uz
Feedback
Leikov's Thought

Leikov's Thought

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
192
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+27 kunlar
-430 kunlar
Postlar arxiv
Every decision for something is a decision against something else.

የምናውቀው ጠብታ የማናውቀው ውቅያኖስ ነው።

ከአሳማ ጋር አትታገል ፥ ሁለታችሁም ትቆሽሻላችሁ ፤ ግን እርሱ መቆሸሹን ይወደዋል።

ወጥነት ቁልፍ ነው በማንኛውም ነገር ላይ ጎበዝ ለመሆን፣ ነገሩን በየቀኑና ለረጅም ጊዜ ማድረግ አለብህ። የተሻለ ሰዓሊ ለመሆን → በየቀኑ መሳል አለብህ። የተሻለ ጸሐፊ ለመሆን → በየቀኑ መጻፍ አለብህ። የተሻለ ተናጋሪ ለመሆን → በየቀኑ መናገር አለብህ። ብዙ ሰዎች በፍጹም አይጀምሩም። አንዳንዶቹ ይጀምራሉ፣ ነገር ግን ነገሮች እየተወሳሰቡ ሲሄዱ ይተዋሉ። ጥቂቶች ብቻ ወጥነት ያሳያሉ፤ በየቀኑ ያደርጉታል፣ ነገሩ ምንም ያህል ቢከብድም አይተዉትም።

ሳስበው የአፍሪካውያን ችግር የብቃት ብቻ አይመስለኝም። እንደኔ እይታ የበታችነት ስሜት የተጠናወታቸው ይመስለኛል። የባርነት ስሜት የለቀቃቸው አይመስለኝም። ነጭ የበላይ እንደሆነ ልቦናቸው ላይ ታትሞ የቀረ መሰለኝ። አውሮፓን ማሸነፍ የሚገባ መስሎ አልታያቸውም። እናም እስካሁን ድረስ ከአውሮፓ ቡድኖች ጋር አቻ ሲወጡ እንኳን እንዳሸነፉ አይነት እየተወደሱ ነበር። አቻ ጥሩ ቢሆንም ግን እንደ ድል እየተቆጠረ ነው። ይህ በራሱ ትክክል አይደለም። ማሸነፍ ነው እንደ ድል ሊታይ የሚገባው! ኮትዲቯር ኳስን የመቆጣጠር ብቃታቸው የሚገርም ነበር። አሪፍ ይወስዱ ይወስዱና ጎል አከባቢ ሲደርሱ ማግባት አይችሉም። አግብቶ ማሸነፍ እንደሚችሉ ያመኑ አይመስለኝም። ጎል ማግባት የሚመጥናቸው እንዳልሆነ ነው መሰለኝ የሚያስቡት። ኮንጎም ገራሚ ነበረች። በእውነቱ እንግሊዝን የማሸነፍ ብቃት ነበራት። ግን አላደረገችውም። አውሮፓን ማሸነፍ ነውር ነዋ። ይህንን ጽንሰ ሀሳቤን የበለጠ እርግጠኛ እንድሆንበት ያደረገኝ የሴኔጋሉ ጨዋታ ነው። ቤልጂየም አሪፍ አይደለችም። በአንጻሩ ሴኔጋል ፈጣን ስትሆን ጎልም የማስገባት ብቃት አላት። ያንንም አደረገችው። ግን አውሮፓን ማሸነፍ ነውር ስለመሰላቸው ተሸነፉ። እስኪ ወደ ህይወት እናምጣው። እኛ ራሳችን ነጭ ስናይ የምንሆነውን ጉድ ስነ ልቦናችን ያውቀዋል። ነጭ ትክክል ፣ አዋቂ ፣ የበላይ ፣ የተሻለ ፣ ገንዘብ ያለው ምናምን አድርገን ነው የምናስበው? እስኪ ማነው ከእናንተ ውስጥ በዕውቀት ከነጭ ጋር ተወዳድሮ ማሸነፍ እንደሚችል የሚያውቅ? ጉዳዩ የብቃት ብቻ ሳይሆን የስነልቦናም ነው። በአንጻሩ ተመልከቱ ነጭ አፍሪካውያን ያሉበትን ሁኔታ። እነ ሞሮኮ ፣ እነ ግብጽ ፣ አልጄሪያ - እያሸነፉም ጭምር ነው። የጥቁር አፍሪካውያንን ፍርሃት ለመገርሰስ አንድ ምሳሌ ሆኖ ጥሶ የሚወጣ አካል ያስፈልጋል። ልክ ኢትዮጵያ ለነጮች ባርያ ሆኖ መገዛት ትክክል እንዳልሆነና ነጮችን ማሸነፍ እንደሚቻል አድዋ ላይ ምሳሌ ሆና ለሙሉ አፍሪካ ነፃ መውጣት ምክንያት እንደሆነችው ማለት ነው። ኢትዮጵያ በኳሱ ብቃት ቢኖራት ይህንን ቀንበር ትሰብረዋለች ብዬ አምናለሁ። በነገራችን ላይ ጥቁር አፍሪካውያን የማሸነፍ ስነልቦናን ከያዙ ኳስ የአፍሪካ ነው የምትሆነው። ይነግሱበታል።

ልጅ እያለሁ እኛ ቤት ቦቢ የሚባል ውሻ ነበር። እወደው ነበር። በጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ቦቢ ፣ ቦቢ ፣ ቦቢ ብዬ ስጮህ ቦቢ ካለበት እየሮጠ ይመጣል። ውጪ ነው የሚያድረው። አንድ ቀን ሰዎች ሰብሰብ ብለው መጥተው ውሻ አውጡ አሉን። በሁኔታው ግራ ተጋብቼ ነበር። ለምንድነው ብዬ አያቴን ጠየቅኋት። ሊገ*ድ*ሉት ነው አለችኝ። ለምን የለም አትያቸውም? ሽንት ቤት ለምን አትደብቂውም? ብደብቀውም ያገኙታል አለችኝ። ቦቢን ገመድ በአንገቱ ላይ አስረው አጥር ላይ ሰቀሉት። እንባ ተናነቀኝ። ሰው ፊት ማልቀስ እፈራ ስለነበር እንደምንም እንባዬ እንዳይፈስ ታገልኩ። ቦቢ ቶሎ እንዲ*ሞት በተሰቀለበት በዱላ ሆዱን መደብደብ ጀመሩ። ቆሜ ማየት አቅቶኝ ትቼ ሄድኩ። አትግ*ደሉት እንዳልላቸው ህፃን ነኝ ፥ እነርሱ ትላልቅ ሰዎች ናቸው። ደግሞ ቦቢን ብቻ ሳይሆን ቤት ለቤት እየዞሩ እየ* ገ* ደ *ሉ ነበር። ልክ እንደ ዘመቻ ነው መሰለኝ። የምወደውን ውሻ ማዳን ያልቻልኩ አቅመቢስ ሰው ነበርኩ። ገ*ዳ*ዮቹ ግን ሲገ*ድ*ሉት በደስታ ነበር። ገመድ ላይ የታሰረ ኳስ እየመታህ እንደምትዝናናው አይነት አለ አይደል ፤ ልክ እንድዛ። እንስሳን አሰቃይቶ መግደል ሰብአዊነት አይደለም። ተፈጥሮአዊ ነገር አለመሆኑን ከእኔ ማየት ይቻላል። እኔ ህፃን ነበርኩ። ውሻን መ*ግ*ደል ስህተት ነው ብሎ ማንም አላስተማረኝም። ማንም መክሮኝም አያውቅም። ግን ቦቢን እንደዛ ሲያደርጉት ውስጤ አልተቀበለውም። ከዚህም ትክክል ያልሆነ ነገር እንደተሰራ መረዳት እችላለሁ። መንገድ ላይ ውሻ ሲያዩ ድንጋይ ያነሱና የሚማቱ ሰዎች አሉ። የእነዚህ ሰዎች አስተሳሰብ ግርም ይለኛል። ደግሞ ነገሩን ሲያደርጉት ደስ እያላቸው ነው። አንድ ምስኪን እንስሳን መማታት ምኑ ነው ደስ የሚያሰኘው?? ሰሞኑን የተለቀቀውን ቪዲዮ ሳይ ቀጥታ ወደ አዕምሮዬ የመጣው ቦቢ ነው። ቪዲዮው ይረብሻል። ግን እኮ ምናልባት ያንን ያደረጉበት ምክንያት ሊኖራቸው ይችላል። ምናልባት ስለ የእብድ ውሻ በሽታ ( rabies ) ሰምታችሁ ሊሆን ይችላል። አንድ በሬቢስ የተጠቃ ውሻ ቁጡ ነው የሚሆነው። ያገኘውን ሁሉ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ በሽታው ይተላለፋል። ውሻንም ሰውንም ሊናከስ ይችላል። በበሽታው በተጠቃ ውሻ የሚነከሰው ሰው ደግሞ ቶሎ ህክምና ካላገኘ በህመሙ ተሰቃይቶ ነው የሚሞተው። በሽታው ውሻውን እንደሚያደርገው ነው ሰውየውንም የሚያደርገው። ይህንን ችግር ለመከላከል ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ ግንዛቤውም ምቹ ሁኔታም የለም። አንድ የታመመን እንስሳ ስራዬ ብሎ የሚያሳክም የለም ፥ ህክምናውም የለም። እንዳደጉት ሀገራት አይደለንም። ደግሞ ብዙ ውሻዎችን አይታችሁ ከሆነ ባለቤት የላቸውም። እንዲያው ዝምብለው በከተማው ላይ እየተዋለዱ ይባዛሉ። አስቡት እነዚህ ውሻዎች በበሽታው ቢጠቁ ። ለአከባቢው ማህበረሰብ ስጋት ነው የሚሆኑት። ታዲያ በዚህ ሁኔታ መፍትሔው ምንድነው? የእንስሳት የህክምና ጣቢያ በበቂ ሁኔታ የለም። ማንም ግድ ብሎት እንዳያሳክም ግንዛቤ አልተፈጠረለትም። ስለዚህ ቀላሉ መፍትሔ ውሾችን እያደኑ መጨረስ ነው ቪዲዮው ላይ እንዳያችሁት። ውሾች ለምን ተ*ገ*ደሉ የሚል ሰብአዊነት ከተሰማን የእንስሳትን የህክምና ጣቢያ እንገንባ። በየመንገዱ ተበትነው ያሉትን ባለቤት አልባ ውሾችን ይዞ የሚንከባከብ ተቋም እንገንባ። ኃላፊነት ተሰምቶን ወደ ቤታችን ወስደን በእንክብካቤ እናሳድጋቸው። ይህንን ባላደረግንበት እንዴት ውሾች ይገ*ደ*ላ*ሉ ብለን ተቆርቋሪ መምሰል ከማስመሰል ያለፈ ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም። በነገራችን ላይ ይሄ በቪዲዮ ወጣ እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን የኖርነው በዚህ አይነት መንገድ ነው።

photo content

አንዳንድ ጨዋታዎች ከፍጻሜ በፊት ያሉ ፍጻሜዎች ናቸው። አስታውሳለሁ 2019 ላይ champions league ግማሽ ፍጻሜ ላይ Liverpool Anfield ላይ Barcelonaን 4-0 በሆነ come back ያሸነፈበት ጨዋታ ለእኔ እጅግ የሚገርም ነበር። የተደነቅሁበት ጨዋታ ነው። እስከ መጨረሻዋ ሰከንድ ተስፋ መቁረጥ እንደሌለብኝ የተማርኩበት ነው። ጨዋታው የፍጻሜ አይደለም ግን ፍጻሜን ያስንቃል። ምንም እንኳን ባርሴሎናን ስደግፍ የነበረ ቢሆንም ( በ Messi ) ምክንያት Liverpool ባደረገው ነገር መደነቄ እና ማጨብጨቤ አልቀረም። የምደግፈው በመሸነፍ እና በማሸነፍ ላይ ብቻ ሳይሆን የጨዋታ ማራኪነት ላይም ትኩረት አደርጋለሁ። እናም ጨዋታውን ወድጄው ነበር። ያለፈውን የዓለም ዋንጫ ጨዋታውን በልብ መንጠልጠልና በግርምት ነበር ያየሁት። France vs Argentina France እንዳታሸንፍ ብፈልግም Mbappe 3 ጎል በማስገባት አስገርሞኛል። በአድናቆት ልቤ ሲሞላ ነበር። ፍጻሜውን የሚመጥን ጨዋታ እያልኩ በደስታ ስመለከት ነበር። ዛሬም France ከ Norway የምታደርገው ጨዋታ አሪፍ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ - እስካሁን ካየናቸው። እንደዛ ያልኩበት ምክንያቴ Mbappe እና Haland ናቸው። የሁለቱም ጎል የማስቆጠር አካሄድ የሚገርም ነው። አስቡት እስከዛሬ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከፍተኛ ጎል ያለው 16 ነበር ሁሉም ተደምሮ ማለት ነው። ግን እነዚህ ሁለቱ ተጫዋቾች በሁለት ጨዋታ ብቻ 4 , 4 ጎል አላቸው። ነገሩን የበለጠ የሚያጦዘው ደግሞ አሁንም ብዙ የማስገባት ብቃት አላቸው። ማታ 4 ሰዓት የሚፈጠሩ ነገሮችን እናያለን።

photo content

ልጅ እያለሁ እኛ ቤት ቦቢ የሚባል ውሻ ነበር። እወደው ነበር። በጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ቦቢ ፣ ቦቢ ፣ ቦቢ ብዬ ስጮህ ቦቢ ካለበት እየሮጠ ይመጣል። ውጪ ነው የሚያድረው። አንድ ቀን ሰዎች ሰብሰብ ብለው መጥተው ውሻ አውጡ አሉን። በሁኔታው ግራ ተጋብቼ ነበር። ለምንድነው ብዬ አያቴን ጠየቅኋት። ሊገ*ድ*ሉት ነው አለችኝ። ለምን የለም አትያቸውም? ሽንት ቤት ለምን አትደብቂውም? ብደብቀውም ያገኙታል አለችኝ። ቦቢን ገመድ በአንገቱ ላይ አስረው አጥር ላይ ሰቀሉት። እንባ ተናነቀኝ። ሰው ፊት ማልቀስ እፈራ ስለነበር እንደምንም እንባዬ እንዳይፈስ ታገልኩ። ቦቢ ቶሎ እንዲ*ሞት በተሰቀለበት በዱላ ሆዱን መደብደብ ጀመሩ። ቆሜ ማየት አቅቶኝ ትቼ ሄድኩ። አትግ*ደሉት እንዳልላቸው ህፃን ነኝ ፥ እነርሱ ትላልቅ ሰዎች ናቸው። ደግሞ ቦቢን ብቻ ሳይሆን ቤት ለቤት እየዞሩ እየ* ገ* ደ *ሉ ነበር። ልክ እንደ ዘመቻ ነው መሰለኝ። የምወደውን ውሻ ማዳን ያልቻልኩ አቅመቢስ ሰው ነበርኩ። ገ*ዳ*ዮቹ ግን ሲገ*ድ*ሉት በደስታ ነበር። ገመድ ላይ የታሰረ ኳስ እየመታህ እንደምትዝናናው አይነት አለ አይደል ፤ ልክ እንድዛ። እንስሳን አሰቃይቶ መግደል ሰብአዊነት አይደለም። ተፈጥሮአዊ ነገር አለመሆኑን ከእኔ ማየት ይቻላል። እኔ ህፃን ነበርኩ። ውሻን መ*ግ*ደል ስህተት ነው ብሎ ማንም አላስተማረኝም። ማንም መክሮኝም አያውቅም። ግን ቦቢን እንደዛ ሲያደርጉት ውስጤ አልተቀበለውም። ከዚህም ትክክል ያልሆነ ነገር እንደተሰራ መረዳት እችላለሁ። መንገድ ላይ ውሻ ሲያዩ ድንጋይ ያነሱና የሚማቱ ሰዎች አሉ። የእነዚህ ሰዎች አስተሳሰብ ግርም ይለኛል። ደግሞ ነገሩን ሲያደርጉት ደስ እያላቸው ነው። አንድ ምስኪን እንስሳን መማታት ምኑ ነው ደስ የሚያሰኘው?? ሰሞኑን የተለቀቀውን ቪዲዮ ሳይ ቀጥታ ወደ አዕምሮዬ የመጣው ቦቢ ነው። ቪዲዮው ይረብሻል። ግን እኮ ምናልባት ያንን ያደረጉበት ምክንያት ሊኖራቸው ይችላል። ምናልባት ስለ የእብድ ውሻ በሽታ ( rabies ) ሰምታችሁ ሊሆን ይችላል። አንድ በሬቢስ የተጠቃ ውሻ ቁጡ ነው የሚሆነው። ያገኘውን ሁሉ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ በሽታው ይተላለፋል። ውሻንም ሰውንም ሊናከስ ይችላል። በበሽታው በተጠቃ ውሻ የሚነከሰው ሰው ደግሞ ቶሎ ህክምና ካላገኘ በህመሙ ተሰቃይቶ ነው የሚሞተው። በሽታው ውሻውን እንደሚያደርገው ነው ሰውየውንም የሚያደርገው። ይህንን ችግር ለመከላከል ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ ግንዛቤውም ምቹ ሁኔታም የለም። አንድ የታመመን እንስሳ ስራዬ ብሎ የሚያሳክም የለም ፥ ህክምናውም የለም። እንዳደጉት ሀገራት አይደለንም። ደግሞ ብዙ ውሻዎችን አይታችሁ ከሆነ ባለቤት የላቸውም። እንዲያው ዝምብለው በከተማው ላይ እየተዋለዱ ይባዛሉ። አስቡት እነዚህ ውሻዎች በበሽታው ቢጠቁ ። ለአከባቢው ማህበረሰብ ስጋት ነው የሚሆኑት። ታዲያ በዚህ ሁኔታ መፍትሔው ምንድነው? የእንስሳት የህክምና ጣቢያ በበቂ ሁኔታ የለም። ማንም ግድ ብሎት እንዳያሳክም ግንዛቤ አልተፈጠረለትም። ስለዚህ ቀላሉ መፍትሔ ውሾችን እያደኑ መጨረስ ነው ቪዲዮው ላይ እንዳያችሁት። ውሾች ለምን ተ*ገ*ደሉ የሚል ሰብአዊነት ከተሰማን የእንስሳትን የህክምና ጣቢያ እንገንባ። በየመንገዱ ተበትነው ያሉትን ባለቤት አልባ ውሾችን ይዞ የሚንከባከብ ተቋም እንገንባ። ኃላፊነት ተሰምቶን ወደ ቤታችን ወስደን በእንክብካቤ እናሳድጋቸው። ይህንን ባላደረግንበት እንዴት ውሾች ይገ*ደ*ላ*ሉ ብለን ተቆርቋሪ መምሰል ከማስመሰል ያለፈ ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም። በነገራችን ላይ ይሄ በቪዲዮ ወጣ እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን የኖርነው በዚህ አይነት መንገድ ነው።

አንዳንድ ጨዋታዎች ከፍጻሜ በፊት ያሉ ፍጻሜዎች ናቸው። አስታውሳለሁ 2019 ላይ champions league ግማሽ ፍጻሜ ላይ Liverpool Anfield ላይ Barcelonaን 4-0 በሆነ come back ያሸነፈበት ጨዋታ ለእኔ እጅግ የሚገርም ነበር። የተደነቅሁበት ጨዋታ ነው። እስከ መጨረሻዋ ሰከንድ ተስፋ መቁረጥ እንደሌለብኝ የተማርኩበት ነው። ጨዋታው የፍጻሜ አይደለም ግን ፍጻሜን ያስንቃል። ምንም እንኳን ባርሴሎናን ስደግፍ የነበረ ቢሆንም ( በ Messi ) ምክንያት Liverpool ባደረገው ነገር መደነቄ እና ማጨብጨቤ አልቀረም። የምደግፈው በመሸነፍ እና በማሸነፍ ላይ ብቻ ሳይሆን የጨዋታ ማራኪነት ላይም ትኩረት አደርጋለሁ። እናም ጨዋታውን ወድጄው ነበር። ያለፈውን የዓለም ዋንጫ ጨዋታውን በልብ መንጠልጠልና በግርምት ነበር ያየሁት። France vs Argentina France እንዳታሸንፍ ብፈልግም Mbappe 3 ጎል በማስገባት አስገርሞኛል። በአድናቆት ልቤ ሲሞላ ነበር። ፍጻሜውን የሚመጥን ጨዋታ እያልኩ በደስታ ስመለከት ነበር። ዛሬም France ከ Norway የምታደርገው ጨዋታ አሪፍ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ - እስካሁን ካየናቸው። እንደዛ ያልኩበት ምክንያቴ Mbappe እና Haland ናቸው። የሁለቱም ጎል የማስቆጠር አካሄድ የሚገርም ነው። አስቡት እስከዛሬ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከፍተኛ ጎል ያለው 16 ነበር ሁሉም ተደምሮ ማለት ነው። ግን እነዚህ ሁለቱ ተጫዋቾች በሁለት ጨዋታ ብቻ 4 , 4 ጎል አላቸው። ነገሩን የበለጠ የሚያጦዘው ደግሞ አሁንም ብዙ የማስገባት ብቃት አላቸው። ማታ 4 ሰዓት የሚፈጠሩ ነገሮችን እናያለን።

ጎድተውኛል ብለህ ያሰብካቸው ሰዎች የጥንካሬህና የድልህ ምክንያቶች መሆናቸውን ብታውቅ ለእነርሱ ያለህን ጥላቻ ታቆም ነበር?

"በዝግ ቤት ጣራው ሰማይ ነው"

ሰው የሚሰማው መስማት የሚፈልገውን ነው።

photo content

ከ France vs Senegal ጨዋታ በኋላ 6:40 አከባቢ ነበር እንቅልፌን የተኛሁት። የ 10 ሰዓቱን የ Argentina vs Algeria ጨዋታ ማየት ፈልጌ ነበር ፥ የሜሲ ደጋፊ ስለሆንኩ። ግን በ 3 ሰዓት ክፍተት ከእንቅልፍ መነሳት ለእኔ ቀላል አይደለም። አላርም ልሞላ አሰብኩና እንቅልፍ ስለሚከብድብኝ ቢጮህም ስለማልነሳ ብዬ ተውኩት። ታዲያ ምን አደረግሁ መሰላችሁ ፥ ጨዋታውን ማየት እንደምፈልግ እና በሰዓቱ መንቃት እንደምፈልግ ለአዕምሮዬ ነገርኩት። በሚገርም ሁኔታ ከእንቅልፌ ስነቃ ሰዓቱ 9:48 ነው። ባዮሎጂ ላይ ጭንቅላታችን ላይ የተፈጥሮ ሰዓት ( natural clock ) እንዳለ አንብቤ ነበር። ነገር ግን እንደዚህ አላርም እየሞላንበት እንደምንጠቀም ግልጥ አልሆነልኝም ነበር😀 ከዚህ ለራሴ አንድ ትምህርት ወሰድኩ። በዓለማችን ላይ ውዱን ንብረት ከአንገቴ በላይ ተሸክሜ እየዞርኩ ግን በሚገባ ሳልጠቀምበት እየኖርኩ እንዳይሆን ብዬ ፈራሁ። አዕምሮ የሚገርም እና ምጡቅ እንደሆነ ከምረዳበት ነገር አንዱ ህልም ነው። ህልም እያየህ ህልምህ እውነት ከመምሰሉ የተነሳ ራስህ በራስህ ህልም ትደመማለህ ፣ ትጨነቃለህ ወይም ትደሰታለህ። ልብ በል እያየህ ያለው ህልም የሌላ ሰው ድርሰት ሳይሆን የራስህ አዕምሮ ውስጥ እየተካሄደ ያለ የአዕምሮህ ፈጠራ ነው። ግን አንዳንዴ ( ይህ ሀሳብ ከእኔ ነው እንዴ የወጣው ) ብለህ እስክትገረም ድረስ ውስብስብ ህልም ታያለህ። ሌላው ወደፊት ሊሆን የሚችለውን ነገር ቀድሞ አውቆ አዕምሮህ ይነግርሃል። ሁሌም ባይሆን አንዳንድ ነገሮች ላይ ሊሆን ያለውን ነገር ቀድመህ ታውቃለህ። በጊዜ ቀድሞህ ሄዶ አዕምሮህ ነገን አይቶ ይመጣል ከዚያም ሊሆን ያለውን ይነግርሃል። አንተም አንዳንድ ውሳኔዎችን ከማድረግ ትቆጠባለህ። ለምን ሲሉህ ምክንያቱን ባታውቀውም ውስጥህ የነገረህ ነገር አለ። እናም ያንን በማድረግህ ከብዙ ጣጣ ትተርፋለህ። ብቻ እግዚአብሔር የሰጠንን አዕምሮ በአግባቡ እንጠቀምበት። ተሸክመን እየዞርን ውድ ነገር ነው። ልንጠቀምበት የሚገባ እና ለበጎ ዓላማ ልናውለው የሚገባ ነው። ለክፋት ካዋልነውም እጅግ በጣም አውዳሚ ሊሆን ይችላል። ለዚህ ምስክር የሚሆን በስም መጥራት የምችለው ሰው በአጠገቤ አለ😆

መምህር :- መዋኘት ትችላለህ? ተማሪ :- አልችልም መምህር:- ከአንተ ውሻ ይሻላል ፣ ቢያንስ እርሱ መዋኘት ይችላል። ተማሪ :- አንተ መዋኘት ትችላለህ? መምህር:- አው ተማሪ :- ታዲያ ከውሻው ጋር ያለህ ልዩነት ምንድነው?

ስራህ ሳያልቅ ቀንህ እንዲያልቅ አትመኝ❕

" ከቆንጆ ሴት ጋር በሚያምር አትክልት ቦታ ለአንድ ሰዓት ተቀመጥ ፥ አንዱ ሰዓት እንደ አንድ ደቂቃ ይሆንብሃል። በጋለ ምድጃ ላይ ደግሞ ሱሪህን አውልቀህ ለአንድ ደቂቃ ተቀመጥ ፥ አንዱ ደቂቃ እንደ አንድ ሰዓት ይሆንብሃል። የንጽጽር ሕግም ይኸው ነው።  "
Albert Einstein - Theory of relativity

አንድ ቀን በአንድ መንደር ሲያልፍ አንድ ቤት በራፍ ላይ፡- «ክፉ ነገር ሁሉ ወደዚህ ቤት አይግባ» የሚል ተለጥፎ ያያል፡፡ ይኸን ጊዜ ዲዮጋን በሩን አንኳኩቶ ባለቤቱ ሲወጣ፡- «ለመሆኑ አንተ እንዴት ገባህ?» ብሎታል፡፡