የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Kanalga Telegram’da o‘tish
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
509
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
+2
የዘንድሮ 7ኛው አገራዊ ምርጫ የጥቃት ኢላማ ሆኖ ነበር።(ጠ/ሚ ዐቢይ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር))
የዘንድሮው ምርጫ ትልቅ ትምህርት የሰጠ ሆኖ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ እንዳይካሄድ የሚፈልጉ አካላት በርካታ ጥረቶችን ቢያደርጉም ምርጫው ትልቅ ትምህርት የተወሰደበት ሆኖ በስኬት ተጠናቋል ብለዋል፡፡
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ከነበሩት ምርጫዎች አንድ የሚለይበት ባህሪ አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "የምርጫው ሂደት በተለያዩ የውስጥ እና የውጭ ኃይሎች የጥቃት ኢላማ ሆኖ ነበር" ሲሉ አብራርተዋል፡፡
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እንዳይደረግ፣ ዜጎችም ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ እንዳይጠቀሙ ቅስቀሳዎች መደረጋቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ዜጎች በአንድ ድምጽ የጋራ ሀገር ለማጽናት በምርጫው ላይ መሳተፋቸው ዜጎች ለሰላማዊ ሀገረመንግስት ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት መሆኑን አንስተዋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
"የዘንድሮው ምርጫ ኢትዮጵያውያን ጽንፈኝነትን በተግባር ያሸነፉበት ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ፣ የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ በርካታ ትምህርቶች የተገነዘቡበት እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት የኖረውን ድልብ የሀገር ግንባታ ባሕል በተግባር ያረጋገጠበት ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ወቅት፣ ምርጫው ራሱ የጥቃት ዒላማ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን የተሰነዘረውን ጥቃት በጽናት መክቶ አሸናፊ መሆን መቻሉን አስታውቀዋል።
"በዘንድሮው ምርጫ አይሳካም" የሚለው አፍራሽ ሐሳብ የብዙዎች ድምፅ ሆኖ በነበረበት ወቅት፣ ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆም ጽንፈኝነትን በተግባር ውድቅ ማድረጋቸውንም አብራርተዋል። ለዚህም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።
በምርጫው ሂደት ላይ የታየውን ሕዝባዊ ተሳትፎ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አዛውንቶች፣ ታማሚዎች፣ ሐዘንተኞች እና እመጫቶች ጭምር በከፍተኛ ስሜት እና ቁርጠኝነት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል።
ይህ የታየው ከፍተኛ ድምፅ እጅግ ታላቅ መልዕክት ያዘለ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ይህንን የሕዝብ ውሳኔና ድምፅ በግዴለሽነት እንደማይመለከተውና ከፍተኛ ክብርና ዋጋ እንደሚሰጠው በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
"ይህንን የሕዝብ ታላቅ ድምፅ አቅልለን አንወስደውም፤ ትልቅ ክብር እንሰጣለን።" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጠናቀቀው ምክር ቤት ውስጥ ለነበራቸው ቆይታ የምክር ቤቱ አባላት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ላቅ ያለ ምሥጋና አቅርበዋል።
አያይዘውም በቀጣዩ የሥራ ዘመን በምክር ቤቱ ውስጥ የማይቀጥሉትን አባላት ጨምሮ፣ ሁሉም ወገኖች ወደፊትም ለሀገር ግንባታና ለሕዝብ አገልግሎት የሚያደርጉትን ንቁ ተሳትፎና በጎ አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የሕ/ተ/ም/ቤት5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የስራ ዘመኑን ካጠናቀቀው ከተሰነባቹ የምክር ቤት አባላት የተነሱ ሃሳብ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች፦
ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያቀረቡላቸውን ጥያቄዎች በተመለከተ
📌 በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥና የትግራይ ህዝብ ከሀገራዊ የልማት ፍሬ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆን መንግሥት በአሁኑ ወቅት እየወሰዳቸው ያሉ ተጨባጭ እርምጃዎችና የወደፊት እቅዶች ምንድናቸው? ከሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ፣ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ የሚዲያ ሰዎችና ፖለቲካኞች ምን ይጠበቃል?
📌የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተጠናቆ የታለመለትን ሀገራዊ አላማ እንዲያሳካ መንግስት በቀጣይ ምን አይነት የሎጅስቲክስ፣ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ድጋፍ ያደርጋል?
📌ይህ ታላቅ ሀገራዊ እድል ያለመስተጓጎል እንዲሳካ ከእያንዳንዱ ዜጋ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪክ ተቋማት፣ ከኢትዮጵያ ወዳጆችና አጋር አካላት በአሁኑ ወቅት ምን አይነት ንቁ ተሳትፎና የጋራ ሀላፊነት ይጠበቃል?
📌ተጀመረው ላልተጠናቀቁ እና ሳይጀመሩ ታቅደው ለቀሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ?
📌የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች 35 በመቶ ግብር፣ 7በመቶ ጡረታ በድምሩ 42 በመቶ ይቆረጥበታል። እጁ ላይ ከሚደርሰው 58 በመቶ ደመወዝ ላይ በእያንዳንዱ በሚሸምተው ሸቀጣሸቀጥ ላይ 15 በመቶ ቫት ይቆረጣል።
📌ለሌሎች አገልገሎቶችም የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላል። የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛው እነዚህ ችግሮች ተዳምረው ኑሮን መቋቋም አቅቷቸዋል እና ምን ታስቧል? ከሚመሰረቱት መንግስት ምን እንጠብቅ?
📌በአዲስ አበባ ያለው የተማሪዎች ምገባ በሌሎች ክልሎችም እንዲጀመር እና አስገዳጅ ቢደረግ?
📌የባህር በር ጥያቄ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ቢያብራሩልን
📌በከፍተኛ ዋጋና ድጎማ የገበውን ነዳጅ ለምን በትክክል ማሰራጨት አልተቻለም? መፍትሔውስ ምንድን ነው?
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና በ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
+9
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የሕ/ተ/ም/ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ተጀምሯል።
የሕ/ተ/ም/ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄዎቻቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ሊያቀርቡ ነው።
በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 17 እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3 መሠረት የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለስልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡
በዚሁ ሕገ መንግሥትና የምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡
በተያያዘም ምክር ቤቱ ፣ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል፡፡
በስብሰባው ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች የሚገኙ ሲሆን የጉባኤው ሙሉ ሂደትም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ለውድ የተቋማችን አመራሮች እና ሠራተኞች በተከታታይ ለአራተኛ ግዜ በየሁለት ሳምንት በደመቀ መልኩ ስናካሂድ የነበረው "እንገናኝ እንሰናኝ!" የሰኞ ንጋት የሠራተኞች መድረክ ነገ ሰኞ ሰኔ 29/2018 ዓ.ም የማይኖር መሆኑን ከወዲሁ ማሳወቅ እንወዳለን።
ተለዋጭ ፕሮግራማችንን በዚሁ በውስጥ ገጻችን የምናሳውቅ ይሆናል።
እናመሠግናለን።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ሴቶች በቴክኖሎጂ እና የ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያ ያላቸው ሚና በሚመለከት ስልጠና ተሰጠ፡፡
ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ለተቋሙ ሴት ሰራተኞች የሴቶችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና የ2030ን ዲጂታል ኢትዮጵያ ተሳታፊነት ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በተቋሙ የአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሀብቶች መሪ ሥራ አሥፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው በንግግራቸው አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታና ዓለማችን የቴክኖሎጂ ታሪክ ባለቤት የሆነችበት ወቅት ላይ ሴቶች ከጥንቱ የእርሻ ዘመን ጀምሮ በማህበረሰብ ውስጥ ያላቸውን ሚና በሚመለከት ለተቋሙ ሴት ሰራተኞች ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ የሚያስመሰግነው መሆኑን ተናግረዋል።
ስልጠናውን የሰጠው ወጣቱ የBayan Software Solution ባለሙያ ቢኒያም ፈለቀ በስልጠናው የሰው ልጅ እድገትና ስልጣኔ ከጥንታዊ የድንጋይ ዘመን እስከ አሁነኛው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ(ሰው ሰራሽ አስተውሎት) ድረስ ያለውን ሂደት ከማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና የልማትና እድገት ጉዞ ከሴቶች ሚና አንጻር እንዲሁም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ(ሰው ሰራሽ አስተውሎት) ጋር ተያይዘው ያሉ ስጋቶችንና ጉዳቶችን እንዴት ለይተን መከላከል እንችላለን የሚለውን በሚመለከት ሰልጣኞችን አሳታፊ የሆነ ስልጠና ሰጥቷል።
የተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አሥፈጻሚ ወ/ሮ አገሬ መኮንን የኢትዮጵያ ሴቶች በተለያዩ ዘርፎች አሁን ላይ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ተጠቃሽ የሚሆኑ ከራሳቸው አልፈው ለሀገር ብዙ ያተረፉ ሴቶችን በምሳሌነት በማንሳት ሴቶችና የቴክኖሎጂን ትስስር አስመልክቶ ያለው ተለምዷዊ እስቤ መቀየር እንዳለበት እና እንደ ሴት እራሳችንን ልናበቃ እንደሚገባ አበክረው ገልጸዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ልክ የዛሬ ወር ከእናንተ ጋር የበረታ ቀጠሮ አለን!
"ንባብ ለሕይወት ሐሙስ ሐምሌ 23/2018
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በድምቀት ይከፈታል።
በርካታ የመጻሕፍት አሳታሚዎች፣ደራሲያን፣የምርምር ተቋማት ምዝገባቸውን አጠናቀው፤ለኤግዚቢሽኑ ስምረት እየተዘጋጁ ነው።
እርሶም ከሐምሌ 23-26/2018 በመረጡት ቀን የድግሳችን ተቋዳሽ ለመሆን ይዘገጁ።
ተቋማዊ ዓመታዊ የድጋፍ እና ክትትል ስራ ተካሄደ፡፡
ሰኔ 25/ 2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የእስትራቴጂክ ሱፐርቪዥን ቡድን የተውጣጡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትን የ2018 በጀት ዓመት ተቋማት ክንውን ዙሪያ ዓመታዊ የድጋፍ እና ክትትል ውይይት አካሂደዋል፡፡
ድጋፍና ክትትሉ ትኩረት ያደረገው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ተግባራት በተዘጋጁ ቼክ ሊስቶች መሰረት በሰነድ ግምገማ፣ መስክ ምልከታ፣ ቃለ ምልልስ እና በውይይት አግባብ ስራቸውን እንዲቀርቡ ቼክ ሊስት በመስጠት በቼክ ሊስቱ መሠረት በጥልቀት የስራ ክፍሎች ሥራ አስፈጻሚዎች ያከናወኑትን ተግባራት በማቅረብ እና ክንውኖችን ሲያከናውኑ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በመጠቆም እና እንደ ስራ ክፍል ለስራዎች መሳካት የተጠቀሟቸውን ስልቶች በመግለጽ ነበር፡፡
በአፈጻጸም ደካማ የሆኑባቸውን አፈጻጸሞችንም በመግለጽ ለወደፊት የሚስተካከሉበትንም አማራጮች በማቅረብ እንዲሁም ለሌሎች ተቋማት ጥሩ ተሞክሮ ናቸው የሚሏቸውንም ለሱፐርቪዥን ቡድኑ ለውይይት በማቅረብ ተቀባይነትንና እውቅናንም አግኝተዋል፡፡
በድጋፍና ክትትሉ ላይም የተቋሙ ሥራ አስፈጻሚዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እና ድጋፍም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚፈልጉ ሃሳቦችንም በጥልቀት እንዲታይ፤ ተቋሙ ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ እና የሥራ ባህሪውም ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ልዩ ስለሚያደርገው ራሱን የሚመራበት ፖሊሲ እንደሚያስፈልገው እና ያለው 179/91 አዋጅ የቆየና ተቋሙን ሙሉ ለሙሉ ትኩረት ያላደረገም እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
በአቶ ብሩክ ተፈራ ሰብሳቢነት የሚመራው ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተውጣጣው የድጋፍ እና የክትትል ቡድን አባላቱ በቀረቡት የበጀት ዓመቱ ክንውን መሳካት እና የሥራ ክፍል አመራሮች ልባቸውን ሞልተው እቅዳቸውን አውቀው በቃል ሥራቸውን ማቅረብ የቻሉት የተቋሙ የበላይ አመራር ለስራው ኃላፊነቱን ሰጥቶ እንዲሰሩ በማድረጉ እና ከዚህ በፊት ክፍት የነበሩትንና በውክልና ሲመሩ የነበሩ ሥራ ክፍሎችን በሰው ኃይል እንዲሟሉ በማድረግ ለሥራው ትኩረት በመስጠት የስራ ክፍሎቹ በእውቀት እንዲመሩ በማድረጉ የተቋሙን የበላይ አመራርን አመስግነዋል፡፡
በመጨረሻም የዓመታዊ የድጋፍ እና የክትትል ቡድን አባላቱ የተቋሙን የአገልግሎት ክፍሎቹንና እንዲሁም በዲጅታል 2030 ዓ.ም በመንግስት ደረጃ ለተያዘው ዲጂታል ኢትዮጵያ ትኩረት የተሰጠውን እንደ እኛ ተቋም የሚገኙ የሀገር መረጃዎች ሜታዳታ በትክክል መሙላት እንዲችሉ የሚያስችለውን አዲሱን ዲጂታላይዝ ማሽን ያለበትን ደረጃ በመጎብኘት እና ተቋሙ እውቅና ያገኘባቸውን የተቋማት የሠነድ ማደራጀት ሥራ ቡድኑ የሚመለከትበትን ሁኔታ እንዲመቻች ጥቆማ በመስጠት እና ለምልከታው ማመቻቸት ያለበትን ሥራ ኃላፊነት በመውሰድ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤትን እና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሠነድ አደረጃጀት እንዲመለከቱ ጥቆማ በመስጠት የምልከታ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
የማይቀርበት የዕውቀት ድግስ!!
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እና በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክት አዘጋጅነት ከሐምሌ 23 እስከ 26/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ታላቅ የዕውቀት ድግስ ተዘጋጅቷል፡፡
በዝግጅቱ፡-የምርምር ተቋማት፣የዕውቀት ማዕከላት፣በርካታ አንጋፋና ወጣት ደራሲያን፣አሳታሚዎች፣የመጻሕፍት መደብሮች በስፋት ይሳተፋሉ።
የመጻሕፍት ዋጋ ላይ ልዩ ቅናሽ ይደረጋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
