የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Kanalga Telegram’da o‘tish
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
514
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
ታኀሣሥ 22/2018 ዓ.ም
የሚኖር ቃል፣የማይጠፋ ቅርስ (የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በአቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት)
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የታላቁን የጥበብ ፈርጥ የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው በሕይወት ዘመኑ ያሰባሰባቸውን ከአምስት ሺህ በላይ መጻሕፍት፣ጋዜጣ፣የጽሑፍ እና የሙዚቃ ኅትመት ውጤቶችን ውድ ስብስቦች ራሱን የቻለ ቦታ በመስጠት እና በስሙ የተሰየመ የንባብ ክፍል በማዘጋጀት አደራጅቶ ለንባብ ክፍት አድርጓል፡፡
በመርኀ ግብሩ የዝግጅቱን ዓላማ ያስተላላፉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ሁላችን በምናውቀው ታሪኩ፤ ያየህይራድ አላምረው፤ የግጥም እና ዜማ ደራሲ እንዲሁም ፕሮዲውሰር እንዲያም ሲል የታላላቅ ሙዚቃዊ ፕሮጀክቶች ነዳፊ ኢንተርፕረነር ነበር፡፡ ለብዙዎቻችን በሚያስገርም እና በሚያስደንቅ፣ ብዙም ባልተነገረለት፣ ጥቂት የቅርቦቹ በሆኑ ወዳጆቹ እና በቤተሰቦቹ ዘንድ ብቻ በሚታወቅ ልምዱ ደግሞ፤ የንባብ ፍቅሩን ብዙ እጥፍ የሚያስከነዳ መጽሐፍ ሰብሳቢነቱ አስደናቂ ነበር በማለት ምስክርነትን ሰጥተውለታል፡፡
አክለውም ከኅልፈቱ በኋላ የተገለጸው ምሥጢሩ ይህ መጻሕፍትን እጅግ አድርጎ የመውደዱ ነገር ነው ቢባል ማጋነን አይኾንም፡፡ “ምን ሲያደርግ ሰበሰባቸው?” የሚያስብሉ መጻሕፍትን እና ያልታተሙ መዛግብትን መሰብሰቡን የኅልፈቱ ዜና ከተሰማበት ታኅሣሥ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. ቀደም ባሉ ቀናት የወጡ አዳዲስ መጻሕፍትን ሳይቀር ገዝቶ እያነበበ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ እነዚህን መጻሕፍት በወጉ አደራጅቶ የሚያስቀምጥበት ቤት እንደሚያስፈልገው ለቤቶች ኮርፖሬሽን ማመልከቻ እስከመጻፍ ባደረሰ ፍቅር፣ መጻሕፍቱን የሚያስቀምጥበት ክፍል ቢጠበውም እንኳ፣ መጻሕፍትን ከመሰብሰብ ግን አልመቦዘኑንና ለአገሩ ያለውን ፍቅርና ለመጪው ትውልድ አሻራውን ያሳረፈም እንደነበር ተናግረዋል፡፡
በመርኀ ግብሩ በክብር እንግድነት የተገኙት የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳም ስለ ፕሮዲውሰሩ ያየህይራድ ታላቅ የጥበብ ፈርጥ እና ንባብን በቁም ነገር የሚያነብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ያየህይራድ የሰራውን ስራ ለማወቅ የእርሱን ስራ አንብቡ፣ያየን ውብ ለስላሳ ያደረገው እውቀት ያለው ሰው በመሆኑ ነው በማለት አንባቢነቱን መስክረውለታል፡፡
የቅርብ ጓደኛው ድምጻዊ አረጋኸኝ ወራሽም ስለ ያየህይራድ ብዙዎቻችን የሠራናቸውን ሥራዎች እንኳን የመሰብሰብ ልምዱ የለንም ያየ ተቀደው የሚጣሉ ታሪኮች ሳይቀሩ አስቀምጧል፡፡ያየ በጣም ቀና ሰው ነው ለመተቸት ሳይሆን ለማስተካከል የሚሞክር፣በሚሰራቸው ሥራዎች አዳዲስ ቃላቶችን በማምጣት ለሁላችንም የሚረዳ ነው፡፡
ይህንኑ በመመልከት ኮሚቴ በማዋቀር ከዚህ ዓለም የተለየባት ቀን ለማሰብ ማህበር መመስረቱንም ተናግሯል፡፡
አንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ ዳዊት ይፍሩም ስለፕሮዲውሰሩ የሰራውን ሥራ ለማሳየት አምጥቶ ሲታይለት እናንተ ያያችሁት ሁሉ ትክክል ነው በማለት የሚቀርብ ልበቀና እና በእውቀቱ ልክ የማይኮራ ታላቅ የእውቀት ሰው ነው ሲል መስክሮለታል፡፡
እህቱ ወ/ሮ ሒሩት አላምረውም ወንድሜ በለፋው፣ በደከመው ልክ ቦታ እንዲያገኝ መንገድ አሳየኝ እያልኩ ፈጣሪዬን ስለው እርሱ ግን እስከመቀመጫው ቦታ እመራሻለሁ ብሎ ፍጻሜውን አሳመረልኝ ስትል ምስክርነቷን፤በተጨማሪም ተቋሙ ለሰጣት እውቅናና ክብር አመስግናለች፡፡
በመርኀ ግብሩ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ፣የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዴኤታ ረ/ፕ ነብዩ ባዬ፣አንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ ዳዊት ይፍሩ፣የሙያ ባልደረቦቹ እና የዚህ ዓላማ ጠንሳሽ እህቱ ሒሩት አላምረው እና በርካታ ቤተሰቦቹ ተገኝተውበታል፡፡
በመጨረሻም በቀድሞ ስሙ ወመዘክር የአሁኑ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በ1936 ዓ.ም ሚያዝያ ወር ሲቋቋም የነበረውንና በያየህይራድ ተጠብቆ የቆየውን መተዳደሪያ ደንብ እህቱ ወ/ሮ ሒሩት አላምረው ለተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ለአቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ለፕ/ር ነብዩ ባዬ አበርክተዋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
+1
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የመጻሕፍት ስጦታ አበረከተ።
ሀብቾ ከተማ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ እና ከሆመቾ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል በግቤ ወረዳ ሆመቾ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት አካል በሆነው የጎምቦራ ወረዳ የንባብ ክበባት ምስረታ መርሐግብር ላይ ተቋሙ
ለሀብቾ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በገንዘብ ሲተመን ከ79 ሺህ ብር በላይ የሆነን 260 መጻሕፍትን ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም አበርክቷል።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ወ/ሮ ሙሉነሽ ላሞሬ እና የጎምቦራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ጎበነ ለንባብ ባህል መዳበር እና ለትምህርት ጥራት እንዲሁም ለተማሪዎች ውጤታማነት የመምህራን እና ወላጆች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
+2
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የመጻሕፍት ስጦታ እና የስልጠና መርሐግብር ያካተተ የንባብ ሳምንት እያከናወነ ነው።
ሆሳዕና ከተማ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ እና ከሆመቾ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል በግቤ ወረዳ ሆመቾ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት ላይ የቤተ መጻሕፍት እና የሰነድ እና መዛግብት ስልጠናን ለዘርፉ ባለሙያዎች እየሰጠ ነው።
የስልጠናው አስፈላጊነት በዘርፉ ያለውን ሙያዊ ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ በተቋሙና በከተማው አመራሮች የተገለጸ ሲሆን ሰልጣኞቹ ስልጠናው ተከታታይነት እንዲኖረው ጥያቄ አቅርበዋል።
ተቋሙ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ እና ከሆመቾ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት በግቤ ወረዳ ላሉ 11 ትምህርት ቤቶችና በጎንቦሮ ወረዳ ለሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት 3268 መጻሕፍት፤ በገንዘብ ሲተመን 1,006,389 ብር የሆነ ስጦታን የንባብ ባህልን በማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እንዲያግዝ አበርክቷል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
የተማሪዎች አቅም ጎልብቶ የትምህርት ጥራት እንዲጠበቅ በንባብ ባህል ላይ መስራት ያስፈልጋል ተባለ።
ሆሳዕና ከተማ
ታህሳስ 21/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል በግቤ ወረዳ ሆመቾ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና አውደ ውይይት ታህሳስ 21ቀን 2018 ዓ.ም በግቤ ወረዳ ተጀምሯል።
በመርሐግብሩ የንባብ ሳምንቱን ዓላማ አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ የንባብ ጠቀሜታን ሲገልጹ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ያለውን ሚና አስረድተዋል።
በመድረኩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በሆምቾ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ምስጋናው ዓለሙ፣ እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል በተከበሩ ወ/ሮ ሙሉነሽ ላሞሬ ሲያደርጉ የንባብ ባህልና የትምህርት ጥራትን ትስስር አብራርተዋል። በተጨማሪም በቀድሞው የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ጸሐይ አድማሱ እና በኢንጂነር አበራ አቤቦ የተሞክሮ እና አነቃቂ ንግግር ተደርጓል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
ታኀሣሥ 21/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሀድያ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በግቤ ወረዳ ሆመቾ ከተማ የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና አውደ ውይይት በግቤ ወረዳ እያካሔደ ይገኛል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ረቡዕ ታኀሣሥ 22/2018 ዓ.ም ልዩ ቀጠሮ ይዟል!!
ስም አይቀበርም!!
==========
ፕሮዲውሰር ያየህ ይራድ አላምረው ከሰራቸው በርካታ ስራዎች በጥቂቱ ለማስታወሻ፡-
-የአስቴር አወቀ "የሰርጌ ትዝታወይም ትውስ አለኝና" በሚል የሚታወቀውን ካሴት ሙሉ ግጥም
-የፀሐዬ ዮሐንስ "እወራረዳለሁ፣ምን ይውጠኝ ነበር"፣
-የሀይልዬ "የኢትዮጵያ አምላክ፣
-የኩኩ ሰብስቤ "ኢትዮጵያ (ይታየኛል)፣
-የፀጋዬ እሸቱ "10ቱ ትዕዛዛት"፣
-የታደለ ሮባ "ባቲና ብሉዝ" -
-የክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ "ቆሜ ልመርቅሽ" -
-ለጌራወርቅ ነቃ ጥበብ እና ለሌሎችም የአርት ሰዎች በርካታ ግጥሞችን የሰጠ ሲሆን በተለይ ደግሞ ልክ እንደ የፍቅር አልበም በየቤታችን ገብቶ ያጣጣምነውን በኤች.አይ.ቪ ዙሪያ በርካታ ተወዳጅ አርቲስቶች የተሳተፉበትን "እንኖራለን ገና " የሚለውን አልበም በማስተባበር እና ድርሰቶች በመስራት ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ነበር፡፡
ፕሮዲውሰር ያየህ ይራድ ብዙ ሰዎች በስም እንጂ በአካል እንደ ማያውቁት ይናገራሉ፡፡ለሀገሩ ኢትዮጵያ ስላለው ፍቅር በየሚዲያው ባይናገርም ለተለያዩ ድምጻውያን የሰጣቸው ግጥሞች ምስክሮቹ ናቸው፡፡ለምሳሌ፡-
ለፀጋዬ እሸቱ
፲ቱ ትዕዛዛት
" የፈጣሪ ትዕዛዝ ቃሉ ቢከበር
ወንጀለኛ መቅጫ ህግም ባልነበር
ከምድራዊው ፖሊስ ከሕግ አስከባሪ፣እንፍራ ፈጣሪን
በኩኩ ሰብስቤ
የሺ ዓመታት የአፍሪካ ገናና
ተከብራ የኖረች በዓለም ዙሪያ ገና
ኢትዮጵያ ዳግም እንደገና
ይታየኛል የሀገር አውራ ሆና የሚለው፡፡
በኃይልዬ ታደሰ
የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ሳይውል ሳያድር
ይጥልላታል ጠላቷን እባንዲራው ስር
አይቀር አንድ ቀን መድረሱ ወቅቱን ጠብቆ
ማሪኝ ይላታል ጠላቷ
እጇ ላይ ወድቆ
በታደለ ሮባ እና ፋንታ በሌ
(ባቲ እና ብሉዝ ) የቅብብል ሥራ
አባም እንዳልልህ ዘመናዊ
ፀጉር አወራረድህ ባህታዊ
ከየት ነው የመጣህ ምናዊ
ለሀገራችን የሙዚቃ ንጉሥ ጥላሁን ገሠሠ የመጨረሻ ሥራ ውስጥ
ቆሜ ልመርቅሽ ተቀበይኝ እማ
ህይወትን መርቀሽ
ሠጠሽኝ እኔማ
ይህ ቀረኝ የምለው የሚቆጨኝ በዓለም ኢትዮጵያ እድሜ ላንቺ ያላየሁት የለም
አንገትሽ ራስሽን ችሎ ልየው እና
ማግስቱን ይውሰደኝ አስር ሞት ይምጣና
ያየህይራድ አላምረው ከቀድሞው ጀግናው የኢትዮጵያ ሠራዊት ቤተሰብ የተገኘ አንጋፋ እና በሳል የዘፈን ግጥም ፀሐፊ እና ፕሮዲውሰር አንዱ ሲሆን ከእርሱ በላይ ስራዎቹ በሀገራችን ሕዝቦች ዘንድ በጥልቀት የሚታወቅ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይህንን የጥበብ ዋርካ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተውን አንጋፋውን የጥበብ ሰው እንዲሁም የበርካታ ግጥምና ዜማዎች ፕሮዲውሰር ያየህይራድ አላምረው በሕይወት ዘመኑ ያሰባሰባቸውን በዓይነትም በቁጥርም በርካታ መጻሕፍት፣የጽሑፍ እና የሙዚቃ ኅትመት ውጤቶችን ውድ ስብስቦች በልዩ ሁኔታ ራሱን የቻለ ቦታ በመስጠትና በስሙ የተሰየመ የንባብ ክፍል በማዘጋጀት ልዩ የርክክብ ሥነ ሥርዓት ያካሒዳል፡፡
በመሆኑም ለዚህ ባለውለታ በሚደረግ መርኀ ግብር ላይ እንድትገኙ በድጋሚ በክብር ተጋብዘዋል።
መርኀ ግብሩ የሚካሔድበት ቦታ፡- በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት አዲሱ ሕንጻ ላይ
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
+1
ባለውለታዎቻችንን እናስባቸው!!
=====================
ተቋማችን በሙያው ለሀገሩ በርካታ አበርክቶ ያበረከተውን ታላቁን የዜማና ግጥም ደራሲ እና ፕሮዱሰር አርቲስት ያየህይራድ አላምረው መታሰቢያነት ቤተመጻሕፍት ለመክፈት ቃል በገባው መሰረት ዝግጅቱን አጠናቆ ታዳሚውን በክብር እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በየሙያ ዘርፋቸው ለሀገራቸው ውለታ የዋሉ ግለሰቦችን እንዳይረሱ የሚያደርጉ ሥራዎችን ከመስራት እና እውቀትና ከመስጠት ባሻገር በሕይወት ዘመናቸው የተጠቀሙባቸውን መጻሕፍት፣መጽሔቶች፣ጋዜጦችን በማሰባሰብ፣በማደራጀት፣ጠብቆ ለትውልድ ተሻጋሪ የማድረግ ስራ በስፋ ይሰራል፡፡
ይህንኑ ተግባሩን እውን ለማድረግ የዜማና ግጥም ደራሲ እና ፕሮዱሰር አርቲስት ያየህይራድ አላምረው በሕይወት ዘመኑ ሲጠቀምባቸው የነበሩ መጻሕፍት እና ሌሎች የመረጃ ሀብቶችን ወደ አገልግሎቱ በማዛወር ለአርቲስቱ መታሰቢያ በተከፈተ ቤተመጻሕፍት ያደራጀውን ረቡዕ ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በይፋ ያስጀምራል፡፡
በመሆኑም አገልግሎቱ ለአርቲስቱ መታሰቢያነት የተከፈተውን ቤተመጻሕፍት በይፋ ለማስጀመር ዝግጅቱን ስላጠናቀቀ በዕለቱ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ላይ እንድትገኙ በክብር ተጋብዛችኀል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ቲዊተር:https//@wemezekr
* እንኳን ደስ አላችሁ፥ እንኳን ደስ አለን!!!
========o=======
ግራንድ አፍሪካን የተቋማት እና የአመራር ሽልማት ድርጅት፥ ታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በዓድዋ መታሰቢያ ሚውዚዬም በተዘጋጀ ታላቅ የሽልማት ሥነ ሥርዓት፣ ተቋማችንን (ተቋማችሁን)፥ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክርን)፥ የወርቅ ደረጃ ተሸላሚ ተቋም አድርጎ ሸልሞታል።
ቤተጻሕፍት ወመዘክር ከተቋቋመበት ከ1936 ዓ.ም. ጀምሮ፣ "ሀገረ መጻሕፍት" የተሰኘችውን ውዲቷ ሀገራችንን፣ መጻሕፍቷን እና መዛግብቷን በዘመናዊ መልክ አሰባስቦ አንባቢ እና ተመራማሪ ትውልድ የመፍጠር፣ ዕውቀት እና መረጃ የሚደራጅበትን ሥርዓት የማበጀት ሥራ እየሠራ 82 ዓመታትን ዘልቋል።
በዚህ ለአንድ ምዕተ ዓመት እየተጠጋ ባለ የተቋም ዕድሜ ውስጥ፥ በሕይወተ ሥጋ የተለዩን እና ከእነሱ ተቋሙን ተረክበው ዛሬም በቅንነት እና በትጋት እያገለገሉ ያሉ ሠራተኞቹ ለዚህ በሕዝብ ፊት ለተሠጠው ታላቅ ዕውቅና ቀዳሚ ተመስጋኞች ናቸው።
ተቋሙን ከ1936 ዓ.ም. ጀምሮ የመሩ 14 አመራሮች፥ ከክቡር አቶ ሠረቀ ብርሃን ገብረ እግዚእ ጀምሮ፣ ክቡር አቶ አርአያ ኃይለ ሥላሴን፣ ክቡር ብላታ ሣሕሌ ጸዳሉን፣ ክቡር አቶ ከበደ ሚካኤልን፣ ክቡር አቶ ተክለ ጻድቅ መኩሪያን....እንዲሁም ክቡር አቶ ይኵኖ አምላክ መዝገቡን፥ የተቋሙን ስም እና ክብር በሚመጥን መልኩ ለሠጡት አመራር እና ላኖሩት ደማቅ አሻራ የተሠጠ ዕውቅና እንደኾነም እናስባለን።
ለተቋሙ ባላቸው ፍቅር የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ትልቅ እገዛ የሚያደርጉ በጎ አድራጊ የተቋሙ ወዳጆችም የተመሰገኑበት ዕውቂያ እና ሽልማትም ነው ማለት ይቻላል።
ከዚህ ኹሉ በላይ፥ የወደፊቱን ሥራችንን በጥንቃቄ፣ በትጋት፣ ዘመንን በሚዋጅ ሥልት እና ዐቅድ የመፈጸም አደራም የሚጥልብን ኾኖ አግኝተነዋል። ስለኾነም፥ ከሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ማግስት ጀምሮ ወገብን አጥብቆ የመሥራት ኃላፊነትን ያስገነዘበን በሕዝብ ፊት የተሠጠ አደራም ጭምር ነው።
ግራንድ አፍሪካን የሽልማት ድርጅትን ለሠጠን ዕውቅና ከልብ እናመሰግናለን። ለተቋማችን ሠራተኞች እና የማኔጅመንት አባላት፣ እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ የሚለውን መልእክት ሳቀርብ እጅግ ታላቅ ደስታ እየተሰማኝ ነው። የስኬት ባለውለታዎችን ኹሉ ወክዬ በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝቼ፥ ከክቡር ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ (የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዝዳንት) እጅ ሽልማቱን በመቀበሌ የተሰማኝ ደስታ ወሰን የለውም። ዕውቅናውን ከነአደራው መረከቤን በዚሁ አጋጣሚ መግለጽ እወዳለሁ።
እንኳን ደስ አላችሁ፥ እንኳን ደስ አለን።
ታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
ሠርፀ ፍሬስብሐት
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት
ዋና ዳይሬክተር።
በህጻናት ላይ ለሚሰሩ ሙያተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ ጋር በመተባበር በልጆች ሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ዓለም አቀፍ አበርክቶ ያለውና አፍሪካዊ ተረቶችን በማሰባሰብ በአምስት ቋንቋዎች በርካታ የልጆች መጻሕፍትን በማዘጋጀት በሚታወቀው ጋናዊ የልጆች መጻሕፍት ደራሲ እና ተዋናይ ሚስተር ፓትሪክ አዳዳይ (Mr.Patrick Addai) በመጋበዝ ለኢትዮጵያ የህፃናት መጽሐፍ ጸሃፊዎች እና ተራኪዎች የተዘጋጀ ሙያዊ ልምድ ልውውጥ እና የይዘት ፈጠራ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ታህሣሥ 9/2018 ዓ.ም ተሰጥቷል፡
በልምድ ልውውጡ ደራሲው የአፍሪካዊ ተረቶች ይዘት፣ለበለፀጉ አህጉራዊ ማንነት ለቀረው ዓለም በጽሑፍ የማስተዋወቅ ዘዴንና በትወና መጻሕፍትን የመተረክ ጥበብን የተመለከተ ልምዱን ለኢትዮጵያውያን ጸሐፍት ልምዱን አጋርቷል፡፡
የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ተቋሙ ይሔንን ዝግጅት አብሮ በማዘጋጀት በዘርፉ ለሚሰሩ ድርጅቶች፣በተቋሙ በዘርፉ ለሚሰሩ ባለሙያዎች እድሉን አግኝተው በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ የልምድ ልውውጥ መድረክ መሳተፋቸውን ጥሩ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ተናግረው
አክለውም የደራሲው መጽሐፍት ለተቋሙ ለማበርከት ቃል መገባቱ ወደዚህ ተቋም ለመገልገል የሚመጡ አንባቢያን እንደፈለጉ ማግኘት እንዲችሉና ለደራሲውም መጽሐፉ በዚህ ሀገራዊ ተቋም መቀመጡ እና መነበብ የሚችልበትን ትልቅ አጋጣሚ የሚፈጥር እንደሆነም ተናግረዋል፡
በኢትዮጵያ የኦስትሪያ ኢምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት የቀጣይ የደራሲው ጉዞ ወደ ኦስትሪያ እንደሆነና ከኢትዮጵያ የልጆች የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ዙሪያ ሥራዎችን ለመስራት እቅዱ እንዳለም ተናግረዋል፡
በዝግጅቱ የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው፣በኢትዮጵያ የኦስትሪያ ኢምባሲ ተወካይ፣የህጻናት መጽሐፍ ጸሐፊዎች፣በዘርፉ የሚሰሩ ድርጅቶች እንዲሁም በተቋሙ የዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎች የተገኙበት ነበር፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ነገ ታህሣሥ 9/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በኀሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ በክብር ተጋብዘዋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የማይቀርበት መድረክ በክብር ተጋብዘዋል!!!
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ ጋር በመተባበር በልጆች ሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ዓለም አቀፍ አበርክቶ ያለውና አፍሪካዊ ተረቶችን በማሰባሰብ በአምስት ቋንቋዎች በርካታ የልጆች መጻሕፍትን በማዘጋጀት የሚታወቀው ጋናዊ የልጆች መጻሕፍት ደራሲ እና ተዋናይ ሚስተር ፓትሪክ አባዳይ (Mr.Patrick Addai) በመጋበዝ
ለኢትዮጵያ የህፃናት መጽሐፍ ጸሃፊዎች እና ተራኪዎች የተዘጋጀ ሙያዊ ልምድ ልውውጥ እና የይዘት ፈጠራ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ሐሙስ ታህሣሥ 9/2018 ዓ.ም ከ8፡00 -10፡00 ሰዓት በተቋሙ ቅጥር ጊቢ ኀሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ ስልጠናው ስለሚሰጥ በዘርፉ የምትሰሩ ድርጅቶች እና ፍላጎቱ ያላችሁ እንድትሳተፉ በክብር ተጋብዛችኋል፡፡
አዘጋጆች፡-
- የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት
-የኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ለሚመለከተው በሙሉ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በየዓመቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በሚዘጋጀው ሀገር ዓቀፍ የግእዝ ጉባዔ ላይ ዘርፉን የሚያጎለብቱ እና ለትውልዱ የሚጠቅሙ መነሻ ጽሑፎችን አወዳድሮ ለዝግጅቱ ማቅረብ ይፈልጋል፡፡
ዘንድሮ ለዘጠነኛ ግዜ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከሚያዚያ 15 - 17 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያዘጋጀው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የግእዝ ጉባዔ ዓውደ ጥናት ላይ ለጉባዔው መወያያነት የሚበቁ ጽሑፎችን በተቀመጠው መስፈርትና የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለውድድር ክፍት ስላደረገ በዘርፉ ልምዱ ያላችሁ እንድትሳተፉ እናሳውቃለን፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከድሬዳዋ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ከታህሳስ 2/2018 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ቀን፤ስልጠና እና የፓናል ውይይት በድሬ ቲቪ ከተላለፈ የተወሰደ
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
