7 369
Підписники
+524 години
+617 днів
+35230 день
Архів дописів
7 366
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
መንግሥታዊ ፍጅት በአርሲ ምድር
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ልጆችዋ ላይ የሚደርሰው ጥቃት እንደ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን፦ ሥርዐታዊ፣መዋቅራዊና ርዕዮተዓለማዊ ነው፣ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ግብ ያለው ነው፣ከኦርቶዶክስ የጸዳች አዲስ ሀገር የመፍጠር ጉዞ ነው። የጥቃቱ ዓይነት ቢለያይም ዋና ዓለማቸው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ኦርቶዶክሳውያንን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጽዳት ነው።ይኽን እቅዳቸውን ከግብ ለማድረስ በአራቱም አቅጣጫ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የመከራ እሳት የተለኮሰ ቢሆንም በኦሮሚያ ክልል እየሆነ ያለው ግን ይለያል ከሁሉም ደግሞ በአርሲ ምድር።የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን የሚታረዱት በመንግሥት መዋቅር እና ከፑንትላንድ እስከ አርሲና ባሌ በተዘረጋው በአልሸባብና በአይአይ ኤስ የአሸባሪ ቡድን ነው። ሰሞኑን በሽርኮ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተሠሩ ሥርዐታዊ ውንብድናዎችን በመረጃና ማስረጃ አጋልጣለው።
ፎቶ አንድ(1)
ኦቢኤን ከሁለት ቀናት በፊት "ኦርቶዶክሳውያን አልተገደሉም"የሚል የሠራው ዶክሜንተሪ ነው።በዚህ ዶክመንተሪ ላይ ካህናትና ኦርቶዶክሳውያን ሽማግሎች "በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ሐሰት ነው" እንዲሉ ተገደዋል።የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጣሂር አማኖ "በወረዳችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲነዙ የነበሩና አሁንም እየተነዙ ያለው ወሬዎች ውሸት ናቸው (ኦርቶዶክሱ አልተገደለም) እንዲህ ዓይነት ወሬዎች ኦርቶዶክሱ በወረዳችን ላይ እንዳይኖር ያደርጋል" ሲል የኦርቶዶክሳውያንን ፍጅት ክዷል ዳግም ጥቃት ሊፈጽሙ እንደሚችሉም ዝቷል። አቶ ጣሂር አብደላ አማን( አብደላ ማይክሮ) ከሚባል ባለሥልጣናት ጋር ከመተባበር ለወሀቢያዎቹ ድጋፍ የሚያደርግና ኦርቶዶክሳውያንን በማስጨፍጨፍ እጁ በደም የቆሸሸ ሰው ነው።በዚህ ወረዳ ከ164 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል(ታግተው ደብዛቸው የጠፋ ይኑሩ ይሙቱ ዩማይታወቅ 26 ኦርቶዶክሳውያንን) ሳያካትት።ዛሬ ሥልጣኑንም ሚዲያውንም ባንኩንም ታንኩን ስለ ተቆጣጠሩት እንደፈለጋቸው ይወሻሉ በሞታችን ላይ ይሳለቃሉ ነገ ግን ከርድ አያመልጧትም።ለሙስሊሙ ሕዝብ ጭምር ጥቁር ታሪክ እያስቀመጡ ነው።
ፎቶ ሁለት(2)
ከዘጠኛ (9)ቀናት በፊት የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያ "ከሽር ካወረዳ ጋዶ ቀጠና ተፈናቅለው ወደ ጎረቤት ወረዳ የሸሹ ምዕመናን የመመለስ ስራ ተጀምሮአል ተፈናቃዮቹን በቀበሌ በመለየት ከሚታና ጋዶ ቀበሌ የተፈናቀሉት ከጋዶ ከተማ በስተ ደቡብ ከሰንጎ ያያ ቀበሌ የተፈናቀሉ ከጋዶ ከተማ በስተ ምስራቅ ቦታ በማዘጋጀት ፕላን እና ካርታ ተሰርቶ ለአንድ አባ ወራ 250 ካሬ ለ200አባወራ የወረዳው ቤተክህነት የወረዳው አስተዳደር የዞን እና የክልል ተወካዮች በተገኙበት የቦታ ርክክብ ተፈጽሞ ለህዝቡ በእጣ ተከፋፎሎ ጌዜያዊ ካርታ ተሰቶአል"በማለት በገጹ ላይ የፖሰተው ነው። እዚህ ጋር ሁለት ነገር ልብ እንበል
1) ዜናው "ምዕመናን" እንጂ ኦርቶዶክሳውያን አይልም።ኦርቶዶክሳውያን አልተገደሉም አልተፈናቀሉም ለማለት ሆን ተብሎ የተሸረበ ሴራ ነው።
2) የእስልምና እምነት ተከታዮች ከሌላ ቦታ ተመልምለው መጥተው ከስደተኞች ኦርቶዶክሳውያን ጋር እንዲቀላቀሉና ፊት ተቀምጠው ፎቶ እንዲነሱ ተደርጓል። እውነታው ግን ከሦስት ቀበሌዎች ማለትም ከሚታና ጋዶ ቀበሌ ፣ከሰንጎ ያያ ቀበሌና ና ከሶዲ ሳዴ ቀበሌ ቤታቸው ፈርሶ ወደ ጎረቤት ወረዳ በ በቆጂ ከተማ የተሰደዱት 100% ኦርቶዶክሳውያን ናቸው። ይኽን ማስረጃ ማቅረብ እችላለሁ።
ሀ) ከሚታና ጋዶ 118 አባወራዎች (667 ኦርቶዶክሳውያን)
ለ) ከሰንጎ ያያ 65 አባወራዎች (ወደ 322ኦርቶዶክሳውያን)
ሐ) ከሶጂ ሳዴ 273 አባወራዎች( ከ1500 በላይ)።
ቤታቸውን ያሰረሱት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ወሀቢያዎችና ሙሉ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ነው። ልብ በሉ ይኽ ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በወረዳው ውስጥ ካሉ 37 ቀበሌዎች በሦስቱ ቀበሌዎች ብቻ ነው ሌሎች የተቀሩ 34 ቀበሌዎችን አያካትትም።ከመስከረም 5/2018ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2018ዓ.ም ብቻ የተፈጸመ ነው።በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀለ አንድም ሙስሊም የለም።ከፊት የተቀየጡት ሙስሊሞች ለፕሮፖጋንዳ ተመርጠው የመጡ ናቸው።በዚህ የሴራ ቅንብር ውስጥ የውስጥ የክልል፣የዞንና የወረዳ ባልሥልጣናት ተሳትፈውበታል።ጥቃቱን የሚመራው የመንግሥት መዋቅር ነው የምንለው ለዚህ ነው።
እንባቢው ያስተውል!!!
👉በእዚህ የ ኦርቶዶክሳውያንን ፍጅት የመካድ ሴራ ውስጥ ከፌዴራል እስከ ወረዳ ድረስ ያለው የመንግሥት መዋቅር ተሳታፊ ነው፣የ ኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተሳታፊ ነው፣የኦሮሚያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተሳታፊ ነው፣አባ ገዳዎች ተሳታፊ ናቸው።
👉 በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደረገው ፍጅት የሚቆመው ኦርቶዶክሳውያን በኅብረት ቆመው ራሳቸውን መከላከል ሲጀምሩ ብቻ ነው።
https://t.me/Eyo21e
7 366
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
• እፎይ ምን ይጠየቅ…?
"…ሰላም ተወዳጆች ሆይ…
"…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዛሬ ምሽት 1:00 ሰዓት ላይ የዘመድ ቴቪ በሳምንታዊው "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር" መርሀ ግብር ላይ ወንድም እፎይን በእንግድነት ጋብዞ ወደ እናንተ ያቀርባል።
"…መርሀ ግብሩን ሚልዮኖች
• በዘመድ ቴቪ በቴሌቭዥን
• በ zemedtv.com ዌብሳይት
• በዘመድ ቴቪ ራምብል
• በዘመድ ቴቪ ትዊተር (×) ሚልዮኖች ይከታተሉታል።
"…ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያና የዘመዴ ቲክቶክም በቀጥታ ስርጭቱን ያስተላልፋሉ።
• እርስዎም ማንም ይሁኑ ማን በሃይማኖትዎ እስላም፣ ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት፣ ኦርቶዶክስ የፈለጉትን ይሁኑ ብቻ ለወንድም እፎይ ቢቀርብልኝ የሚሉት ጥያቄ ካለ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በአዲሱ የእጅ ስልክ ቁጥሬ +4915216158791 ኋትስአፕ ላይ በመጻፍ መጠየቅ ይችላሉ።
• መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ ‼
• ስምምነ …?
7 366
+1
◈ኦርቶዶክስ በድንቡልቡል ደናቁርት አትወከልም፦
◈ክርስትና ከማንኛውም ምድራዊ ቅልውጥና የነጻች ቅድስት እውነት ናት።
◈ወዳጎረሷቸው የሚዞሩ ሰዎች አፍና ሆድ እንጂ ልብና መንፈስ የላቸውም።በነዚህ ድንቡልቡል መሀይማን ተስፋ የሚቆርጥ ክርስቲያን የለም።
◈ክርስትና የርቱዓን እና የልቡባን ሃይማኖት ናት።
◈ከሲኖዶሱ ጀምሮ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ብለው የተሰለፉ፤ መንግሥተ ሰማያትን በመንግሥተ ብልጽግና የቀየሩ፤ቀሚሳቸውን አንሰርትተው ሆዳቸውን አስፍተው የሚመላለሱ፤ነውር ጊጪ የሆኑ ብዙዎች ናቸው።
➻ጽላት የሚሠርቁ፣በጎሳ ደም የተጠመቁ፣በኦርቶዶክሳዊነት የሚሳለቁ፣በምእመናን መከራ የሚቦርቁ..አባቶች የሲኦል አጋፋሪዎች ናቸው።
◈በዚህ ጸረ ኦርቶዶክሳውያን አባት መሳዮች የሚደናገርም የሚደናገጥም ክርስቲያን የለም።
◈እስከ ጥግ ድረስ ገልበን የምናውቃቸው ድንቡልቡል ደና-ቁ_ርት ምእመኑን አይሸውዱትም።
◈እነዚህን ተስፋ የሚያደርግ አንዳንድ ምእመን ካለ በቁሙ የተጎዳ ስለሆነ ነፍስ ይማር እንለዋለን።
7 366
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+1
"እነ ኦቦ አፈወርቅም ወደ ግብርና ገብተው ስንዴ ወደውጭ export ሊያደርጉልን ነው አሉ ? " ።ደቀ መዝሙር መምህሩን አሰረ ፍኖት ተከተለ ማለት ይኽ ነው።
ነገ ግን ሰይጣን አሳስቶኝ ነው አያዋጣም።ነገ ለፍርድ የምትቁርቡበት እንጂ ንስሐ የምትገቡበት አይደለም።
7 366
Repost from Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
+5
"…ባለፈው ማክሰኞ ግንቦት 11/2018 ዓም ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ይጓዝ የነበረ አውቶቡስ ሰላሌ ሜዳ ላይ አሊዶሮ አካባቢ በኦሮሞ ነፃ አውጪ ሠራዊት በሚባሉት በሽመልስ አብዲሳ ፕላን ቢ ቡድን ታጣቂዎች የአውቶቡሱ ጎማ እና ሹፌሩ በጥይት ተመትቶ፣ የፊት መስታወቱንም በጥይት በሳስተው ከ40 በላይ የሚሆኑ መንገደኞችን አፍነው አግተው መውሰዳቸው ተዘግቧል።
"…በሌላ በኩልም በኦሮሞና በሲዳማ ብሔሮች መካከል በተነሣ የብሔር ግጭት ከሁለቱም ወገን በዜጎች ሕይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። ነገር ግን ሁሉም ዝም፣ ጭጭ ነው። ጭጭ አልኳችሁ።
"…የኦሮሞ ብልጽግና አፍ እንዲሆኑለት ያሰማራቸው እንኳን እሺ ድርጊቱ የመንግሥታቸውን ገፅታ ስለሚያበላሽ አይናገሩትም። ለታገቱትም ሆነ ለተገደሉት ድምፅ እንዲሆኑም አይጠበቅም። መቼም በአራቱም አቅጣጫ በር ተዘግቶበት፣ መውጫ መግቢያ አጥቶ፣ በራብ ለሚቆላው፣ ደሞዝ ተቋርጦበት፣ ነዳጅም ተከልክሎ ፍዳ እየተቀበለ በአምሳለ ሲኦል ለሚኖረው ለወገኑ ለትግራይ ሕዝብ አንዲት ነገር ትንፍሽ እንዳይል የፈረመው ወሴ ትግሬው አዶና*ም ድምፅ እንዲሆን አይጠበቅም።
"…የእኔ ጥያቄ በኦሮሞ ምድር አሊዶሮ ላይ የ6 ወር ሕጻንን ጨምሮ ዐማራ በመሆናቸው ብቻ ስለታገተው ሕዝብ እንዴት እንዲህ እንደዋዛ ዝም ይባላል? እሺ ሲዳማዎች እንኳን "በጌታቸው" አንድ ስለሆኑ ከደቡብ ከወላይታና ከጉራጌ፣ ከሀድያና ከከምባታ ለይቶ ጉራጌ ያለማትን ሃዋሳን ገንጥሎ ክልል አድርጎ ስለሰጣቸው፣ እንደ ባለውለታ ስለሚቆጥሩት ቢገድላቸውም፣ እንሰት ምግባቸውን ጨፍጭፎ ቢያስርባቸውም፣ ቤት ንብረታቸውን ቢያወድምባቸውም በኦሮሙማው ላይ ላይተነፍሱ ይችላሉ። ዐማራዎቹ ግን በየሚዲያዎቻቸው ጭምር ዝም ጭጭ ያሉት ለምንድነው? ከዐማራም የታገቱት በአብዛኛው ጎጃሞች ናቸውና እንዲህ ዝም ጭጭ ያሉት ምን ሁነው ነው? የአርሰናል ዋንጫ መብላት ከወገናቸው መታገት እንዴት እንዴት በለጠ?
• ብቻ ነገሩ ውስብስብ ያለ ነው የሚመስለው።
7 366
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+1
አለመጠርጠር ጅልነት ነው
ጀርመኖች 6 ሚሊየን አይሁዳውያንን ለመጨፍጨፍ ያመቻቸው ዘንድ አስቀድመው ደኅንነታችሁን ልናስጠብቅላችሁ ነው ፣ ዳግም ልናሰፍራችሁ ነው በማለት አታለው ከሕዝቡ ለይተው ካስወጧቸው በኋላ በተዘጉ ከተሞች ውስጥ ሰበሰቧቸው። ይኽን ካደረጉ በኋላ ነው ሠራዊት አሰማርተው የፈጇቸው ።
የሽርካ ኦርቶዶክሳውያን እጣፈንታ እንዲህ እንዳይሆን ያሰጋል።አለመጠርጠር ጅልነት ነው።ከወረዳው ተሰደው በቆጂ ከተማ የተጠለሉት እነዚህ ኦርቶዶክሳውያን ዳግም ወደ ወረዳቸው መመለሳቸው ይበል የሚያሰኝ ነው ነገር ግን በአንድ አከባቢ ላይ ብቻ ማስፈሩ አደጋ አለው።ዳግም መጥተው እንደማይጨፈጭፏቸው በምን እርገጠኞች እንሁን? ሥርዐቱ ኦርቶዶክስን የጥቃት ዒላማ አድርጎ በሚንቀሳቀስበት በዚህ ዘመን አለመጠርጠር ጅልነት ነው።መፍትሔ የሚሆነው የኦርቶዶክሱን ኅልውና ማስጠብቅና በራሱ ርስት ላይ እንዲኖር ማድረግ ነው።የሽርካ ኦርቶዶክሳውያን ሆይ ጥንቃቄ አይለያችሁ ።
7 366
Repost from Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ልጆችዋ ላይ እየደረሱ ያሉ ሥርዐታዊ፣መዋቅራዊና ርዕዮተ ዓለማዊ በደሎች ከብዙ በጥቂቱ
1) በ ቤተ ክርስቲያንቱ ላይ የውሸት ትርክት መፈብረክ
2) ከየትኛውም የሥልጣን ከመሪነት እርከን ማግለል
3) ኦርቶዶክሳውያንን ታርጌት ያደረገ ማኒፌስቶና ፖሊሲ መቅረጽ
4)ኦርቶዶክስ ጠልነት የ"አዲሲቷ ኢትዮጵያ "የፕሮጄክት አካል ይደረጋል
5) ኦርቶዶክሳውያን፦ነውርን፣በጅምላ መገደልንና መሰደድን ፣የዘር ፍጂትን ማለማመድ፣ሥርዐታዊ ውንቡድናን እንዲለማመዱ ማድረግ ፣ኦርቶዶክሳውያንን ማጥቃት እንደ ባሕል እንዲቆጠር ማድረግ
6)ቁጥር አምስት (5) ላይ የተዘረዘሩ በደሎችን ካለማመዱ በኋላ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ተግባራዊ ጥቃት ማድረግ
7) ቤተ ክርስቲያን በተቋም ደረጃ እንድትዳከም ማድረግ
👉ከሲኖዶስ ጀምሮ እስከ አንድ ግለሰብ ተወካይ ማሳጣት
👉ሁከት መፍጠር
👉መዋቅሮቿ ሁሉ በሰላዮች እንዲያዙ ማድረግ
👉ሳያስፈቅዱ በጀቷን መቀማት
👉 ጠንካራ ማኅበራትን ማዳከም ሽባ ማድረግ
👉ሲኖዶሲ ልጆቹን እንዳይታደግ
8) ከውስጥም ከውጭም ጯሂ ለምን ብሎ የሚጠይቅ እንዳይኖር ካደረጉ በኋላ ያለ ከልካይ ኦርቶዶክሳዊነትን
ማጥፋት
9) ኦርቶዶክሳውያን ላይ ሁለገብ ጥቃት ማድረስ፣ከሞት የተረፉት እንዲሳቀቁ የእዕምሮ እረፍት እንዳይኖራቸው፣ገብተው መውጣት ፣ወጥተው መግባት እንዳይችሉ ማድረግ
10) ኦርቶዶክሳዊው ማኅበረሰብ የሚበዛባቸው አከባባዊዎችን የጥቃት ዒላማ ማድረግ፣ዉክልና ያለው እንደ Emirates ያሉ ሀገራት የተሳተፉበት ተራዛሚ የማይቋጭ ጦርነት ማካሄድ ኦርቶዶክሳውያንን መጨድጨፍ፣ማሳነስና ማዳከም
11)በወጠጤ ፓስተሮችና ዉሸታም ሰዎች ስሟን እንዲያጠለሿት፣እሴቷን እንዲያናኑ፣የጥፋት ትንቢት እንዲተነብዩባት ማድረግ
12) ወሀቢስቶች(አክራሪ ሙስሊሞች) በማደራጀት ኦርቶዶክሳውያን ላይ የፕሮፓጋንዳ፣ የማኅበራዊ ሚዲያ፣አካላዊ ጥቃት እንዲያደርሱባት ማድረግ
13) ከሐዋርያት ሲኖዶስ የተለየ በኦርቶዶክስ ጠል ፖለቲካ የሚመራ የሰፈር ሲኖዶስ በመፈበርክ እልቂት መፈጸም ፣ኦርቶዶክሳዊ ኅብረትን መበተን
14) ቀድመው የነቁ በጉባኤ ቤት፣በማኅበራት፣በሰንበት ትምህርት ቤት፣በንግድ፣በፖለቲካ፣በትምህርት ተቋማት ወዘተ...ውስጥ ያሉ ልጆችዋን በማሳደድ ፣በማሳቀቅ፣በማሰርና በመግደል ኦርቶዶክሳውያን ድምፅ የሚሆናቸው እንዲያጡ ማድረግ
15)ቤተክርስቲያን በዚህ ሁሉ ስቃይ ውስጥ ሆና የማገገሚያ ጊዜ እረፍት እንዳተገኝ ያለማቋረጥ መነዝነዝ
መፍትሔው ምንድን ነው?
👉ሁኔታዎችን በትክክል መረዳት፦ትናንት የሆነብንን፣አሁን እየሆነብን ያለውን ፣ነገ ይሆንብን ዘንድ የታቀደውን
👉 ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ትስስር መፍጠር
👉ነጻ አውጪ አለመጠበቅ ሁላችንም የመፍትሔው አካል መሆን
👉አደናቂፊ እና አደንዛዥ የሴራ ሰበካዎችን ለይቶ እምቢ አልሰማም ማለት
👉እየጸለዩ መሥራት እየሠሩ መጸለይ
https://t.me/rete14
7 366
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+2
የጊዜ ጉዳይ ነው ቤተ ክርስቲያን ላይ ግፍ የሠራ ሁሉ ይዋረዳል።አላህም እግዚአብሔርም አንድ ናቸው እያሉ ሕዝቡን ግራ ሲያጋቡ የነበሩ በስርቆት ተይዘው ወደ ከርቸሌ ተወርውረዋል። እናዋርዳታለን ብለው ተዋረዱ።
