የቀጠናው ተመልካች
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
4 317
Obunachilar
-324 soatlar
-127 kun
-7530 kun
Postlar arxiv
4 317
🇺🇸⚔️🇮🇷 ትራምፕ፡ "በኢራን ላይ የሚደረጉ ወታደራዊ ዘመቻዎች ከ2 እስከ 3 ሳምንታት ሊቆዩ ይችላሉ።
የተኩስ አቁሙ በእርግጥ አብቅቷል ማለት አልችልም። በድርድር ወይም በወታደራዊ መፍትሄ እናሸንፋለን።"
ከሰዓታት በፊት፣ ኢራን፣ ከስምምነቱ ልትወጣ እንደሆነ አስጠንቅቃለች።
4 317
🇮🇷⚡️ትንንሽ ነጫጭ ኮፊያ ያደረጉት ድንቢጦች የአሜሪካና የእስራኤል አጋር የሆኑት ሱኒ አረቦች፣ አናታቸው ላይ የቆመው ግብዳው፣ ሺዓ ኢራን ናቸው።
4 317
🇾🇪❌🇸🇦 - የየመኑ አንሳር አላህ (ሁቲ)፣ ዋና ዋና የሳውዲ አረቢያ አየር ማረፊያዎችን እና የኃይል መሠረተ ልማቶችን ኢላማ እንደሚያደርግ ተናግሮ፣ የቦታዎችን ምስሎች ከነ coordination መገኛቸው ጋር በመልቀቅ "ምላሹ እየመጣ ነው" ሲል ተናግሯል።
ከሰዓታት በፊት በደቡባዊ ሳዑዲ፣ በአል አብሃ አየር ማረፊያ ላይ በተሰነዘረ የሚሳዬል ጥቃት፣ ጉዳት ሳይደርስ እንዳልቀረ እየወጡ ያሉ ምስሎች ያሳያሉ።
4 317
🇷🇺 የተኳሿን ማነስና ከተተከለው ጠብመንጃ በታች ማጠርን ትኩር ብዬ ሳየው፣ አፍሪካዊ ትሆን እንዴ አልኩኝ? ለሩሲያ የምትዋጋ ቅጥረኛ አፍሪካዊ። ኮማንደሩንም እኮ በጣጥሳው ነበር።
4 317
🇷🇺 የተኳሿን ማነስና ከመሳሪያው በታች ማጠር ትኩር ብዬ ሳየው አፍሪካዊ ትሆን እንዴ አልኩኝ? ለሩሲያ የምትዋጋ ቅጥረኛ አፍሪካዊ። ኮማንደሩንም እኮ በጣጥሳው ነበር።
4 317
💥🇸🇦የሳዑዲ አረቢያ መከላከያ ኃይሎች፡ "በሁቲ ሽብርተኞች ወደ ደቡባዊ የሳዑዲ ግዛት የተተኮሱትን ባለስቲክ ሚሳኤሎችን አክሽፈን ጥለናል። በአሁኑ ሰዓት ሁሉም ነገር በቁጥጥር ሥር ነው።
4 317
🇾🇪⚡️🇸🇦 — በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው አብሃ አየር ማረፊያ፣ ከየመን እየተተኮሱ ባሉ ሚሳዬሎች በአሁኑ ሰዓት ጥቃት እየደረሰበት ነው። በአካባቢው ሳይረኖች እየጮሁ ናቸው።
4 317
🇷🇺⚡️የሩሲያ ጦር፣ Mi-24 ሄሊኮፕተር ላይ የሚገጠምን ጠብመንጃ በመኪና ላይ ለድሮን መምቻ ገጥሞ በመሞከር ላይ ሳለ፣ የጠመንጃው ኃይል ተኳሹን አሽቀንጥሮ ሲጥለው የሚያሳይ ምስል ትናንት ወጥቷል።
4 317
🇺🇸 🇴🇲 ❌ 🇮🇷 ⚡️ - ኦማን ኢራን የሆርሙዝ ባሕርን በተመለከተ የቀረበውን ሐሳብ ውድቅ እንዳደረገች ለዩናይትድ ስቴትስ አቃጠረች።
🔴 በምላሹም ዋሽንግተን በኢራን ላይ ዳግም የባሕር ኃይል እገዳውን እና ወታደራዊ ዘመቻውን ለመቀጠል ወስናለች።
4 317
🇮🇷 ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም በፈንጅ ማጠር ጀምራለች ስትል ኤሜሬት ለአሜሪካ አቃጠረች።
የኤሚሬትስ ምንጮች ኢራን በሆርሙዝ ባሕር ውስጥ ፈንጂዎችን መቅበሯን እንደቀጠለች ይናገራሉ፣ በቅርቡ የአሜሪካ ጥቃቶችም ይህንን ሂደት ለማደናቀፍ ያለመ ነው ተብሏል።
በባሕር ወሽመጡ ውስጥ ያለው ትራፊክ ማሽቆልቆሉን የቀጠለ ሲሆን፣ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 21 መርከቦች ብቻ እንዳለፉ ተነግሯል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቴህራን ካሁን በኋላ አሜሪካን እንደምታንጸባርቅ እና ዋሽንግተን ሁሉንም ስምምነቶች ሙሉ በሙሉ ለማክበር እስክትመለስ ድረስ በስምምነቱ ውስጥ ያሉትን ግዴታዎቿን መወጣቷን እንደምታቆም ገልጿል።
ኢራን የተፈረመውን ስምምነት ጥሳ እንደማታውቅ በመናገር፣ ሁሉንም ስምምነቶች በመጣስና ባለማክበር ዋሽንግተን ሙሉ ሃላፊነቱን እንደምትወስድ ተናግራለች።
4 317
— 🇺🇸/🇮🇷 የአሜሪካ ጦር ኃይል፣ የባሕር ላይ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በመጠቀም የኢራንን የመርከብ ማቆሚያዎች በባሕር ዳርቻዎቻቸው ሲመታ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ለቋል።
*-*-*
እነዚህን የባሕር ላይ ድሮኖችን አሜሪካ ያመጣችው ከዩክሬን መሆን አለበት። በጦር ሜዳ እነዚህን ድሮኖች መጠቀም የጀመሩት ዩክሬኖች ናቸው።
ጀልባ ሳይዝ ናት፣ ስሪቷ ሙሉ ተቀጣጣይ ፈንጂ ናት። ሶፍትዌሮች ኮምፒውተሮች ናቪጌሽን ሲስተሞች አሏት። በባሕር ላይ ሄዳ መርከቦችንና በባሕር ላይ ያሉ ወታደራዊ ዒላማዎችን እና የባሕር ላይ ድልድዮችን (Crimiea Bridge) ምሰሷቸውን በመምታት ከባድ ጥፋት ታደርሳለች። የሩሲያ አየር ኃይል በብዙ የተጎዳበት ድሮን ናት።
ሩሲያ ከነዚህ የባሕር ድሮኖች ንብረቶቿን ለመጠበቅ በዙሪያቸው የብረት ሰንሰለት ታጥራለች። ለምሳሌ በድልድይ ምሰሶዎቿ ዙሪያ የብረት ሰንሰለቶችን አርቃ በመወጠር ታጥራለች። ከFPV ድሮኖች ራሳቸውን ለመከላከል የአሳ ማጥመጃ እንደሚወጥሩት ማለት ነው።
ምናልባት ከአሁን በኋላ ኢራን በሰንሰለት ማጠር ሊኖርባት ይችላል።
4 317
— 🇺🇸/🇮🇷 ፕሬዝዳንት ትራምፕ፡ ‘በኢራን ያለው ሁሉም ነገር ለአሜሪካ የተገባ ነው። ነዳጁ፣ ወርቁ፣ ሰብሉ፣ ጋዙ፣ ሁሉንም እንወስደዋለን።
4 317
+2
ከጥቂት ሰዓታት በፊት የሳዑዲ አየር ኃይል በየመን የሰነዓ አየር ማረፊያን በተከታታይ ጥቃቶች መደብደቡ ታወቀ።
የሳዑዲ ጥቃት በአየር ማረፊያው ሊያርፍ የነበረውን የኢራንን የመንገደኞች አይሮፕላን እንዳያርፍ ለማስገደድ ነው ተብሏል።
በየመን አየር ክልል፣ ከዚህ በፊት ሳዑዲና አጋሮቿ የበረራ ማዕቀብ ጥለው የነበረ መሆኑና በዚህ ወር መግቢያ ኢራን ማዕቀቡን በመጣስ አይሮፕላን በመደበኛ በረራዎች ማሳረፍ መጀመርዋ ትልቅ መነጋገሪያ ነበር።
በወቅቱ ኢራን፣ አይሮፕላኖቿን በየመን አየር መከልከል የሚችል ማንም የባዕድ ሀገር መብት እንደሌለውና መብቱ የየመን ሕዝብ እና መንግሥት ብቻ መሆኑን አሳውቃ፣ አይሮፕላኖቿ እንዳያርፉ በሚሰሩ ሀገሮች ላይ አሳማሚ ቅጣት እንደምትሰነዝር አስጠንቅቃ ነበር።
የዛሬው የሳዑዲ የሰነዓ አየር ማረፊያ ድብደባ ከባድ የነበረ ሲሆን፣ ማረፊያ መንደርደሪያውን ሙሉ በሙሉ ያፈረሰ መሆኑ ተነግሯል።
በአሁኑ ሰዓት የኢራን አይሮፕላን በምዕራብ የመን አል-ሁደይዳ አየር ማረፊያ ለማረፍ ተገዷል።
የየመን ሁቲ ጦር ኃይሎች፣ 'በአይሁዶች አጋር በሆነችው ሳዑዲ ላይ አሳማሚ አፀፋ እየመጣ ነው' በማለት መግለጫ አውጥተዋል።
4 317
🇬🇧🇮🇱 - ዩናይትድ ኪንግደም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የአይሁዶችን ደህንነት ለመጠበቅ እና የማምለኪያ ቦታዎቻቸውን በተጠናከረ ጥበቃ ለመጠበቅ፣ $350 ሚሊዮን ዶላር እንደመደበች ተናገረች።
ለዚሁ ሲባልም 1000 አዳዲስ ፖሊሶች ይቀጠራሉ።
4 317
🇬🇧🇮🇷 - ዩናይትድ ኪንግደም IRGCን 'አሸባሪ ድርጅት' በማለት በይፋ ሰይማለች።
አባልነት፣ በስብሰባዎች ላይ መገኘት ወይም ምልክቶቹን በይፋ ማሳየት፣ አሁን በብሪታንያ በሽብርተኝነት የሚያስቀጣ ወንጀል ነው።
4 317
+2
🇺🇸⚡️FBI፣ የሴኔተር ሊኒዝ ግርሃምን አሟሟት እየመረመረ ነው።
*-*-*
ሰውዬውን ሲጥ አርገውት ይሆን ሩሲያዎች በዩክሬን? ኢራኖችስ፣ ይሆኑ እንዴ እንደዛቱበት? FBI መመርመር የፈለገው ምናልባት በሆነ መንገድ ተገድሏል በሚል ፍራቻ ነው።
'ይመርመርልን፣ ወይ በሩሲያ፣ ወይ በኢራን ተገድሎ ነው' እያለች በአሁኑ ሰዓት የምታለቅሰውን፣ የፕሬዝዳንቱን ልዩ አማካሪ Laura Loomer ን የዛሬ ትዊተር ፖስቶች ተከትሎ እንደሆነ FBI እየመረመረ ያለው ጥርጥር የለኝም።
Laura Loomer ራሷ ኢራኖች ሊገድሏት እንደሚፈልጉ ከሊንዚ፣ ከትራምፕ እና ከታቂ ሰዎች ጎን ለጎን የተናገሯት ናት።
ትናንት በፖስቴ ኢራኖች ሊገድሏቸው እንደሚፈልጉ አንስቼ ነበር። በዚህ ፖስት በላይ ያለውን ርዕስ እየነካካችሁ ብታነቡት መልካም ነው።
4 317
🇺🇸⚡️ - ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙት ሁሉም የአሜሪካ ባንዲራዎች ለሊንዚ ግራሃም ክብር ለሚቀጥሉት ስድስት ቀናት በግማሽ ምሰሶ እንዲውለበለቡ አዘዙ።
ለሀገራችን እና ለሚወደው የደቡብ ካሮላይና ግዛት ብዙ ያስመዘገበው ውድ ጓደኛዬ እና በእውነት ታላቅ ሰው ለሴናተር ሊንዚ ግራሃም አስደናቂ ህይወት እና ስኬቶች ክብር በመላው ዩናይትድ ስቴትስ ያሉ ሁሉም የአሜሪካ ባንዲራዎች እስከ ቅዳሜ ምሽት ከቀኑ 6 ሰአት ላይ ወደ ግማሽ ምሰሶ እንዲወርዱ አዝዣለሁ።
4 317
🇺🇸 / 🇮🇷 ፕሬዝዳንት ትራምፕ - '
የሆርሙዝ ወሽመጥ ክፍት ነው፣ እሺ? ኢራናውያን ክፉና ጨካኝ ሰዎች ናቸው። ስለ ሆርሙዝ ምንም ተጨማሪ ጥያቄዎችን አልፈልግም፣ ሆርሙዝ እንዲ፣ ሆርሙዝ እንዲያ፣ እኛ እዚህ የመጣነው ሊንዚ ግራሃምን ለመዘከር ነው፣ እሱ ድንቅ ሰው ነበር፣ እኔ ሐዘን ላይ ነኝ፣ ብትችሉ ድረሱኝ፣ ያለበለዚያ ዝም በሉ።
