣጠር፣ ሕገ-ወጥ መመሪያዎችን የማረም እና አስፈላጊ ድጋፍ የመስጠት ስልጣን ተሰጥቶታል። በአጠቃላይ፣ ይህ ረቂቅ አዋጅ የጥብቅና ሙያን በሙያዊ ብቃት፣ በኃላፊነት መድን እና በጠንካራ የዲስፕሊን ቁጥጥር ስርዓት ለማንቃት የተዘጋጀ ሰነድ ነው። የሸሪክ ለውጥ ማሳወቂያ ማሻሻያው የጥብቅና ድርጅቶችን አሠራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የሚከተለውን ግዴታ አስቀምጧል፡ ·      ማንኛውም የጥብቅና ድርጅት አዲስ ሸሪክ ሲያስገባ፣ የነበረ ሸሪክ ሲለቅ ወይም ሸሪክ ሲሞት ለውጡን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳወቅ አለበት። ·      በዚህ ድንጋጌ መሠረት የሸሪክ ለውጥን አለማሳወቅ እንደ ቀላል የዲስፕሊን ጥፋት ይቆጠራል። ·      ይህንን ጥፋት የፈጸመ የጥብቅና ድርጅት ከ15,000 እስከ 25,000 ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል። የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance) ደንበኞችን ከጠበቆች ወይም ከጥብቅና ድርጅቶች ሊደርስባቸው ከሚችል የሙያ ስህተት ለመከላከል የሚከተሉት ድንጋጌዎች ተጨምረዋል፡ ·      ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት፣ ሥራውን በአግባቡ ባለመወጣቱ ምክንያት በደንበኛው ላይ ለሚደርስ ጉዳት ካሳ የሚሆን የሙያ ኃላፊነት መድን መያዝ አለበት። ·      ጠበቆች የጥብቅና ፍቃድ ሲያወጡ ወይም ሲያሳድሱ ይህንን የሙያ ኃላፊነት መድን የያዙ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ·      የዚህ መድን ዋና ዓላማ የደንበኛን መብት በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ማስጠበቅ እና ለሚፈጠሩ የሙያ ስህተቶች የካሳ ክፍያ ዋስትና መፍጠር ነው። ጥያቄ- ይህ ማህበር ሲቋቋም እና አዋጁ ሲወጣ ጠበቃው ራሱን በራሱ ለማስተዳደር ሚስችል መሸጋገሪያ ነው ተብሎ ነበር ፣ ጠበቃው ከደካማ እና ተለጣፊ አስተዳደር ተላቆ ከመንገስት ሞግዚተነት ወጥቶ ራሱን በራሱ ማሰተዳደር መች ይሆን የሚጀምረው???????
122
4
#out_of_topic 'Trust' እና 'Google TV' የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የ
#out_of_topic 'Trust' እና 'Google TV' የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የባንክ ሂሳብን የሚያጠፉ "Trust"፣ "Google TV" እና "Known" የተባሉ አደገኛ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። እነዚህ መተግበሪያዎች በተለይ በGoogle Chrome፣ Telegram እና WhatsApp መድረኮች ላይ የሚጋሩ ሲሆን፥ ተጠቃሚዎች ሳያውቁ የገንዘብ ዝውውር በመፈጸም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ። ​ይህ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሳይበር ጥቃት በስፋት እየተስተዋለ የመጣው ተጠቃሚዎች ከተላኩላቸው አጠራጣሪ ሊንኮች ላይ መተግበሪያዎቹን ሲያወርዱ መሆኑ ታውቋል። መተግበሪያዎቹ አንዴ ስልክ ላይ ከተጫኑ በኋላ ከሞባይል ባንኪንግ ጋር የተያያዙ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመስረቅ ገንዘብ የመውሰድ አቅም እንዳላቸው ተገልጿል። ህብረተሰቡ ከዚህ መሰሉ የሳይበር ዘረፋ ራሱን ለመጠበቅ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Play Store ወይም App Store) ብቻ ማውረድ እንዳለበት ባንኩ አሳስቧል። ​ከተጠቀሱት የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የሚላኩ አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት እና በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎች ላይ የባዮሜትሪክ (የፊት ወይም የአሻራ) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምሮ መጠቀም ለአደጋው የመጋለጥ እድልን በእጅጉ እንደሚቀንስ ተነግሯል።
115
5
የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን በተመለከተ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች 1) በስጦታ፣ በሽያጭ ወይም በሌላ መንገድ ተገልጋዮች ንብረት ለማስተላለፍ ሲመጡ ካርታው ከጀርባው የተረጋገጠ መሆን አለበት፡፡ ካርታው ዲጂታል ከሆነ የጀርባ ማህተም አያስፈልገውም፡፡ 2)በካርታው ከጀርባ ላይ ንብረቱ በውርስ የተገኘና የወራሾች ዝርዝር የተፃፈበት ከሆነ ተጨማሪ ማስረጃ ማየት ሳያስፈልግ መስተናገድ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የንብረቱ መለያ ተጠቅሶ ወራሾች መሆናቸው በደብዳቤ ከተገለጸ አገልግሎቱን መስጠት ይቻላል፡፡ 3)በውርስ ወይም በስጦታ የተገኘ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት የጋብቻ ማስረጃ አይጠየቅም፡፡ 4)ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውጭ የተመዘገቡ የሚንቀሳቀሱም ሆነ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የማስተላለፍ ወይም የማከራየት አገልግሎት ማግኘት የሚቻለው ንብረቶቹ በሚገኙበት ክልል/ከተማ አስተዳደር ነው፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሊስተናገዱ አይችሉም፡፡ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም የሚያስተናግደው በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚመለከተው መ/ቤት የተመዘገቡ ንብረቶችን ብቻ ይሆናል፡፡ 5)ከጋብቻ በፊት በተቋሙ ቀርበው የንብረት ማግለል ውል ያደረጉ ወይም በፍ/ቤት ያጸደቁ ተጋቢዎች ንብረታቸውን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት ሲመጡ የትዳር አጋራቸው ስምምነት አያስፈልግም፡፡ ሆኖም የንብረት ማግለሉ ስምምነት አሁን ጸንቶ ካለው ጋብቻ የትዳር አጋር ጋር የተደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ 6)አካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች ንብረት ለመግዛት የሚቻል ሲሆን ሁለቱም ወላጆች ሊገኙ ይገባል ፡፡ ካልሆነ አባት ወይም እናት ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡ ሆኖም ከእናትና አባት ውጪ የሆነ ሞግዚት አካላመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ንብረት ለመግዛት በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡ 7.)ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ ሞግዚቱ እናትና አባትም ቢሆኑም በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡ 8.)ያላገባ ማስረጃ ላይ ቀደም ሲል ጋብቻ ስለመኖሩ የሚጠቁም የጊዜ መረጃ ሲኖር ንብረቱ በጋብቻ ወቅት የተፈራ ሊሆን ስለሚችል ንብረቱ የተፈራበትን ጊዜ የሚያመለክት ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ተጨማሪ ማስረጃ ሊቀርብ ይገባል፡፡ 9.)ተነጻጻሪ ካርታ ማለት በአንድ የቦታ ስፋት ውስጥ የተለያዩ ቤቶችና ባለመብቶች ያሉበትና በተለያዩ ሰዎች ሊያዝ የሚችል ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ ይዞታ ላይ የባለቤትነት መብት ያለው ሰው የራሱን ካርታ በመያዝ ድርሻውን ጠቅሶ መሸጥ ይችላል፡፡ 10)ካርታ ላይ የሚጠቀሰው ቀን ካርታው የተሰጠበትን ቀን እንጂ ንብረቱ የተፈራበትን ቀን በቀጥታ ላያመለክት ይችላል፡፡ ስለሆነም ንብረቱ የተፈራበትን ቀን ለማወቅ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የንብረቱ ባለቤት ተጨማሪ ማስረጃ እንዲያቀርብ መደረግ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከመሬት አስተዳደር ለገቢዎች እና ለካርታው ባለቤት የሚሰጡ ደብዳቤዎችን አያይዞ መስራት ይቻላል፡፡ 11) የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለማስተላለፍ የፍቺ ውሳኔ ይዘው የሚቀርቡ ባለጉዳዮች ንብረቱ የጋራ ወይም የግል ስለመሆኑ በፍርድ ቤት የጸደቀ የንብረት ክፍፍል ስምምነት ወይም ውሳኔ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 12)ንብረት በስጦታ ለማስተላለፍ የተሠጠ የውክልና ሥልጣን ስጦታው ለማን እንደሚሰጥ እና ንብረቱ ምን አይነት እንደሆነ በውክልናው ላይ በግልፅ መቀመጥ አለበት፡፡ ነገር ግን በውክልና ስጦታ ለመቀበል ሲሆን ስጦታ ይቀበልልኝ የሚለው አገላለጽ በቂ ነው፡፡ 13) የጋራ ንብረት በሽያጭ በሚተላለፍበት ጊዜ ገዢው ከንብረት ተጋሪው ውጪ የሆነ እንደሆነ የተጋሪው የቅድሚያ መግዛት መብት መጠበቁን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪውን ምስክር በማድረግ፣ የሚንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪው ማረጋገጫ እንዲሰጥ ማድረግ ይቻላል፡፡ 14) የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ከሆነ የታደሰ በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ወይም በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት ቢያንስ አሥር ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በሥራ ላይ ማዋሉን የሚገልጽ ማስረጃ እና የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሊቀርብ ይገባል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ሌላ የመኖሪያ ቤት በስሙ የሌለ ስለመሆኑ የሚገልጽ ከሚመለከተው የንብረት መዝጋቢ አካል ማስረጃ ማቅረቡን እንዲሁም ከተቋሙ የመረጃ ቋት ማጣራት ያስፈልጋል፡፡
119
6
ፀደቀ‼️ የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️ *ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው። በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦ ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል። ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል። የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል። ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
109
7
ታክስ ከፋይ ተቋማት የተወሰነባቸው የታክስ ክፍያ ላይ ቅሬታ ማሰማት ከፈለጉ ቅሬታቸውን በጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት ለሚቋቋመው ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን አቅርበው መፍትሄ ያገኛሉ ተባለ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባከናወነው መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ እና ማሻሻያ በማድመጥ በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል። ቋሚ ኮሚቴው በረቂቅ አዋጁ ላይ ካደረጋቸው ወሳኝ ማሻሻያዎች መካከል የታክስ አለመግባባቶችን የሚያስማማው "አስማሚ" (Mediator) አሰያየምን የተመለከተው ይገኝበታል፡፡ በመጀመሪያው ረቂቅ ላይ አስማሚው በታክስ ባለሥልጣኑ እንዲሰየም ተደንግጎ የነበረ ቢሆንም፣ ቋሚ ኮሚቴው "ገለልተኝነትን ለማረጋገጥ" ሲባል አስማሚው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እንዲሰየም በሚል ማሻሻያ አድርጎበታል፡፡ በማሻሻያው መሰረት ታክስ ከፋይ ተቋማት የተወሰነባቸው የታክስ ክፍያ ላይ ቅሬታ ማሰማት ከፈለጉ ቅሬታቸውን በጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት ለሚቋቋመው ገለልተኛ የባለሙያዎች(አስማሚ) ቡድን አቅርበው መፍትሄ የሚያገኙ ይሆናል። ሌላኛው ማሻሻያ የቀረበው አዲስ ማስረጃን ከማቅረብ ጋር ተያይዞ የሚጣልን ቅጣት የሚመለከት ነው። ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያላቀረቡትንና በኋላ ላይ በታክስ ዕዳ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ አዲስ ማስረጃ ሲያቀርቡ የሚጣልባቸው ቅጣት እንዲሻሻል ተደርጓል። በዚህም መሠረት ታክስ ከፋዩ ሊከፈል ከሚገባው የታክስ ዕዳ ላይ 10 በመቶ (ቀድሞ 20 በመቶ የነበረው) ቅጣት እንዲከፍል በማሻሻያው ተደንግጓል። በተጨማሪም ቋሚ ኮሚቴው በድርጅቶች የሚፈጸሙ የታክስ ወንጀሎችን ተጠያቂነት በተመለከተ ማብራሪያ የሚሰጥ ማሻሻያ አድርጓል። የታክስ ሕግን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመው ድርጅት ወይም በግለሰብ ባለቤትነት ሥር ያለ የንግድ ድርጅት በሚሆንበት ጊዜ፣ ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም የፋይናንስ ኃላፊ ተጠያቂ የሚሆኑበት አግባብ ተመቻችቷል። ይህ ማሻሻያ የተደረገው የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመ የየትኛውም ድርጅት ስራ አስኪያጅ ተጠያቂ ማድረግ ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት እንደሆነ ተመላክቷል።
144
8
Matn yo'q...
163
9
የታክስ አስተዳደር አዋጅ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 23፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ፣ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። 👉 አዲሱ አዋጅ ደረሰኝ ሊሰጥ ሲገባው ያልሰጠ ማንኛውም ታክስ ከፋይ በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር መቀጫ የሚጥል ነው።
184
10
የፅናትና የስኬት ማማ፡ ከቀን ስራ ወደ ህግ ምሩቅነት! ትናንት ኑሮን ለማሸነፍና ለነገው ማንነቱ መሰረት ለመጣል በከባድ የቀን ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው ይሄው ጠንካራ ወጣት፣ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲ
የፅናትና የስኬት ማማ፡ ከቀን ስራ ወደ ህግ ምሩቅነት! ትናንት ኑሮን ለማሸነፍና ለነገው ማንነቱ መሰረት ለመጣል በከባድ የቀን ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው ይሄው ጠንካራ ወጣት፣ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (Mizan-Tepi University) በህግ ትምህርት ዘርፍ በደማቅ ሁኔታ ተመርቆ የድካሙን ፍሬ አጭዷል። ይህ ለነገ እቅዳቸውና ህልማቸው ሌሊት ከቀን ለሚደክሙ በርካታ ወጣቶች ትልቅ ተስፋንና መነቃቃትን የሚፈጥር እውነተኛ የስኬት ማማ ነው። ማንኛውም ሰው አሁን ያለበት አስቸጋሪ ሁኔታ የህይወቱን የመጨረሻ ምዕራፍ ሊወስን እንደማይችል ይህ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመዘገበው ደማቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው። በትጋትና በቆራጥነት ከተሰራ ትናንት በከባድ የጉልበት ስራ ውስጥ የነበረው ማንነት፣ ዛሬ የፍትህና የህግ ባለሙያ ሆኖ ለመቆም እንደሚያስችል በሚገባ ያሳየናል። እኛም ለዚህ ብርቱ ወጣት ለደረሰበት ትልቅ የስኬት ምዕራፍ ያለንን ጥልቅ አድናቆት እየገለጽን፣ ለቀጣዩ የሙያ ህይወቱ መልካም ምኞታችንን እንመኛለን። ህልም ኖሯችሁ ነገር ግን መንገዱ አልጋ በአልጋ ላልሆነላችሁ ወጣቶች ሁሉ ይህ አስደናቂ ጉዞ ትልቅ ብርታትና መማሪያ እንደሚሆን እናምናለን።
206
11
'የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ረቂቅ'
213
12
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞችን አዋጅ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 309/2018
237
13
“የሸሪዓ ሕጉን መሠረት ያደረጉ ስምምነቶችን” የመዳኘት ሥልጣን የሚሰጠው የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18/2018 ባካሄደው አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የተሻሻለውን የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል፡፡ አዋጁ ተጠሪነቱ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሆነ “የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔ” እንዲቋቋም የሚፈቅድ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ረቂቁን ያጸደቀው ከሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ከመረመረ በኋላ ነው፡፡ አዲሱ አዋጅ በ1992 “የሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን አቋም ለማጠናከር” በሚል የጸደቀውን  የሚሽር ነው፡፡ በተሻረው አዋጅ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች ጋር “የወል ዳኝነት” የሚኖራቸው በውስን ጉዳዮች ላይ ነበር፡፡ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት በአዋጁ የተቀመጠው “የጋብቻ፣ የፍቺ፣ የቀለብ አወሳሰን፣ አካለ መጠን ያልደረሱ ሕጻናት ሞግዚትነት፣ የወቅፍ፣ የሥጦታ ወይም የኑዛዜ ጉዳዮች”ን ነበር፡፡ የተሻሻለው አዋጅ በተመሳሳይ ለሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በሸሪዓ ሕጉ ላይ የተመሠረቱ “የጋብቻና የጋብቻ ውጤት፣ የፍቺና የፍቺ ውጤት፣ የቀለብ አወሳሰን፣ አካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናት አስተዳደግና ሞግዚትነት ወይም በቤተሰብ ተዛምዶና የሕግ ችሎታ ያጡ ሰዎች ላይ የሚነሱ ጉዳዮች”ን እንዲሁም “የወቅፍና የወቅፍ አስተዳደር (ናዚርነት)፣ የሥጦታ (ሂባ)፣ የውርስ፣ ውርስ ማጣራትና ውርስ ሐብት ክፍፍል ወይም የኑዛዜ ጉዳዮችን የተመለከቱ ጉዳዮች”ን እንዲዳኙ “የወል ሥልጣን” ይሰጣል፡፡ አዲሱ አዋጅ ከዚህ ቀደም ያልነበሩ ጉዳዮችንም ያካተተ ነው፡፡ በዚህም አግባብ ለሸሪዓ ፍርድ ቤት በግልጽ “የሸሪዓ ሕጉን መሠረት አድርገው የተመሠረቱ ስምምነቶችና ግንኙነቶችን” የመዳኘት ሥልጣን ይሰጣቸዋል፡፡ በኅዳር 2017 ለውይይት በቀረበው “የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የሕግ ማዕቀፍ፣ አደረጃጀት፣ የሰው ኃይል አስተዳደርን ችግሮች በመለየት የመፍትሔ ሐሳብ ለማቅረብ በተዘጋጀ” ሠነድ ላይ እንደሠፈረው፤ “ሸሪዓን መሠረት ያደረገ ባንክ፣ ኢንሹራንስ፣ የሙአለ ንዋይ ገበያ (ካፒታል ማርኬት) እና ሌሎች የሸሪዓን ሕግ መሠረት አድርገው የተመሠረቱ ስምምነቶችና ግንኙነቶች” ጋር በተያያዘ የሚነሱ አለመግባባቶችን” የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች እንዲዳኙ ምክረ ሐሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ አዲሱ አዋጅ በተጨማሪም “በውጪ ሀገር የሞቱ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የቀብር ሥነ ሥርዓት እንዲፈጸም የሚፈቀድንና የጋብቻ ሥነ ሥርዓትን የሚያከናውኑ የሸሪዓ አጋቢዎች ፍቃድ መስጠትን” አካቷል፡፡ ከፍቺ ጋር በተገናኘ “በመደበኛ ፍርድ ቤት የተሰጠ የፍቺ ውሳኔን መሠረት በማድረግ ኒካህ እንዲወርድ የሚቀርብ ጥያቄን” በተመለከተ የመዳኘት ሥልጣን ይሰጣል፡፡ የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባዔ እንዲቋቋም የሚያደርገው አዋጁ፤ ይህ ጉባዔ ተጠሪነቱ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሆኖ የራሱ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ተቋም መሆኑን ደንግጓል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ የፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ የፌደራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አንድ ተወካይ፣ በፌደራል ሽሪዓ ፍርድ ቤቶች ዳኞች የጋራ ስብሰባ የሚወከል አንድ የዳኞች ተወካይ፣ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዑለማ ጉባዔ አባላት ውስጥ ሁለት ተወካይ፣ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የሚወከል በዳኝነት ሥራ የረዥም ጊዜ ልምድ ያለው ሙስሊም የፌደራል ፍርድ ቤት ዳኛ፣ በሞያዊ ብቃት፣ በስነ ምግባሩ የተመሰገነና ማህበራዊ ተቀባይነቱ ከፍ ያለ፣ ለሕግ የበላይነትና ለሸሪዓ ፍትሕ ሥርዓቱ እድገት ቁርጠኝነት ያለውና የጎላ አስተዋጽዖ ያበረከተ ወይም ለማበርከት ይችላል ተብሎ የሚገመት በጉባዔው የሚመረጥ አንድ ሰውን በአባልነት ያካትታል፡፡ ከጉባዔው አባላት ውስጥ ቢያንስ ሁለት ሴቶች በተወካይነት እንደሚካተቱም ይደነግጋል፡፡ በኢትዮጵያ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በመንግሥት ድጋፍ የተቋቋሙት በ1934 ነው፡፡
275
14
​⚖️ ​በስርቆት ወንጀል አንድ ተከሳሽ "ሰርቋል" ለመባል ንብረቱን መንካት፣ መቁረጥ...ወዘተ ብቻውን በቂ ነውን? ወይንስ ንብረቱ የግድ ወደ ተከሳሹ ይዞታ መግባት አለበት? * የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 230945 ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል። ​🔍 የይዞታ ለውጥ (Possession) እና ስርቆት ​በወንጀል ህግ አንቀፅ 665 መሠረት፣ ስርቆት የሚፈፀመው አንድን ዕቃ አንስቶ በመውሰድ (Taking away) እና በራስ ይዞታ ስር በማድረግ ነው። ይህ ማለት፦ ​ንብረቱ ከባለቤቱ ቁጥጥር መውጣት አለበት። ​ንብረቱ ወደ ወንጀል አድራጊው ይዞታ መግባት አለበት። ​📍 የሰበሩ ክርክርና ውሳኔ ​በዚህ መዝገብ ላይ ተከሳሹ የኤሌክትሪክ ፖል (ምሶሶ) ብረትን በመጋዝ ሲቆራርጥ እጅ ከፈንጅ ተይዟል። ​የበታች ፍርድ ቤቶች እይታ፦ ብረቱን ለመስረቅ መቁረጥ መጀመሩ "ፍፃሜ ያገኘ ስርቆት" ነው በሚል ጥፋተኛ አድርገውት ነበር። ​የሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም፦ ተከሳሹ ብረቱን እየቆረጠ እንጂ አንስቶ አልወሰደም። ንብረቱ ገና ከምሶሶው ተለይቶ ወደ ተከሳሹ ቁጥጥር (ይዞታ) አልገባም። ​💡 ዋናው የህግ ነጥብ ​ድርጊቱ በቆረጣ ላይ እያለ መቋረጡ፣ የይዞታ ለውጥ (Change of Possession) እንዳልተከናወነ ያሳያል። በመሆኑም፦ ​ንብረቱ ወደ ተከሳሹ እጅ ካልገባ ድርጊቱ "የስርቆት ሙከራ" (Attempt) እንጂ ፍፃሜ ያገኘ ወንጀል ሊባል አይችልም። ​በመሆኑም ተከሳሹ በወንጀል ህግ አንቀፅ 27(1) እና 669(1)(ለ) መሠረት በስርቆት ሙከራ ብቻ ሊቀጣ ይገባል ሲል ወስኗል። ​📢 ማጠቃለያ፦ አንድን ንብረት ለመስረቅ መሰናዳት ወይም ንብረቱን ለመውሰድ የሚያስችል ተግባር ላይ እያሉ መያዝ (ለምሳሌ፡ መቁረጥ፣ መፍታት...) ነገር ግን ንብረቱን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር አውሎ አለመውሰድ በህጉ በ"ሙከራ" ደረጃ የሚያስቀጣ ተግባር ነው።
189
15
🧬 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ በቤተሰብ እና ማስረጃ ሕግ: ቁልፍ የሰበር ውሳኔ መርሆዎች ⚖️  1. 🛡 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ መከላከያ ማስረጃ እንጂ እንደ ፍርድ ቤት ግዴታ ያለመወሰዱ ➡️ በአባትነት ማረጋገጫ ክስ ላይ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ አባትነትን ለማረጋገጥ የሚቀርብ የመከላከያ ማስረጃ እንጂ፣ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያዝ የሚገባው አይደለም። የአባትነት ክስ ሲቀርብ ተከሳሹ መጥሪያ ደርሶት ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ የመከራከር መብቱን ራሱ የተወ ከሆነ፣ ቀርቦ የመከላከያ መብቱን ስላልተጠቀመ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ የመጠየቅ መብቱን ከክሱን ከመከላከል ጋር እንደተወ ይቆጠራል [ሰ/መ/ቁ 154767]። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሌለበት ውሳኔ መስጠቱ ስነ ስርዓታዊ አግባብን የጣሰ አይደለም [ሰ/መ/ቁ 154767]። 2. 📜 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ በሦስተኛ ወገን (ኑዛዜ ተጠቃሚ) ሲጠየቅ ❌ የቤተሰብ ሕግ የአባትነት መካድ ክስ ሊያቀርቡ የሚችሉ ወገኖችን ማንነት ይገድባል። የኑዛዜ ተጠቃሚ የሆነ ሦስተኛ ወገን፣ የመካድ ክስ ለማቅረብ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ እንዲሁም የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚያስፈልገውን የፍርድ ቤት ፈቃድ አስቀድሞ ባለማግኘቱ፣ ያለምንም ሕጋዊ መሠረት የዘረመል (D.N.A) ምርመራ እንዲደረግ ማዘዙ ከመነሻው በሕጉ የተመለከተውን ሥርዓት ያልተከተለ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው [ሰ/መ/ቁ 152719]። 3. 🔨 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ ባለመፈጸሙ ምክንያት በፍሬ ነገር ላይ መወሰን ⏳ ለቀጠሮ ምክንያት የሆነው ጉዳይ (እንደ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ውጤት) ሳይፈጸም የቀረው ከተከራካሪ ወገኖች በአንዱ ጉድለት ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን መፈጸም ሳይጠብቅ የመሰለውን ውሳኔ ለመስጠት ይችላል [ሰ/መ/ቁ 152100]። በመሆኑም፣ ፍርድ ቤቱ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ፣ ትዕዛዙን አልፎ በሌሎች ማስረጃዎች (ለምሳሌ በሰው ምስክር ቃል) ላይ ተመስርቶ የሟች ልጅነትን ማጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አይደለም [ሰ/መ/ቁ 152100]። 4. ⚖️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ ገዥ (Conclusive) ማስረጃ አለመቆጠሩ እና ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር መመዘን 🔬 የዘረመል (DNA) ምርመራ ውጤት ብቻውን ፍፁማዊ ገዥ (conclusive) ማስረጃ አይደለም ። አባትነትን የማረጋገጥ ዓላማ ሲኖር፣ የምርመራ ውጤቱ በሌሎች የማስረጃ ዓይነቶች (ለምሳሌ ልጁን እንደ አባት በመንከባከብ፣ የሰው ምስክር ቃል ወይም የልጅነት ሁኔታ) ሊረጋገጥ ከሚችለው ፍሬ ነገር ጋር ተመዝኖ መታየት አለበት ። 5. 👂 የሳይንሳዊ ማስረጃን የመስማት ግዴታ (ለማስተባበል) 🚨 ፍርድ ቤቶች በተከራካሪ ወገኖች የልጅነት ግምትን ለማስተባበል ሲባል የዘረመል ምርመራ እንዲደረግ የቀረበውን አቤቱታ በአግባቡ ማስተናገድ አለባቸው ። 🛑 አንድ ወገን የልጅነት ግምትን ለመቃወም የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ እያለ ፣ የስር ፍርድ ቤት ጥያቄውን ሳይመረምር ወይም ውድቅ ያደረገበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ ፣ እንዲሁም በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ አባትነትን ማረጋገጡ የሰበር ሰሚ ችሎት ገዥ ትርጉም የሚፃረር መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው ። 📝 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በልጅነት ሁኔታ (circumstantial evidence) የተረጋገጠ የሕግ ግምት በሳይንሳዊ ማስረጃዎች እንደ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ ሊስተባበል ይችላል ። 6. 💵 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪ እና የፍትሕ አሰጣጥ 💰 ምንም እንኳን ምርመራውን የጠየቀው ወገን ወጪ የመሸፈን ኃላፊነት ቢኖርበትም ፣ የገንዘብ አቅም አለመኖር ፍትሕን ሊያጓድል አይገባም። ፍርድ ቤቱ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪው በማን ይሸፈን የሚለውን ከሕግ አኳያ አይቶ መወሰን ሲገባው፣ ይህን አለማድረጉ ስህተት ነው ። 7. ⭐️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ጥራት እና ተጨማሪ የባለሙያ አስተያየት ⚰️ ከሟች አስክሬን የተወሰደ የዘረመል (DNA) ናሙና በብክለት ምክንያት አስተማማኝ ውጤት መስጠት ባልቻለበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የበለጠ ግልጽ ለማድረግ ተጨማሪ የልዩ አዋቂ ባለሙያ አስተያየት መስማቱ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 136ን የተከተለ በመሆኑ የሚነቀፍ አይደለም ። 8. 👰‍♀️ በጋብቻ ውስጥ ለተወለደ ልጅ የአባትነት ግምት እና የመካድ ክስ 💍 በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ወይም የተጸነሰ ልጅ የአባትየው ነው ተብሎ በሕግ ይገመታል ። አባትነት በሕግ በተሰጠው ግምት መሠረት የተረጋገጠ እንደሆነ፣ አመልካች የምርመራውን ውጤት ከመጠየቅ በፊት በቤተሰብ ሕጉ በሚፈቅደው አግባብ የመካድ ክስ ማቅረብ ይኖርባታል ። በፍሬ ነገር ደረጃ በጋብቻ ውስጥ መወለድ መረጋገጡ፣ የዘረመል (DNA) ምርመራ ይደረግ የሚለውን ክርክር ተቀባይነት ያሳጣዋል ። 9. 🗑 በሌላ ማስረጃ አባትነት ሲረጋገጥ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራን ውድቅ ማድረግ 📄 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በቂ የሰነድና የሰው ማስረጃዎች በመመርመር እናትነት ወይም ልጅነት የተረጋገጠ እንደሆነ ፣ ፍርድ ቤቶች ተጨማሪ የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ የቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ ሊያደርጉ ይችላሉ ።
708
16
የሰበር መ/ቁ.262248  ጥቅምት 06 ቀን 2017 ዓ.ም                                                 ተከሳሽ ሕጻናት ልጆች ካሉት ቅጣት መገደብ ግደታ ስለመሆኑ =================== ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት ድንጋጌ ቅጣት እንዲገደብ በህጉ  ክልከላ ካልተደረገበት በስተቀር ተከሳሽ ህጻናት ልጆች የሚያስተዳድር መሆኑን ገልጾ ባቀረበበት ፍ/ቤት በህጻናቱ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ቁሳዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት ሲባል ቅጣቱን አለመገደብ መሠረታዊ የህግ ስህተት ስለመሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር  መ/ቁ 262248 በቀን 06/02/2017  በዋለው ችሎት አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል። ©ጠበቃ ሁነኛው በቀለ በማናቸውም ፍ/ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ
516
17
+3
Tax Law Session 4 Slides.pptx
455
18
በአዲስ አበባ በመጪው የክረምት ወቅት ጎርፍ ቢያጋጥም ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ  ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ከተማዋ በከፍተኛ ወጪ እያካሄደችው ካለው የ“ትራንስፎርሜሽን” ስራ በኋላ፣ በክረምት ወቅት የሚከሰት የጎርፍ አደጋ የከተማዋን ገጽታ እንዲያበላሽ እንደማይፈቀድ አስገነዘቡ። ከንቲባዋ ይህንን ያሉት የክረምት ወራትንና የ90 ቀን እቅድን አስመልክቶ ከአመራሮች ጋር በነበራቸው የውይይት መድረክ ላይ ነው። አዲስ አበባ በአሁኑ ወቅት የበርካታ አፍሪካውያን መነጋገሪያ መሆኗን የገለጹት ከንቲባዋ፣ ይህንን ትልቅ ስም ይዞ በጎርፍ ምክንያት ሰው የሚጠቃበት ሁኔታ ከተፈጠረ ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸዋል። "ይህን ሁሉ የከተማ ትራንስፎርሜሽን (transformation) ሰርተን አዲስ አበባ የአለም መነጋገሪያ ሆና፣ የብዙ አፍሪካ ወንድሞቻችን እህቶቻችን መነጋገሪያ ሆና፣ በክረምት ጎርፍ መጥቶ ይሄን ያህል ሰው/ቤት አጠቃ፣ በፍጹም (deserve አናደርግም) አይመጥነንም" በማለት አመራሩ በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል። በተጨማሪም ከፍ ያለውን የከተማችንንና የሀገራችንን ስም ይዞ የተነሳውን ስራ(የከተማዋን ልማት) በጣም ያጎድፈዋል ነው ያሉት። በተለይም በቅርቡ በተካሄዱት የኮሪደር ልማት ስራዎች ወቅት ሳይታዩ የታለፉ ወይም የተዘጉ የጎርፍ መውረጃዎች ካሉ፣ ክረምቱ ከመግባቱ በፊት በፍጥነት መለየትና ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ከንቲባዋ አሳስበዋል። ለዚህም ስራ ከማዕከል ይልቅ ክፍለ ከተሞች ቀጥተኛ ተጠያቂነት እንዳለባቸው ገልጸው " ከማንም በላይ ግን ክፍለ ከተሞች ናቸው ተጠያቂዎች በዚህ ቦታ ይሄ ቢያጋጥመን (ጎርፍ)፣ አንደኛ እዛ ህዝብ ውስጥ ውላችኋል ታድራላችሁ ትሰራላችሁ ከማህበረሰቡ ጋራ ተቀራርባችሁ ታውቃላችሁ ችግር ያለበትንም ታውቃላችሁ የማዕከል ሴክተር ሁሉም ቦታ እንዲያውቅ አንጠብቅበትም እያንዳንዱ ወረዳ እያንዳንዱ ክፍለ ከተማ አካባቢውን እንዲያውቅ ይጠበቃል" በማለት ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። ከንቲባዋ አያይዘውም በክረምቱ በጎ ፍቃድ ስራ ሲከናወን በመንግስት በጀት ላይ ብቻ ሊደገፍ እንደማይገባ አስገንዝበዋል። አመራሩ የግል ባለሃብቶችንና ኮንትራክተሮችን በማስተባበር ማሽነሪዎችንና የሰው ሃይልን ለጽዳትና ለጥገና ስራ እንዲያሰማሩ መመሪያ ሰጥተዋል። “ማህበራትና ኮንትራክተሮች አሁን ካልረዱን ታዲያ መቼ ነው የሚረዱን?”ሲሉ የጠየቁት ከንቲባዋ፣ እያንዳንዱ ወረዳና ክፍለ ከተማ አካባቢውን ጠንቅቆ በማወቅ የተለየ የርብርብ ስራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል
372
19
የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አመራረት፣ አሰረጫጨት እና አወጋገድ ላይ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት መፈጠር እንዳለበት ተመላከተ። ሰኔ 8/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):-የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ+2
የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አመራረት፣ አሰረጫጨት እና አወጋገድ ላይ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት መፈጠር እንዳለበት ተመላከተ። ሰኔ 8/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):-የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለክልል የትራንስፖርት ዘርፍ እና የከተማ መስተዳድር ኃላፊዎች በዘርፉ በወጡ አዋጆች ፣ ደንቦች ፣እና መመሪያዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አመራረት፣ አሰረጫጨት፣ አወጋገድ ላይ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት መተግበር ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር አለሙ ሰሜ አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ( ታርጋ) ለውጥ ተመሳሳይ ታርጋዎችን ለማስቀረት፣ ህገ ወጥ ታርጋን ለመከላከል፣ ከተሽከርካሪ ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ፣የተሽከርካሪ ስርቆትን ለማስቀረት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት በመሆኑ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ እንደሚቻል ተናግረዋል። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ በርኦ ሀሰን በበኩላቸው አዲሱ የተሽከርካሪ ታርጋ ለውጥ የትራንስፖርት ዘርፉን ሪፎርም ለማድረግ፣ የዘርፉን ፓሊሲ ለማሳለጥ እና ወጥ የሆነ መረጃ አያያዝ እንዲኖር በማስቻል ሀገራዊ የዘርፉ ስታንዳርድ ከፍ የማድረግ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ ከነባሩ ታርጋ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲቻል፣ ከተሽከርካሪ መረጃ አያያዝ ጋር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት፣ የተሳለጠ እና የተናበበ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር ለማስቻል አዲሱ የተሽከርካሪ ታርጋ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። @law8studies
404
20
💡 የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ ሥርዓት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1142/2018 የታክስ አስተዳደር ሥርዓትን ማዘመንና ከወቅቱ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር ማጣጣም የአንድ አገር ኢኮኖሚ በጤናማ ሁኔታ ለመራመድ ካሉት መሠረታዊ ምሰሶዎች አንዱ ነው። ይሁን እንጂ ይህ መመሪያ እስካሁን ሳይወጣ መቆየቱ በታክስ አሰባሰብ፣ በዲጂታል ንግድ ቁጥጥርና በሕግ ተፈጻሚነት ረገድ በርካታ መዋቅራዊ ክፍተቶችን ፈጥሮ ቆይቷል። በተለይም ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው የኢኮሜርስ (e-Commerce) ዘርፍ፣ የኦንላይን የገበያ መድረኮች እና የተለያዩ የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ግልጽና ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ስላልነበራቸው መንግሥት ማግኘት የሚገባውን የታክስ ገቢ እንዲያጣ ከማድረጉም በላይ ሕጋዊ ታክስ ከፋዮች ካልተመዘገቡ ነጋዴዎች ጋር ፍትሐዊ ያልሆነ የገበያ ውድድር ውስጥ እንዲገቡ አስገድዶ ነበር። በተጨማሪም የወረቀቱ የደረሰኝ አሰጣጥ ሥርዓት ለታክስ ስወራ፣ ለሐሰተኛ ደረሰኝ ዝውውርና ለአሠራር መጓተት ሰፊ በር ከፍቶ መቆየቱ ይታወቃል። ይህ አዲስ የወጣው መመሪያ ቁጥር 1142/2018 እነዚህን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የሚከተሉት ከፍተኛ ፋይዳዎች አሉት፦ 💡 የታክስ ስወራን መከላከልና ገቢን ማሳደግ፡ እያንዳንዱ ግብይት በተከናወነበት ቅጽበት (Real-time) በቀጥታ ከባለሥልጣኑ ማዕከላዊ ሥርዓት ጋር እንዲገናኝ በማድረጉ እና ደረሰኝ ማተም የሚቻለው የማዕከሉን መለያ ቁጥር (IRN) እና QR Code ሲያገኝ ብቻ በመሆኑ ሐሰተኛ ደረሰኞችን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። 💡 ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግልጽ የሕግ ማዕቀፍ መፍጠር፡ መመሪያው የኢኮሜርስ ኦፕሬተሮችን፣ የክላውድ ሽያጭ መመዝገቢያዎችን እና ሶፍትዌርን እንደ አገልግሎት አቅራቢዎችን ሕጋዊ ኃላፊነት በግልጽ አስቀምጧል። በአንድ መድረክ ላይ ከአንድ በላይ ሻጮች ቢኖሩ እንኳ እያንዳንዱ አካል በገዛ የ-TIN ቁጥሩ ደረሰኝ እንዲቆርጥ በማስገደድ በዲጂታል ገበያው ላይ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል። 💡 የንግድ አሠራርን ማቅለልና ወጪን መቀነስ፦ ታክስ ከፋዮች የሽያጭ መረጃዎችን በዲጂታል አማራጮች (በኢሜይል ወይም በ-SMS) ለገዥዎች መላክ እንዲችሉ በመፍቀድ የሕትመትና የካርቦን ወጪን ከመቀነሱም በላይ ንግዶች የራሳቸውን የውስጥ ሥርዓት ከታክስ ሥርዓቱ ጋር በቀላሉ እንዲያዋህዱ ዕድል ይሰጣል። 💡 የመረጃ ደህንነትና የኦዲት ተአማኒነት፡ ሥርዓቱ ከመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ዕውቅና ማግኘት ያለበት በመሆኑ እና የኦዲት መዝገብ (Audit Log) እንዲኖረው ስለሚያስገድድ፣ የታክስ ከፋዩ መረጃ በምስጠራ (Encryption) ተጠብቆ እንዲቆይና ባለሥልጣኑ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ሕጋዊ ኦዲት እንዲያደርግ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። 💡 የአሠራር ቀጣይነትን ማረጋገጥ፡ የኢንተርኔት መቆራረጥ በሚኖርበት ጊዜ ንግዶች እንዳይደናቀፉ የራሱ የሆነ "ከቀጥታ ግንኙነት ውጭ ሥራ ማስቀጠያ ሥርዓት" (Offline Resiliency) መዘርጋቱ የንግድ እንቅስቃሴው ሳይቋረጥ ታክስ በአግባቡ እንዲመዘገብ ያስችላል። በአጠቃላይ ይህ መመሪያ መውጣቱ በታክስ አስተዳደሩ ላይ የነበሩትን ክፍተቶች በመሙላት የዲጂታልና የሕግ ሥነ-ምኅዳሩን በማቀናጀት፣ ፍትሐዊ የንግድ ውድድር እንዲሰፍንና የአገሪቱ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ሕጋዊ መሠረት እንዲይዝ የሚያደርገው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው። ኮቨናንት ሀብ የጥብቅና ድርጅት
244