Law studies ⚖️
Kanalga Telegram’da o‘tish
Welcome to Law studies telegram channel ⚖️ This channel is dedicated to helping law students succeed. ✔️ Simple & clear law notes ✔️ Past exam questions & answers ✔️ Key articles & case summaries ✔️ Exam tips & important topics
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
365
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+97 kunlar
+2030 kunlar
Ma'lumot yuklanmoqda...
O'xshash kanallar
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Avgust '26
Avgust '26
+1
0 kanalda
Iyul '26
+367
0 kanalda
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 01 Avgust | +1 |
Kanal postlari
+6
# አስደሳች የሕግ ውሳኔ! የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያስተላለፈው ታሪካዊ ውሳኔ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ፣ የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ ወይም ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪዎች በእስር እንዲቆዩ ትዕዛዝ መስጠት ሕገ-ወጥ መሆኑን አብራርቷል።
# ዋና ዋና ነጥቦች፦
የጉዳዩ አመጣጥ፡ አመልካች (አቶ አበበ ዳሙሳ) በተጠረጠሩበት የኃይማኖት ማጥፋት እና የቴሌኮም የገንዘብ ማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ፣ ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ15 ቀን ጊዜ በመስጠት ክስ እንዲመሰረት አዟል።
የቀረበው ክርክር፡ "የምርመራ ጊዜ ተሰጥቶ ክስ ሳይመሰረት እና ከእስር ሳይፈቱ እንደገና ለሁተኛ ጊዜ የምርመራ ጊዜ መጠየቅ ሕገ-ወጥ ነው፤ የሰዎች የነፃነት መብት ሊከበር ይገባል" የሚል የሰበር ቅሬታ ቀርቧል።
የሰበር ችሎት ትንተና፡
በሕገ መንግሥቱ አንደ 17/2 እና 19/6 መሠረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገው ሥርዓት ውጪ ነፃነቱ ሊነፈግ እንደማይችል ተደንግጓል።
የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ እና ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪውን ከእስር ሳይፈቱ በተደጋጋሚ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ማራዘም መሠረታዊ የሕግ ስህተት መሆኑ ተረጋግጧል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ፡
የታችኛው ፍርድ ቤቶች የሰጡዋቸው የምርመራ ጊዜ ማራዘሚያ ትዕዛዞች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸው በመሆኑ ተሻሽለዋል።
አመልካች 50,000 (አምሳ ሺህ) ብር ዋስትና በማስያዝ ወይም በቂ ዋስትና ቀርቦ ከእስር እንዲፈቱ ተወስኗል።
| 2 | ያለ ዋስ ከ7,000 ብር በላይ ደሞዝ እየከፈለችው አይፎን ስሕኳን ለመስረቅ ሲል ከሰባት ጊዜ በላይ በስለት ወ ግቶ ህይወቷ በአሰቃቂ በሆነ ሁኔታ እንዲያልፍ ያደረገው ወጣት
በአዳማ ከተማ "እናት ጓዳ" የተባለውን ተወዳጅ የምግብ ቤት በመክፈት፣ በጥረቷና በልፋቷ ስኬታማ መሆን የቻለችው ወጣት ሄለን ኩማ ትባላለች።
ሄለን ለሰዎች መልካም፣ ቀናና ሰውን አምኖ ለመቀበል ወደኋላ የማትል ደግ ሴት ነበረች። ነገር ግን ይህ መልካምነቷና ሰውን በሙሉ እምነት የመቀበል ልማዷ ሳይታሰብ ወደ ከባድ አደጋና መራራ ሀዘን ይልካታል ብሎ ያሰበ አልነበረም።
ሄለን በሆቴሏ ውስጥ ፍየል የሚያርድና ስጋ የሚያዘጋጅ አንድ ወጣት ቀጠረች። በወር ከ7,000 ብር በላይ ደሞዝ እየከፈለች፣ በስራው ጎበዝ ስለነበር ተጨማሪ ማበረታቻዎችንና ስጦታዎችን እያበረከተችለት እንደ ቤተሰብ አምኖት ለ6 እና 7 ወራት አብረው ሰሩ።
ሆኖም ግን ይህንን ወጣት ስትቀጥረው አንድ ትልቅና ወሳኝ ነገር ዘንግታ ነበር ።ማንነቱን በአግባቡ ሳታጠና፣ ከየት እንደመጣ ሳታረጋግጥ እና ምንም አይነት "ህጋዊ ተያዥ ወይም ዋስ" ሳታስይዝ በደግነቷና በልምድ እምነቷ ብቻ ነበር ያስገባችው።
በአንድ ወቅት ሄለን በስራዋ ያገኘችውን ሞቅ ያለ የእለት ገቢ (ከ40,000 ብር በላይ) እና ገና በቅርቡ በ110,000 ብር የገዛችውን ዘመናዊ አይፎን ስልክ እንዲሁም ሌሎች ስልኮችን ተመለከተ። በውስጡ የነበረው የስግብግብነትና የክፋት መንፈስ ቀሰቀሰና እምነቱን ጥሎ ንብረቷን ለመዝረፍ አቀደ።
በእለቱ ሌሊት ገዳዩ ከወትሮው በተለየ መልኩ ፍየል ለማረድ ወደ ቤቷ መጣ። ከዚህ ቀደም በነበራቸው ስምምነት መሠረት በሩን እንዳያያንኳኳ ሚስኮል አደረገላት። ሄለን በንጹህ ህሊና ተነስታ የግቢውን በር ከፈተችለት።
በር ከፍታ ወደ ቤት ስትመለስ ግን የታጠቀውን የብረት የቡና ሞቀጫ ዘነዘና በማጅራቷ ላይ አረፈባት። በወደቀችበትም በያዘው ስለት/ቢላዋ በሰውነቷ ላይ ከ6 ጊዜ በላይ ወግቶ በጽኑ አቆሰላት።
በዚያው ምሽት ከሌላ አካባቢ (ከአዋሽ/መልካሳ) ለትብብርና ለንግድ ጉዳይ እንግዳ ሆና መጥታ አብራት ያደረችው ውድ ጓደኛዋ፣ የሄለንን የጩኸት ድምፅ ሰምታ ልታድናት ስትሮጥ ትወጣለች። ሆኖም ግን ይህ ጨካኝ ገዳይ እሷንም ምህረት ሳያደርግላት ከ7 ጊዜ በላይ በስለት ወግቶ ህይወቷ እዚያው አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ እንዲያልፍ አደረገ።
ገዳዩ 4 ውድ ስልኮችን ዘርፎ ከአዳማ በመኮብለል ወደ ሞጆ ከተማ አመራ። ነገር ግን የወንጀሉ አስቃቂነትና የሟች ድምፅ ዝም አላለም! የአዳማና የሞጆ ከተማ ህዝብ ከፖሊስ ጎን በመሰለፍ፣ በእግር፣ በሞተርና በታክሲ ወንጀለኛውን ለማደን በቁርጠኝነት ወጣ። በሞጆ መናሀሪያ አካባቢ ሊሰወር ሲል በአካባቢው ህዝብ ንቁ ተሳትፎና በፖሊስ የተቀናጀ ጥረት እጅ ከፍንጅ ተያዘ።
ጉዳዩ በህግ የተያዘ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱም የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች መርምሮ በወንጀለኛው ላይ "የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት" ውሳኔ አስተላልፎበታል። ⚖️
ከዚህ መራራ ታሪክ ለሁላችንም የሚሆን ትልቅ ትምህርት ማመንና መተማመን በህግና በስርዓት ይሁን!
ቤት ሰራተኛ፣ ጥበቃ፣ አራጅ፣ አሽከርካሪም ሆነ የትኛውንም ሰራተኛ በምናስገባበት ጊዜ በደግነትና በበጎነት ብቻ መመራት የለብንም። ማንነታቸውን (Digital Id ኮፒ አድርጎ መያዝ ) ....
ከየት እንደመጡ፣ ቀደም ሲል ምን ይሰራ እንደነበር ሳናጠና እና ሙሉ «ህጋዊ ዋስ/ተያዥ» ሳናስይዝ ሰራተኛ ማስገባት በንብረታችን ብቻ ሳይሆን በህይወታችን ላይ መጫወት ነው።
የህዝብና የፖሊስ ቅንጅት ውጤት፦የአዳማና የሞጆ ህዝብ ያሳየው እርስ በርስ የመረዳዳትና ወንጀለኛን አሳዶ የመያዝ ቁርጠኝነት ለአገራችን ትልቅ ምሳሌ የሚሆን ነው።
አምነሽ ያስጠጋሽውና አበልጽገሽ የቀጠርሽው ሰው ድንገት ገዳይሽ ሲሆን እጅግ ከባድና ልብ ሰባሪ ነው ነገር ግን መልካምነት ህጋዊ አሰራርን አይተካም፤ ሁሌም ጥንቃቄ ያቅደሙ!
ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በግዮን ማለዳ ስም መፅናናትን እንመኛለን ። ነብሷን ይማርልን #RIP እባካችሁን ይህንን መልእክት በማጋራት ወይም ለወዳጅ ዘመድዎ #ሼር በማድረግ የብዙዎችን ህይወትና ንብረት ከታሰበ አደጋ እንታደግ!
@@Law8studies | 169 |
| 3 | Matn yo'q... | 140 |
| 4 | " በፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሳይሰጥ ጋዜጠኞችንና ዋና አዘጋጆችን ለእስራት መዳረግ የተከለከለ ነው " - ወ/ሮ ስመኝ ውቤ
በኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የተዘጋጀው የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 1427/2018 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 18/2018 ዓ.ም. መጽደቁ ይታወቃል።
በዚህ የመረጃ ነጻነት አዋጅ መሠረት፣ በፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ለምርመራም ሆነ ለሌላ ምክንያት ጋዜጠኞችን፣ ዋና አዘጋጆችን እና ከጉዳዩ ጋር የተያያዘ ሌላ ሰው ለእስራት መዳረግ የተከለከለ መሆኑን ዋና ዕንባ ጠባቂዋ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ ገልጸዋል።
ወ/ሮ ስመኝ አክለውም፣ መረጃን በቅን ልቦና ያሰራጨ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያ (ጋዜጠኛ) ከተጠያቂነት ነጻ መሆኑን ተናግረዋል።
" አንድ ጋዜጠኛ ከመንግሥትም ሆነ ከግል ድርጅት በሕጋዊ መንገድ ባገኘው ሰነድ ላይ የተዛባ ወይም የተሳሳተ መረጃ ቢኖር እንኳ፣ ያንን መረጃ ለሕዝብ ያጋራው ወይም ያሳተመው በቅን ልቦና መሆኑ ከተረጋገጠ፣ በሕግ ተጠያቂ አይሆንም " ብለዋል።
በተጨማሪም፣ " ጥፋትን ወይም ጎጂ የሆነ ከባድ አደጋን የተመለከተ መረጃ ለሕዝብ ይፋ በማድረጉ አስተዳደራዊ ወይም ሕጋዊ ቅጣት የተላለፈበት ጋዜጠኛ ለፍርድ ቤት ይግባኝ የማቅረብ መብት አለው " ሲሉ አክለዋል።
አዋጁ ሆን ብሎ መረጃ ወይም ሰነድ ፦
- ያጠፋ፣
- ያበላሸ፣
- የቀየረ፣
- የደለዘ፣
- የደበቀ፣
- ያፋለሰ፣
- በተንኮል የከለከለ፣
- ሐሰተኛ ሰነድ የሠራ
- ሙስናን፣ ሌላ ሕገ-ወጥ አሠራርን፣ የሥራ አፈጻጸም ብቃት ጉድለትን ወይም የግለሰብ፣ የመንግሥት አካል ወይም የድርጅት ቅሌትን ለመሸፈን መረጃን በሚስጥር እንዲያዝ ያደረገ አካል በ5 ዓመት በማይበልጥ እስራት ወይም 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት፣ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ይደነግጋል።
በተመሳሳይ ፦
° የመረጃ ጥያቄን መከልከል፣
° መረጃ አለማውጣት፣
° መረጃ ጠያቂዎችንና አካል ጉዳተኞችን ለመርዳት ፈቃደኛ አለመሆን፣
° ግልባጭ አለመስጠት ወይም ሆን ብሎ ሐሰተኛ መረጃ ማቅረብ እስከ 1 ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራት ወይም ከ25,000 እስከ 50,000 ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ይገልጻል።
እንዲሁም፣ በአዋጁ የተደነገጉ ግዴታዎችን ሆን ብሎ ያልተወጣ አካል ከ25 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር እንደሚቀጣ ተመልክቷል።
ወ/ሮ ስመኝ እንዳሉት፣ የቀድሞው አዋጅ መረጃ የመስጠት ግዴታ የጣለው በመንግሥት ተቋማት ላይ ብቻ ሲሆን፣ አዲሱ አዋጅ ግን ትላልቅ የግል ድርጅቶችን፣ ከመንግሥት ጋር በአጋርነት የሚሰሩ እና የመንግሥትን ውክልና ወስደው የሚሰሩ የግል አካላትንም ጭምር መረጃ እንዲሰጡ ያስገድዳል።
እንደ አዋጁ፣ ማንኛውም ተቋም መረጃ የመስጠት ግዴታ ያለበት ሲሆን፣ ይህንን ግዴታ ለማስፈጸም ራሱን የቻለ የመረጃ ኃላፊ መመደብ ይጠበቅበታል።
በተጨማሪም፣ እያንዳንዱ ተቋም የቀረቡለትን የመረጃ ጥያቄዎች፣ የሰጣቸውን ምላሾች እና የክልከላ ምክንያቶችን የያዘ ዓመታዊ ሪፖርት ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ማቅረብ እንደሚኖርበት፣ ተቋሙም እነዚህን ሪፖርቶች በየዓመቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
አዋጁን ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችሉ ረቂቅ ደንቦችና መመሪያዎች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ወ/ሮ ስመኝ፣ እነዚህ ደንቦች በምክር ቤት እስከሚጸድቁ ድረስም አዋጁን መሠረት በማድረግ ሥራዎች እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። | 230 |
| 5 | Matn yo'q... | 174 |
| 6 | የቅጣት ገደብ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቅጣት አወሳሰን መመሪያ አንጻር ሲታይ፡-
የወንጀል ቅጣት እና አፈጻጸማቸውን በሚመለከት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 87 ላይ የተቀመጠው መርህ በሕጉ የተመለከቱት ቅጣቶች እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ሕጉ ሊደርስበት የሚችለውን ዓላማ ለማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ በሕጉ መሠረት መፈጸም አለባቸው፡፡ ቅጣቶቹ እና የጥንቃቄ እርምጃዎቹ ምን ጊዜም ሰብአዊ ክብርን በሚጠብቅ መንገድ መፈጸም ይኖርባቸዋል በማለት ይደነግጋል፡፡ የዚሁ ሕግ አንቀጽ 88(2) ቅጣቱ ሊወሰን የሚገባው የወንጀል አድራጊውን ግላዊ የአደገኝነት መጠን፤ ያለፈ የሕይወት ታሪኩን፤ ወንጀል ለማድረግ ያነሳሱትን ምክንያቶች እና የአሳቡን ዓላማ፤ የግል ኑሮውን ሁኔታ፤ የትምህርት ደረጃ እንዲሁም የወንጀሉን ከባድነት እና የአፈጻጸሙን ሁኔታዎች በማመዛዘን ነው በማለት ይደነግጋል፡፡ በንዑስ ቁጥር (4) ላይ ደግሞ የቅጣት አወሳሰንን ትክክለኛነት እና አንድ ወጥነት ለማረጋገጥ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቅጣት አወሳሰን መምሪያ ሊያወጣ ይችላል በሚል ተመልክቷል፡፡
የወንጀል ሕጉ ዓላማ ወንጀል እንዳይፈጸም ማድረግ ሲሆን ይህንንም የሚያደርገው ስለወንጀሎች እና ስለቅጣታቸው በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፤ ማስጠንቀቂያነቱ በቂ ባልሆነ ጊዜ ደግሞ ወንጀል ፈጻሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈጸም እንዲቆጠቡ እና ለሌሎች ማስተማሪያ እንዲሆኑ ወይም እንዲታረሙ ማድረግ ነው፡፡
ወንጀል ፈጻሚዎች ሆነ ብለው ወንጀል ለመፈጸም በማሰብ ወይም በቸልተኝነት ከቀላል እስከ ከባድ ቅጣት የሚያስከትሉ ወንጀሎችን ይፈጽማሉ፡፡ ዳኞች ወንጀል ፈጻሚዎች ለፈጸሙት ጥፋት የወንጀል ሕጉን ዓላማ እና ግብ በሚያሳካ ሁኔታ ሚዛኑን ጠብቀው ቅጣት መጣል ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን የሚያደርጉትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 88(2) ላይ በተቀመጠው ሁኔታ እንደ ሰው ሚዛን በመመዘን ነው? ወይስ ቅጣትን ለመገደብ የሚያስችሉ የቁጥር ስሌቶችን በማስላት?
ቅጣት ሲገደብ የፍርዱ ውሳኔ በወንጀለኞች መዝገብ ላይ ተመዝግቦ ከሌላው ውጤት ጋር ነዋሪ የሚሆን በመሆኑ ቅጣትን መገደብ በወንጀለኛው ላይ ቅጣት እንዳይፈጸም የማድረግ ውጤት ብቻ ያለው ሳይሆን ወንጀለኛው ዳግም ጥፋት ከመፈጸም እንዲታቀብ የማድረግ ውጤት ያለው በመሆኑ ቅጣትን መገደብ የወንጀል ሕጉ ዓላማ እና ግብ ከሚሳካባቸው መንገዶች አንዱ ነው፡፡
ቅጣት ሊገደብ የሚችለውም ጥፋተኛ የተባለን ሰው ለጥፋቱ መነሻ የሆኑትን ምክንያቶችን በጠቅላላው በመመልከት በጥፋተኛው ላይ የተወሰነውን ቅጣት ለጊዜው በገደብ እንዲታገድ በማድረግ የወንጀለኛውን ጠባይ ለማረምና ለማሻሻል እንዲሁም ወደ መደበኛ ማህበራዊ ኑሮው ለመመለስ ጠቃሚ መሆኑ በታመነ ጊዜ ስለመሆኑ የቅጣት ገደብን አስመልክቶ ከተደነገጉት የወንጀል ሕጉ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡
ፍ/ቤቶች ቅጣትን ለመገደብ የሚያስችሉ የተለያዩ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ማስባት እንዳለባቸው፤ እነዚህም ሁኔታዎች ወንጀለኛው ቀድሞ ያልተቀጣ ሆኖ ጠባዩም አደገኛነት እንደሌለው የሚታመንበት እንደሆነ፤ጥፋቱ በመቀጮ፤ በግዴታ ስራ ወይም ከሶስት አመት የማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኝነቱን ካረጋገጠ በኋላ ለወደፊት ጠባዩን ለማረም እንደሚችል እምነት ሊጣልበት የሚችል መሆኑና በዚህ ውሳኔ ብቻ እስከ መጨረሻው ሊሻሻል የሚችል መሆኑን ሊያምንበት ይገባል፤ እንዲሁም ጥፋተኛው አስቀድሞ የተፈረደበት ቢሆንም ባይሆንም የተፈረደበትን ቅጣት ከመፈፀሙ በፊት ለተወሰነ ጊዜ ቅጣቱ ታግዶለት አመሉ ቢፈተን ሁለተኛ ጥፋት ከማድረግም የሚታገድ መሆኑና ስለጠባዩም መሻሻል አንድ ፅኑ ማስጠንቀቂያ ብቻ የሚበቃ መሆኑ ፍርድ ቤቱ ያመነበት እንደሆነ ቅጣቱ ከአፈፃፀም ታግዶ እንዲቆይ ሊያዝ የሚችል ስለመሆኑ ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 192 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ያስገነዝባሉ፡፡
ጥፋተኛው ከዚህ በፊት የጽኑ እሥራት ቅጣት ወይም ከሦስት ዓመት የሚበልጥ ቀላል እሥራት ቅጣት ተፈርዶበት እንደሆነ እና እንደገናም በተከሰሰበት ወንጀል ከእነዚህ ቅጣቶች አንዱ የሚወሰንበት እንደሆነ ወይም ጥፋተኛው ከዚህ ቀደም ያልተቀጣ ሆኖ በተከሰሰበት ወንጀል ከአምስት አመት የበለጠ የጽኑ እሥራት ቅጣት የሚፈረድበት እንደሆነ በጥፋተኛው ላይ የተወሰነው ቅጣት እንዳይገደብ የሚያደርጉ ሁኔታዎች መሆናቸውን በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 194 ድንጋጌ ላይ በዝርዝር ተመልክቷል፡፡
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 88(4) በተሰጠው ስልጣን መሠረት የቅጣት አወሳሰን ትክክለኛነት እና ወጥነትን ለማረጋገጥ የቅጣት አወሳሰን መመሪያ 1 እና 2 አውጥቶ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ አሁን ደግሞ የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ወጥቶ በስራ ላይ ውሏል፡፡
አዲሱ የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ከያዛቸው አዲስ ሐሳቦች ውስጥ በአባሪ ሶስት ላይ የተቀመጠው የእስራት ቅጣትን በገደብ የማቆየት ውሳኔ አሰጣጥ ሰንጠረዥ ነው፡፡ ይህ ሰንጠረዥ ቅጣት ለመገደብ ታሳቢ የሚሆነውን ምክንያት፤ ለምክንያቱ የሚያዘውን ነጥብ እና ጥፋተኛ የተባለው ሰው ያገኘው ነጥብ የሚሞላበትን ሰንጠረዥ የያዘ ነው፡፡ ሰንጠረዡ እንደሚያመለክተው ለእያንዳንዱ የቅጣት መገደቢያ ምክንያት ዳኞች ከ - እስከ በማለት ፍቅድ ስልጣን አስቀምጦ የሚሰጡትን መነሻ እና መድረሻ ነጥብ አስቀምጧል፡፡ በዚሁ አግባብ ተሰልቶ ጥፋተኛ የተባለው ሰው የሚያገኘው ነጥብ ከመቶ እንደሚሰላ ያሳያል፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት የሚመጣው ነጥብ ቅጣቱን ለመገደብ ጥቅም ላይ የሚውል መሆኑን መመሪያው ያሳያል፡፡
የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባወጣው የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 በአባሪ ሶስት ላይ ያስቀመጠው የእስራት ቅጣትን በገደብ የማቆየት ውሳኔ አሰጣጥ ሰንጠረዥ ዳኞች ወንጀል ፈጻሚዎች ለፈጸሙት ጥፋት የወንጀል ሕጉን ዓላማ እና ግብ በሚያሳካ ሁኔታ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 88(2) ላይ በተቀመጠው ሁኔታ እንደ ሰው ሚዛናቸውን ሳይስቱ መዝነው የቅጣት ገደብን ለመፍቀድ ወይም ለመንፈግ የሚያስችል ነው ? ወይስ ቅጣትን ለመገደብ የሚያስችሉ የቁጥር ስሌቶችን በማስላት ብቻ ውሳኔ እንዲወስኑ የሚያስገድድ ? የሚለው ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ነው፡፡
#እትመትአሰፋ
source #Etmet Assefa fb page | 196 |
| 7 | በመኪና_ሽያጭ_ጉዳይ_ላይ_በተደረጉ_ክርክሮች_በሰበር_የተሰጡ_ወሳኔዎች_.pdf | 149 |
| 8 | ~
የጥፋተኝነት ድርድር” (plea bargaining) ማለት ምን ማለት ነው?
Plea bargaining (የጥፋተኝነት ድርድር) ማለት በወንጀል ፍትህ ስርአት ውስጥ ተከሳሽ (defendant) ከአቃቤ ሕግ (prosecutor) ጋር ጥፋተኛ ነኝ ብሎ ከስምምነት ሲደርስ የሚፈጠር ሂደት ነው።
አዲሱ የወንጀል ስነስርዓትና የማስረጃ ሕጋችንም አዋጅ ቁጥር 1410/2018ዓ.ም ከአንቀጽ 169-179 ባሉት ድንጋጌዎች ይህን ሀሳብ ይዞ ተከስቷል
በአሜሪካ የወንጀል ፍትህ ስርአት ያለው ሚና የወንጀል ጉዳዮች ከ90% በላይ መደበኛ ክርክር ሳይደረግባቸው በጥፋተኝነት ድርድር(Plea bargaining) እልባት እያገኙ ነው
በዚህም መሰረት የሚያስገኛቸው ትሩፋቶች:-
1ኛ. የቅጣት መቀነስ፦ ተከሳሹ ክሱን ስለሚቀበል
ከመደበኛ ቅጣት ያነሰ ቅጣት ይቀበላል
2ኛ. የክስ መቀነስ፦ ከከባድ ወንጀል → ወደ ቀለል ወንጀል ሊቀየር ይችላል
3ኛ. ፍርድ ሂደት መቀነስ፦ ሙሉ ፍርድ (trial) ሳይካሄድ ጉዳዩ በፍጥነት ይቋረጣል
4ኛ. የጊዜና ወጪ ቅናሽ፦ ለፍርድ ቤት,
ለመንግስትና ለተከሳሽ
5ኛ. እርግጠኛ ውጤት (certainty)
ተከሳሹ የሚቀበለውን ቅጣት ቀድሞ ያውቃል
ከከፍተኛ አደጋ (ከባድ ፍርድ) ይድናል።
አሉታዊ ጎኖች(Negative effect)
1, ንፁሐን ሰዎች ሊጫኑ ይችላሉ
2, ፍትሕ ሙሉ በሙሉ አይፈጸምም ሊባል ይችላል
3, የአቃቤያን ሕግ ኃይል ሊበዛ ይችላል።
በአጠቃላይ በሀገራችን የወንጀል ፍትህ ስርአት ውስጥ የዘመኑ አንድ አዲስ ገፀ- በረከት ነው። | 251 |
| 9 | ዕለታዊ🛎
ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች
⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖⚖
✍ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች የምንላቸው በወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 84 ስር የተዘረዘሩት ናቸው፡፡
ሀ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በከሀዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በወራዳነት ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኝነት፣ጥላቻ፣ ስግብግብነት፣ መጥፎ ነገርን ለመስራት ወይም ሰውን ለመጉዳት ፍጹም ፍቃደኛ በመሆን ወይም በተለየ ክፋት ወይም ጨካኝነት እንደሆነ ፡፡
በዚህ ድንጋጌ መሰረት ቅጣትን ለማክበድ ከመካከላቸው የአንዱ መሟላት በቂ ነው፡፡
ለ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ስልጣኑን፣ ተግባሩን ወይም የተጣለበትን እምነት ወይም ሀላፊነት ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ
የመንግስትን ስራ ለመስራት ወይም ለመምራት ስልጣን የተጣለበት ሰው ስራውን በታማኝነት እና በቅንነት መፈጸም አለበት፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ስልጣን ተገን በማድረግ ለራሱም ሆነ ለሌላው ጥቅም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ አንድን ወንጀል ከፈጸመ ቅጣት ሊከብድበት እንደሚገባ የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡
ሐ.ወንጀለኛው በቀድሞ ጥፋተኛነቱ ወይም ወንጀልን ማድረግ ሙያ ወይም ልማድ አድርጎ መያዙ፣ ወይም የወንጀሉ አፈጻጸም ዘዴ፣ ጊዜ፣ ቦታና የአፈጻጸም አኳሀን፣ በተለይም በሌሊት ወይም በሽብር ወይም በሁከት ለአደጋ ሽፋን ወይም በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ ወንጀሉን በማድረግ የተለየ አደገኝነቱን አሳይቶ እንደሆነ ::
በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ እነኚህም፡-
1.ወንጀልን ማድረግ ሙያው ወይም ልማዱ አድርጎ መያዝ
2.የወ/ል አፈጻጸም ዘዴ፣ጊዜ፣ቦታ እና የአፈጻጸም አኳሀን
3.ወንጀልን በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ መፈጸም ናቸው፡፡
በተጨማሪም ሌሊት የሚለው ሀረግ ከስንት ሰዓት ጀምሮ እንደሆነ አሻሚ ቢሆንም በተለምዶ ፍርድ ቤቶች ከሌሊቱ 6፡00-12፡00 ድረስ ያለውን የጊዜ ገደብ በሌሊትነት ወስደው ቅጣት ያከብዱበታል፡፡
በእጅ ወይም በዱላ የውንብድና ወንጀልን የፈጸመ ሰው እና የስለት ወይም የጦር መሳርያዎችን ተጠቅሞ ይህንኑ ወንጀል የፈጸመ ሰው የወንጀል ማድረግ አደገኛነቱ እኩል ሊሆን አይችልም፡፡
መ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ወንጀል ለመፈጸም በተደረገ ስምምነት መሰረት ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ወይም ወንጀል ለመፈጸም ከተቋቋመ ቡድን ጋር በመስማማት ወይም አባል በመሆን ይልቁንም እንደ ወንጀል ቡድን ሹም ወይም አደራጅ ወይም መሪ በመሆን እንደሆነ ::
ወንጀልን ለመፈጸም ከሌላው ጋር ወይም ለዚሁ አላማ ከተደራጀ ቡድን ጋር በአባልነት በመስማማት ወንጀልን ማድረግ ቅጣትን ሊያከብድ የሚችል በቂ ምክንያት ነው፡፡
ሠ.ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በዕድሜው፣ በጤንነቱ፣ በኑሮው ወይም በስራው ሁኔታ ልዩ ጥበቃ በሚያሻው ሰው ላይ በተለይም ለመከላከል አቅም በሌለው፣ መንፈሰ ደካማ፣ በሽተኛ ወይም አካል ጉዳተኛ ፣ እስረኛ ወይም በቅርብ ዘመዱ ላይ ወይም የበላዩ ወይም የበታቹ በሆነ ሰው ላይ፣ በህግ በተቋቋመ ባለስልጣን ወይም የስራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንድ የህዝብ አገልጋይ በሆነ ሰራተኛ ላይ እንደሆነ ቅጣቱ ሊከብድበት ይችላል :: | 377 |
| 10 | ድሬዳዋ ፦ የወላጅ አባቱን ሀብት ለመውረስ በማሰብ ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ በተባባሪው ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደ።
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት በድሬዳዋ ከተማ ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ 1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን አሊዬ ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከግብረ አበሩ 2ተኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን የወላጅ አባቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋሉ።
ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ዱካቸውን ለማጥፋትና በከተማዋ እንዳልነበሩ ለማስመሰል ወዲያውኑ ወደ አዲስ አበባ በያዙት የግል ተሽከርካሪ ይኮበልላሉ።
ነገር ግን ወንጀለኞቹ ከህግ ማምለጥ አልቻሉም።
የድሬዳዋ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወንጀለኞቹ ጥለውት የሄዱትን አነስተኛ ፍንጮች በመከተል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል።
ፖሊስ ያደራጀውን የምርመራ መዝገብ የተረከበው የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት (አቃቤ ህግ)፣ የቀረቡትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በመተንተን ክሱን በፍርድ ቤት ሲከታተል ቆይቷል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፦
1ኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን የወላጅ አባቱን ህይወት በመቅጠፉ በሞት ቅጣት እንዲቀጣ
2ኛ ተከሳሽ ሊበን ወንደሰን በቅንጅት በመሳተፉ በ 20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖባቸዋል።
ይህ የሞት ፍርድ ቅጣት የሚፈጸመው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ርዕሰ ብሔር ፍርዱን ሲያፀድቁ ብቻ ነው። የመዝግቡ ግልባጭም ለርዕሰ ብሔሩ ጽ/ቤት እንዲላክ ፍርድ ቤት አዟል።
ቪድዮ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ | 272 |
| 11 | ስለ የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ማሻሻያ
አጭር ማብራሪያ
***
1.የቁጥጥር እና የአስተዳደር ማዕቀፍ ማሻሻያ
የስልጣን ሽግግር፡ በነባሩ አዋጅ የነበሩ የ"ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ" ስልጣኖች በሙሉ ወደ "ፍትሕ ሚኒስቴር" ተላልፈዋል። ይህም የሕግ ባለሙያዎችን አስተዳደር ከፍትሕ አስተዳደር ጋር በማዋሃድ የአሠራር አንድነትን ለመፍጠር ያለመ ነው።
የውጭ ሀገር ጠበቆች፡ በውጭ ሀገር ፍቃድ ያላቸው ጠበቆች ኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎት ለመስጠት የሚችሉት በፍትሕ ሚኒስቴር ተመዝግበው እና ከአገር ውስጥ ጠበቃ ወይም ድርጅት ጋር በመሆን ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።
2. የብቃት መመዘኛዎች እና የሥራ ልምድ
ማሻሻያው ለጠበቃነት ፍቃድ የሚጠየቀውን የትምህርት ዝግጅት እና የሥራ ልምድ በዲግሪ ደረጃዎች (ዲፕሎማ፣ የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ) ከፋፍሎ አስቀምጧል።
የሙያ መግቢያ ፈተና እንዲኖር የተደነገገ ሲሆን፣ በዳኝነት ወይም በዐቃቤ ሕግነት ረጅም ዓመታት ላገለገሉ ባለሙያዎች ያለፈተና የጥብቅና ፍቃድ የሚሰጥበት ሁኔታ በሕግ መርህ መሰረት ተቀምጧል።
3. የጥብቅና ድርጅቶች አስተዳደር
የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance): ጠበቆች ወይም የጥብቅና ድርጅቶች በሥራ ላይ ስህተት ቢፈጽሙ ለደንበኛ የሚከፈል ካሳን ለመሸፈን የግድ መድን ሊኖራቸው እንደሚገባ ተደንግጓል። ይህ የደንበኛ መብት ጥበቃን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሕግ መርህ ነው።
የአደረጃጀት መፍረስ፡ የድርጅት መፍረስን የሚያስከትሉ ምክንያቶች በግልጽ የተቀመጡ ሲሆን፣ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ ይህን መረጃ ለሚኒስቴሩ የማሳወቅ ግዴታ ተጥሎበታል።
4. የዲስፕሊን ሥርዓት እና ቅጣት
ሰነዱ የዲስፕሊን ጥፋቶችን ወደ "ቀላል" እና "ከባድ" በመክፈል ለቅጣቶች ግልጽነት ፈጥሯል፡
የቅጣት አወሳሰን፡ የገንዘብ መቀጮ፣ የፍቃድ ዕግድ እና የፍቃድ መሰረዝ እርምጃዎች እንደ ጥፋቱ ክብደት ይወሰናሉ። ለምሳሌ፣ የሀሰተኛ ማስረጃ ማቅረብ ወይም ሙስና እንደ ከባድ የዲስፕሊን ጥፋት ተቆጥሮ የፍቃድ መሰረዝ ቅጣትን ያስከትላል።
የመሰየም አቤቱታ (Rehabilitation): በከባድ ጥፋት የተቀጣ ጠበቃ፣ ቅጣቱ ከተፈጸመ ከሁለት ዓመት በኋላ የዲስፕሊን ሪከርዱ እንዲሰረዝለት ለዲሲፕሊን ጉባኤ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው።
5. የአሠራር ግልጽነት
የጠበቆች ማህበር አመራሮች ከአባላት መካከል በምርጫ እንዲሾሙ መደረጉ እና ተጠሪነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤ መሆኑ፣ የአመራር አባላትን ተጠያቂነት የሚያረጋግጥ የዴሞክራሲያዊ አሠራር መርህ ነው።
ፍትሕ ሚኒስቴር ማህበሩን የመቆጣጠር፣ ሕገ-ወጥ መመሪያዎችን የማረም እና አስፈላጊ ድጋፍ የመስጠት ስልጣን ተሰጥቶታል።
በአጠቃላይ፣ ይህ ረቂቅ አዋጅ የጥብቅና ሙያን በሙያዊ ብቃት፣ በኃላፊነት መድን እና በጠንካራ የዲስፕሊን ቁጥጥር ስርዓት ለማንቃት የተዘጋጀ ሰነድ ነው።
የሸሪክ ለውጥ ማሳወቂያ
ማሻሻያው የጥብቅና ድርጅቶችን አሠራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የሚከተለውን ግዴታ አስቀምጧል፡
· ማንኛውም የጥብቅና ድርጅት አዲስ ሸሪክ ሲያስገባ፣ የነበረ ሸሪክ ሲለቅ ወይም ሸሪክ ሲሞት ለውጡን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳወቅ አለበት።
· በዚህ ድንጋጌ መሠረት የሸሪክ ለውጥን አለማሳወቅ እንደ ቀላል የዲስፕሊን ጥፋት ይቆጠራል።
· ይህንን ጥፋት የፈጸመ የጥብቅና ድርጅት ከ15,000 እስከ 25,000 ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።
የሙያ ኃላፊነት መድን (Professional Indemnity Insurance)
ደንበኞችን ከጠበቆች ወይም ከጥብቅና ድርጅቶች ሊደርስባቸው ከሚችል የሙያ ስህተት ለመከላከል የሚከተሉት ድንጋጌዎች ተጨምረዋል፡
· ማንኛውም ጠበቃ ወይም የጥብቅና ድርጅት፣ ሥራውን በአግባቡ ባለመወጣቱ ምክንያት በደንበኛው ላይ ለሚደርስ ጉዳት ካሳ የሚሆን የሙያ ኃላፊነት መድን መያዝ አለበት።
· ጠበቆች የጥብቅና ፍቃድ ሲያወጡ ወይም ሲያሳድሱ ይህንን የሙያ ኃላፊነት መድን የያዙ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
· የዚህ መድን ዋና ዓላማ የደንበኛን መብት በሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ማስጠበቅ እና ለሚፈጠሩ የሙያ ስህተቶች የካሳ ክፍያ ዋስትና መፍጠር ነው።
ጥያቄ- ይህ ማህበር ሲቋቋም እና አዋጁ ሲወጣ ጠበቃው ራሱን በራሱ ለማስተዳደር ሚስችል መሸጋገሪያ ነው ተብሎ ነበር ፣ ጠበቃው ከደካማ እና ተለጣፊ አስተዳደር ተላቆ ከመንገስት ሞግዚተነት ወጥቶ ራሱን በራሱ ማሰተዳደር መች ይሆን የሚጀምረው??????? | 200 |
| 12 | #out_of_topic
'Trust' እና 'Google TV' የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው
በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የባንክ ሂሳብን የሚያጠፉ "Trust"፣ "Google TV" እና "Known" የተባሉ አደገኛ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።
እነዚህ መተግበሪያዎች በተለይ በGoogle Chrome፣ Telegram እና WhatsApp መድረኮች ላይ የሚጋሩ ሲሆን፥ ተጠቃሚዎች ሳያውቁ የገንዘብ ዝውውር በመፈጸም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ።
ይህ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሳይበር ጥቃት በስፋት እየተስተዋለ የመጣው ተጠቃሚዎች ከተላኩላቸው አጠራጣሪ ሊንኮች ላይ መተግበሪያዎቹን ሲያወርዱ መሆኑ ታውቋል። መተግበሪያዎቹ አንዴ ስልክ ላይ ከተጫኑ በኋላ ከሞባይል ባንኪንግ ጋር የተያያዙ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመስረቅ ገንዘብ የመውሰድ አቅም እንዳላቸው ተገልጿል።
ህብረተሰቡ ከዚህ መሰሉ የሳይበር ዘረፋ ራሱን ለመጠበቅ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Play Store ወይም App Store) ብቻ ማውረድ እንዳለበት ባንኩ አሳስቧል።
ከተጠቀሱት የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የሚላኩ አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት እና በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎች ላይ የባዮሜትሪክ (የፊት ወይም የአሻራ) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምሮ መጠቀም ለአደጋው የመጋለጥ እድልን በእጅጉ እንደሚቀንስ ተነግሯል። | 193 |
| 13 | የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን በተመለከተ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች
1) በስጦታ፣ በሽያጭ ወይም በሌላ መንገድ ተገልጋዮች ንብረት
ለማስተላለፍ ሲመጡ ካርታው ከጀርባው የተረጋገጠ መሆን አለበት፡፡ ካርታው ዲጂታል ከሆነ የጀርባ ማህተም አያስፈልገውም፡፡
2)በካርታው ከጀርባ ላይ ንብረቱ በውርስ የተገኘና የወራሾች ዝርዝር የተፃፈበት ከሆነ ተጨማሪ ማስረጃ ማየት ሳያስፈልግ መስተናገድ ይችላሉ፡፡ ሆኖም የንብረቱ መለያ ተጠቅሶ ወራሾች መሆናቸው በደብዳቤ ከተገለጸ አገልግሎቱን መስጠት ይቻላል፡፡
3)በውርስ ወይም በስጦታ የተገኘ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት የጋብቻ ማስረጃ አይጠየቅም፡፡
4)ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውጭ የተመዘገቡ የሚንቀሳቀሱም ሆነ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን የማስተላለፍ ወይም የማከራየት አገልግሎት ማግኘት የሚቻለው ንብረቶቹ በሚገኙበት ክልል/ከተማ አስተዳደር ነው፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሊስተናገዱ አይችሉም፡፡ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም የሚያስተናግደው በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚመለከተው መ/ቤት የተመዘገቡ ንብረቶችን ብቻ ይሆናል፡፡
5)ከጋብቻ በፊት በተቋሙ ቀርበው የንብረት ማግለል ውል ያደረጉ ወይም በፍ/ቤት ያጸደቁ ተጋቢዎች ንብረታቸውን ለማስተላለፍ ወይም ለማከራየት ሲመጡ የትዳር አጋራቸው ስምምነት አያስፈልግም፡፡ ሆኖም የንብረት ማግለሉ ስምምነት አሁን ጸንቶ ካለው ጋብቻ የትዳር አጋር ጋር የተደረገ ሊሆን ይገባል፡፡
6)አካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች ንብረት ለመግዛት የሚቻል ሲሆን ሁለቱም ወላጆች ሊገኙ ይገባል ፡፡ ካልሆነ አባት ወይም እናት ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡ ሆኖም ከእናትና አባት ውጪ የሆነ ሞግዚት አካላመጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ንብረት ለመግዛት በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡
7.)ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ ሞግዚቱ እናትና አባትም ቢሆኑም በፍ/ቤት የተሰጠ ተጨማሪ ስልጣን ሊቀርብ ይገባል፡፡
8.)ያላገባ ማስረጃ ላይ ቀደም ሲል ጋብቻ ስለመኖሩ የሚጠቁም የጊዜ መረጃ ሲኖር ንብረቱ በጋብቻ ወቅት የተፈራ ሊሆን ስለሚችል ንብረቱ የተፈራበትን ጊዜ የሚያመለክት ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ተጨማሪ ማስረጃ ሊቀርብ ይገባል፡፡
9.)ተነጻጻሪ ካርታ ማለት በአንድ የቦታ ስፋት ውስጥ የተለያዩ ቤቶችና ባለመብቶች ያሉበትና በተለያዩ ሰዎች ሊያዝ የሚችል ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ ይዞታ ላይ የባለቤትነት መብት ያለው ሰው የራሱን ካርታ በመያዝ ድርሻውን ጠቅሶ መሸጥ ይችላል፡፡
10)ካርታ ላይ የሚጠቀሰው ቀን ካርታው የተሰጠበትን ቀን እንጂ ንብረቱ የተፈራበትን ቀን በቀጥታ ላያመለክት ይችላል፡፡ ስለሆነም ንብረቱ የተፈራበትን ቀን ለማወቅ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የንብረቱ ባለቤት ተጨማሪ ማስረጃ እንዲያቀርብ መደረግ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከመሬት አስተዳደር ለገቢዎች እና ለካርታው ባለቤት የሚሰጡ ደብዳቤዎችን አያይዞ መስራት ይቻላል፡፡
11) የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለማስተላለፍ የፍቺ ውሳኔ ይዘው የሚቀርቡ ባለጉዳዮች ንብረቱ የጋራ ወይም የግል ስለመሆኑ በፍርድ ቤት የጸደቀ የንብረት ክፍፍል ስምምነት ወይም ውሳኔ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
12)ንብረት በስጦታ ለማስተላለፍ የተሠጠ የውክልና ሥልጣን ስጦታው ለማን እንደሚሰጥ እና ንብረቱ ምን አይነት እንደሆነ በውክልናው ላይ በግልፅ መቀመጥ አለበት፡፡ ነገር ግን በውክልና ስጦታ ለመቀበል ሲሆን ስጦታ ይቀበልልኝ የሚለው አገላለጽ በቂ ነው፡፡
13) የጋራ ንብረት በሽያጭ በሚተላለፍበት ጊዜ ገዢው ከንብረት ተጋሪው ውጪ የሆነ እንደሆነ የተጋሪው የቅድሚያ መግዛት መብት መጠበቁን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪውን ምስክር በማድረግ፣ የሚንቀሳቀስ ንብረት ሲሆን ተጋሪው ማረጋገጫ እንዲሰጥ ማድረግ ይቻላል፡፡
14) የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ከሆነ የታደሰ በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ወይም በኢንቨስትመንት አዋጁ መሠረት ቢያንስ አሥር ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በሥራ ላይ ማዋሉን የሚገልጽ ማስረጃ እና የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሊቀርብ ይገባል፡፡
የማይንቀሳቀስ ንብረት ገዢው የውጭ ሃገር ዜጋ ሌላ የመኖሪያ ቤት በስሙ የሌለ ስለመሆኑ የሚገልጽ ከሚመለከተው የንብረት መዝጋቢ አካል ማስረጃ ማቅረቡን እንዲሁም ከተቋሙ የመረጃ ቋት ማጣራት ያስፈልጋል፡፡ | 190 |
| 14 | ፀደቀ‼️
የታክስ ቅሬታ አጣሪው ተቀየረ፤ የታክስ ቅጣትም በግማሽ ተቀነሰ‼️
*ሰኔ 23/2018 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ላይ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጎ በዛሬው ዕለት አጽድቋል። ማሻሻያው በተለይም ለታክስ ከፋይ ተቋማት የፍትህ አድማሱን የሚያሰፋና የቅጣት ጫናን የሚቀንስ ነው።
በአዋጁ የተካተቱት ዋና ዋና ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፦
ከዚህ ቀደም በታክስ ባለሥልጣኑ በራሱ ይሰየም የነበረው የታክስ "አስማሚ" (Mediator)፣ ከአሁን በኋላ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰየም ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ይተካል፡፡ ይህም የታክስ ክርክሮች ፍትሃዊ እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲታዩ ያስችላል።
ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን በኋላ ላይ የዕዳ መጠን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሲያቀርቡ ይጠብቃቸው የነበረው 20 በመቶ ቅጣት፣ በግማሽ ተቀንሶ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የሚፈጽሙ ድርጅቶች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ድንጋጌ ተካቷል። በዚህም መሰረት ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት በስልጣን ላይ የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጆች ወይም የፋይናንስ ኃላፊዎች ለወንጀሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ህጉ በግልጽ አስቀምጧል።
ይህ ማሻሻያ የታክስ አስተዳደርን ይበልጥ ግልጽ፣ ፍትሃዊ እና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። | 189 |
| 15 | ታክስ ከፋይ ተቋማት የተወሰነባቸው የታክስ ክፍያ ላይ ቅሬታ ማሰማት ከፈለጉ ቅሬታቸውን በጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት ለሚቋቋመው ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን አቅርበው መፍትሄ ያገኛሉ ተባለ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባከናወነው መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ እና ማሻሻያ በማድመጥ በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።
ቋሚ ኮሚቴው በረቂቅ አዋጁ ላይ ካደረጋቸው ወሳኝ ማሻሻያዎች መካከል የታክስ አለመግባባቶችን የሚያስማማው "አስማሚ" (Mediator) አሰያየምን የተመለከተው ይገኝበታል፡፡
በመጀመሪያው ረቂቅ ላይ አስማሚው በታክስ ባለሥልጣኑ እንዲሰየም ተደንግጎ የነበረ ቢሆንም፣ ቋሚ ኮሚቴው "ገለልተኝነትን ለማረጋገጥ" ሲባል አስማሚው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እንዲሰየም በሚል ማሻሻያ አድርጎበታል፡፡
በማሻሻያው መሰረት ታክስ ከፋይ ተቋማት የተወሰነባቸው የታክስ ክፍያ ላይ ቅሬታ ማሰማት ከፈለጉ ቅሬታቸውን በጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቤት ለሚቋቋመው ገለልተኛ የባለሙያዎች(አስማሚ) ቡድን አቅርበው መፍትሄ የሚያገኙ ይሆናል።
ሌላኛው ማሻሻያ የቀረበው አዲስ ማስረጃን ከማቅረብ ጋር ተያይዞ የሚጣልን ቅጣት የሚመለከት ነው።
ታክስ ከፋዮች በታክስ አወሳሰን ወቅት ያላቀረቡትንና በኋላ ላይ በታክስ ዕዳ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ አዲስ ማስረጃ ሲያቀርቡ የሚጣልባቸው ቅጣት እንዲሻሻል ተደርጓል።
በዚህም መሠረት ታክስ ከፋዩ ሊከፈል ከሚገባው የታክስ ዕዳ ላይ 10 በመቶ (ቀድሞ 20 በመቶ የነበረው) ቅጣት እንዲከፍል በማሻሻያው ተደንግጓል።
በተጨማሪም ቋሚ ኮሚቴው በድርጅቶች የሚፈጸሙ የታክስ ወንጀሎችን ተጠያቂነት በተመለከተ ማብራሪያ የሚሰጥ ማሻሻያ አድርጓል።
የታክስ ሕግን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመው ድርጅት ወይም በግለሰብ ባለቤትነት ሥር ያለ የንግድ ድርጅት በሚሆንበት ጊዜ፣ ወንጀሉ በተፈጸመበት ወቅት የነበሩ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም የፋይናንስ ኃላፊ ተጠያቂ የሚሆኑበት አግባብ ተመቻችቷል።
ይህ ማሻሻያ የተደረገው የታክስ ህግን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመ የየትኛውም ድርጅት ስራ አስኪያጅ ተጠያቂ ማድረግ ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት እንደሆነ ተመላክቷል። | 231 |
| 16 | Matn yo'q... | 235 |
| 17 | የታክስ አስተዳደር አዋጅ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 23፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ፣ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
👉 አዲሱ አዋጅ ደረሰኝ ሊሰጥ ሲገባው ያልሰጠ ማንኛውም ታክስ ከፋይ በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር መቀጫ የሚጥል ነው። | 269 |
| 18 | የፅናትና የስኬት ማማ፡ ከቀን ስራ ወደ ህግ ምሩቅነት!
ትናንት ኑሮን ለማሸነፍና ለነገው ማንነቱ መሰረት ለመጣል በከባድ የቀን ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው ይሄው ጠንካራ ወጣት፣ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (Mizan-Tepi University) በህግ ትምህርት ዘርፍ በደማቅ ሁኔታ ተመርቆ የድካሙን ፍሬ አጭዷል።
ይህ ለነገ እቅዳቸውና ህልማቸው ሌሊት ከቀን ለሚደክሙ በርካታ ወጣቶች ትልቅ ተስፋንና መነቃቃትን የሚፈጥር እውነተኛ የስኬት ማማ ነው።
ማንኛውም ሰው አሁን ያለበት አስቸጋሪ ሁኔታ የህይወቱን የመጨረሻ ምዕራፍ ሊወስን እንደማይችል ይህ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመዘገበው ደማቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በትጋትና በቆራጥነት ከተሰራ ትናንት በከባድ የጉልበት ስራ ውስጥ የነበረው ማንነት፣ ዛሬ የፍትህና የህግ ባለሙያ ሆኖ ለመቆም እንደሚያስችል በሚገባ ያሳየናል።
እኛም ለዚህ ብርቱ ወጣት ለደረሰበት ትልቅ የስኬት ምዕራፍ ያለንን ጥልቅ አድናቆት እየገለጽን፣ ለቀጣዩ የሙያ ህይወቱ መልካም ምኞታችንን እንመኛለን።
ህልም ኖሯችሁ ነገር ግን መንገዱ አልጋ በአልጋ ላልሆነላችሁ ወጣቶች ሁሉ ይህ አስደናቂ ጉዞ ትልቅ ብርታትና መማሪያ እንደሚሆን እናምናለን። | 268 |
| 19 | 'የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ረቂቅ' | 252 |
| 20 | የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞችን አዋጅ ለመደንገግ
የወጣ አዋጅ ቁጥር 309/2018 | 288 |
