uk
Feedback
Exit Exam Preparation

Exit Exam Preparation

Відкрити в Telegram

Exit Exam በከፍተኛ ውጤት ለማለፍ የሚረዳ ፣ ከዚ በፊት የነበሩ የExit Exam ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያቸው የያዘ Quiz Bot @Exit_Exam_preparationbot

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Exit Exam Preparation

Канал Exit Exam Preparation (@exit_exam_prep) є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 51 270 підписників, посідаючи 3 372 місце в категорії Освіта та 617 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 51 270 підписників.

За останніми даними від 01 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 7 962, а за останні 24 години на -38, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 66.76%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 29.55% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 34 227 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 15 148 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 148.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Exit Exam በከፍተኛ ውጤት ለማለፍ የሚረዳ ፣ ከዚ በፊት የነበሩ የExit Exam ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያቸው የያዘ Quiz Bot @Exit_Exam_preparationbot

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 02 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.

51 270
Підписники
-3824 години
-1467 днів
+7 96230 день
Архів дописів
የጤና ተመራቂዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና ውጤት በቅርቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል። ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች (ከአንስቴዥያ በስተቀር)
የጤና ተመራቂዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና ውጤት በቅርቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል። ከሰኔ 17-19/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች (ከአንስቴዥያ በስተቀር) ውጤት በቅርቡ ይፋ እስከሚደረግ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሚኒስቴር ጠይቋል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች ማለፋቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። በአዲስ አበባ የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂ
+1
በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች ማለፋቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። በአዲስ አበባ የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁ ውጤታችሁን ለመመልከት 👇 https://aa.ministry.et/#/result በአዲስ አበባ ከተማ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና፣ ከ86 ሺህ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው ይታወሳል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

#ESSLCE #ExamProtocols የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከነገ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት ይሰጣል። ተፈታኞች ሊ
+1
#ESSLCE #ExamProtocols የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከነገ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት ይሰጣል። ተፈታኞች ሊይዟቸው የሚገቡ ➻ የመፈተኛ መግቢያ ካርድ ➻ የፋይዳ መታወቂያ/የቀበሌ/የትምህርት ቤት መታወቂያ ➻ እስክሪብቶ፣ እርሳስ እና ላፒስ የተከለከሉ ነገሮች ➻ ስልክ፣ ታብሌት፣ ስማርት ሰዓት፣ ካሜራ፣ ስማርት ጃኬት ➻ ያልተፈቀዱ ካልኩሌተሮች ➻ ማንኛውም አይነት ወረቀት፣ መጻሕፍት፣ የማስታወሻ ደብተር ተፈታኞች ዛሬ የሚሰጠውን አጠቃላይ የፈተና አሰጣጥ ገለጻ (Orientation) መከታተል ይጠበቅባቸዋል። የፈተና አሰጣጥ መመሪያዎችን መጣስ ከፈተናው መሰረዝ ባለፈ ከባድ ሕጋዊ ቅጣት ያስከትላል ተብሏል። የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

35 A+ ያስመዘገበው የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 35 A+ በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆ
35 A+ ያስመዘገበው የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 35 A+ በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ተማሪ አንቲ ምትኩ 3.99 አጠቃላይ ውጤት በማምጣህ በላቀ ማዕረግ የተመረቀ ሲሆን፤ 35 A+ 13 A እና 1 A- በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ በመሆን ተመርቋል። 👏👏 ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 679 ተማሪዎች ትናንት አስመርቋል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

#coc coc ማለፊያ ነጥብ በየ አመቱ ወጥ አይደለም ይህም የሆነበት ምክንያት ማለፊያ ነጥቡ ሚወሰነው modified angoff method በመጠቀም ነው modified angoff method ማለት በ
#coc coc ማለፊያ ነጥብ በየ አመቱ ወጥ አይደለም ይህም የሆነበት ምክንያት ማለፊያ ነጥቡ ሚወሰነው modified angoff method በመጠቀም ነው modified angoff method ማለት በጤና ሚንስትር በተመረጡ subject experts ለያንዳንዱ ጥያቄ ከተማሪዎች ብዛት ስንቱን ይመልሳል ሚለውን ግምት በ% የሚያስቀምጡበት ነው ለምሳሌ ሶስት የተመረጡ experts 100 የነርሲንግ ጥያቄን የወሰዱ ተማሪዎች ግምት ቢያስቀምጡ ለእያንዳንዱ ጥያቄ ከ100% ግምታቸውን ያስቀምጣሉ ለምሳሌ ለአንደኛው ጥያቄ ክብደት 85,80,80 በተከታታይ % በያስቀምጡ 85+80+80/3=0.816 የመጀመሪያው ጥያቄ ነጥብ ይሆናል የመጨረሻው ውሳኔ ሁሉም ጥያቄዎች በተመሳሳይ መልኩ ከተሰሩ በኋላ አማካይ ተወስዶ ማለፊያ ነጥቡ ይወሰናል። ለዚህ ማንም የአመቱን ማለፊያ ነጥብ አሁን ላይ በእርግጠኛነት ሊናገር አይችልም source moh exam development administration group የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

#MoH በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና #በሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት መታቀዱን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። ለዚህም በቅርብ ቀን
#MoH በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለወስዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና #በሐምሌ ወር 2018 ዓ.ም መጨረሻ ለመስጠት መታቀዱን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። ለዚህም በቅርብ ቀን ምዝገባ እንደሚጀመር ሚኒስቴሩ ገልጿል። በመሆኑም በሰኔ ወር የመውጫ ፈተና የወሰዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች ለብቃት ምዘናው የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃዎችን እንድታሟሉ እና ለምዝገባው ዝግጁ እንድታደርጉ ተብሏል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

የ Exit Exam ማዘጋጃ Telegram ቦታችንን ሲጠቀሙ የነበሩ ተፈታኞች! እኛ በስነስርዓት ያዘጋጀናቸውን Last Year Exit Exam፣ Model እና MCQ ጥያቄዎችን በመሥራት፣ እንዲሁም ዝር
+4
የ Exit Exam ማዘጋጃ Telegram ቦታችንን ሲጠቀሙ የነበሩ  ተፈታኞች! እኛ በስነስርዓት ያዘጋጀናቸውን Last Year Exit Exam፣ Model እና MCQ ጥያቄዎችን በመሥራት፣ እንዲሁም ዝርዝር ማብራሪያዎቹን በማንበብ ብቻ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቂ ዝግጅት በማድረግ ማለፍ ብቻ ሳይሆን የሚያኮራ ውጤት አስመዝግበዋል! ብዉ ተጠቃሚዎች actively  ብዙ ጥያቄዎችን በመስራት ፈተናውን አልፈው የምስጋና መልዕክት እየላኩልን ይገኛሉ። ያላለፋቹም ካላቹ ለቀጣይ ዙር በተጣሩ ፈተና ተኮር በሆኑ ጥያቄዎች ብዙ ነገሮችን አሻሽለን እናቀርብላቹሀለን። BOT :@Exit_Exam_preparationbot Channel : @Exit_Exam_prep

ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ ____ ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በ28 የፈተና ጣቢያዎችመሰጠት ጀምሯል፡፡ ስለሆነም ነገ 18/10/201
ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ ____ ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በ28 የፈተና ጣቢያዎችመሰጠት ጀምሯል፡፡ ስለሆነም ነገ 18/10/2018 ዓ.ም የፈተናው መርሃ-ግብር Nursing, Human Nutrition, Optometry, Physiotherapy እና Surgical Nursing ሙያ ላይ የተመዘገባችሁ ተመዛኞች ምዘናው የጠዋቱ ከ1:30 ሰዓት እንዲሁም የከሰዓቱ ከ7:30 ሰዓት ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ በፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ምዘናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ ____ ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የጤና ባለሙያዎች ብቃት ምዘና ፈተና በዛሬው ዕለት በ28 የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት ይጀምራል፡፡ ስለሆነም ዛሬ
ለብቃት ምዘና ፈተና ተመዛኞች በሙሉ  ____ ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የጤና ባለሙያዎች ብቃት ምዘና ፈተና በዛሬው ዕለት በ28 የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት ይጀምራል፡፡  ስለሆነም ዛሬ 17/10/2018 ዓ.ም የፈተናው መርሃ-ግብር Medicine, Public Health, Medical Laboratory Science, Midwifery, Medical Radiology Technology እና Pediatric and Child Health Nursing ሙያ ላይ የተመዘገባችሁ ተመዛኞች ምዘናው የጠዋቱ በ3 ሰዓት እንዲሁም የከሰዓቱ በ8 ሰዓት እንደሚጀመር አውቃችሁ ቀድማችሁ በፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ምዘናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን:: የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ቅሬታችሁን እስከ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ማቅረብ ትችላላችሁ። - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከመውጫ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች፣ ቅሬታችሁን ማቅረብ የም
ቅሬታችሁን እስከ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ማቅረብ ትችላላችሁ። - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከመውጫ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች፣ ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። ውጤት ያያችሁበትን ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/usernamepage በመጠቀም፣ በገፁ ላይ የሚገኘውን "Submit Complaint" የሚለውን አማራጭ በመጫን ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አስረድቷል። ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ 👇 ከሰኔ 17-23/2018 ዓ.ም ቅሬታ አቅራቢዎች በአካል ወደ  የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሔድ ሳይጠበቅባችሁ በኦንላይን ብቻ ቅሬታችሁን እንድታቀርቡ ተብሏል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ቅሬታዎን ያስገቡ! በመውጫ ፈተና ውጤትዎ ላይ ቅሬታ ካለዎት ቅሬታዎን በኦንላይን ያስገቡ፡፡ ➫ ውጤትዎ ያልተገኘ ከሆነ ➫ Disqualified የተባሉ ከሆነ ➫ ፊርማ ቢፈርሙም NG የተባሉ ከሆነ ➫
+2
ቅሬታዎን ያስገቡ! በመውጫ ፈተና ውጤትዎ ላይ ቅሬታ ካለዎት ቅሬታዎን በኦንላይን ያስገቡ፡፡ ➫ ውጤትዎ ያልተገኘ ከሆነ ➫ Disqualified የተባሉ ከሆነ ➫ ፊርማ ቢፈርሙም NG የተባሉ ከሆነ ➫ የተሳሳተ ጾታ ከመረጡና መሠል ቅሬታ ካለዎ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ የመውጫ ፈተና ውጤት ባዩበት ሊንክ (https://result.ethernet.edu.et) ላይ Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Complaint Category ከሚለው ይምረጡ፣ Description የሚለው ባዶ ቦታ ላይ ቅሬታውን አጠር አድርገው ይግለፁ፣ ስልክ ቁጥርዎን ያስገቡና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ያጠናቅቁ፡፡ የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

📣 Exit Exam ውጤት ተለቋል አሁን ላይ ሲስተሙ በመጨናነቁ ምክንያት  ዌብሳይቱ  not found ማለት ጀምሯል። ሰርቨሩ ዳግም መስራት እስኪጀምር በትግስት እንድጠብቁ አደራ እንላለን  ሁልጊዜም ውጤት ሲለቀቀ መሰል ችግሮች  እንደሚኖሩ  ይታወቃል ። Link = https://result.ethernet.edu.et የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ ሰኔ 16/2
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በመረጣችሁት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት የሚጠበቅባችሁ ሲሆን ወደ ፈተና ጣቢያ ስትመጡ የብሄራዊ መታወቂያ (National ID) እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print out ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡ የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

#ExitExamComplaints ሰሞኑን የተሰጠውን የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተናን ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል። በ
+2
#ExitExamComplaints ሰሞኑን የተሰጠውን የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተናን ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በ88 ማዕከላት እና በ287 የፈተና አይነቶች በተሰጠው ፈተና ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና የትምህርት ክፍሎች "ቅሬታ አለን" ያሉ ተፈታኞች ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የፋርማሲ ተማሪዎች "የፈተናው ጥያቄዎች አስቀድመው ተሰርቀው ለተወሰኑ ተማሪዎች ተሰራጭተዋል" የሚል ቅሬታ አቅርበዋል። ሌላው፣ በአንዳንድ የትምህርት ዘርፍ ውስጥ ካሉ ተፈታኞች ዘንድ የተነሳው ቅሬታ ፈተናው ከተቀመጠው የይዘት መመሪያ (Blueprint) ውጪ መውጣቱ ነው። ከዚህ ባለፈ መልስ የሌላቸው ስህተት የሆኑ ጥያቄዎች እንደነበሩ ተመሳሳይ ምርጫዎች መደገማቸውንም ተማሪዎች ጠቁመዋል። በአንዳንድ የትምህርት ዘርፎች ላይ የሰዓት እጥረት እንደነበር ተፈታኞቹ ጠቁመዋል። (ASTU) እና በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ያጋጠመው ተደጋጋሚ የመብራት መቋረጥ እንደነበርና በተለይም በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የጤና ኢንፎርማቲክስ ተማሪዎች ፈተና ወቅት መብራት አራት ጊዜ በመጥፋቱ ምክንያት የባከነው ሰዓት ሳይተካላቸው ቀርቶ፣ የ100 ጥያቄዎችን ፈተና በአንድ ሰዓት ውስጥ ብቻ እንዲያጠናቅቁ መገደዳቸውን ተማሪዎቹ ገልፀዋል። በተመሳሳይ እንደ አካውንቲንግ ባሉ የሂሳብ ስሌት በሚጠይቁ ዘርፎች ካልኩሌተር እና የማሰቢያ ወረቀት መከልከላቸው ጥያቄዎችን በግምት ለማጥቆር እንደዳረጋቸውና ተማሪዎቹ ለቲክቫህ አብራርተዋል። ነገርግን ለቀረቡ ጥያቄዎች እስካሁን የተሰጠ መልስ የለም። በተነሱት ጉዳዮች ላይ የሚያወጣውን መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

COC ተፈታኝ ለሆኑ በሙሉ share አርጉላቸው። ይሄ የቴሌግራም ቦት ከዚ በፊት የነበሩ የ COC ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያቸው የያዘ ነው። ጥያቄዎቹ ለመስራት አመቺ ስለሆኑ የትም ቦታ ሆነው
COC ተፈታኝ ለሆኑ በሙሉ share አርጉላቸው። ይሄ የቴሌግራም ቦት ከዚ በፊት የነበሩ የ COC ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያቸው የያዘ ነው። ጥያቄዎቹ ለመስራት አመቺ ስለሆኑ የትም ቦታ ሆነው መስራት ይችላሉ የተካተቱ Health Department 1, Pharmacy 2, Bsc Nursing 3, Medical Laboratory 👇 @Exit_Exam_Preparationbot

47 A+ ያስመዘገበችው ተመራቂ 👏👏 ተማሪ ሩት አባተ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እጅግ በላቀ ማዕረግ በዛሬው ዕለት ተመርቃለች። የ Electrical Power and Control Engi
+2
47 A+ ያስመዘገበችው ተመራቂ 👏👏 ተማሪ ሩት አባተ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እጅግ በላቀ ማዕረግ በዛሬው ዕለት ተመርቃለች። የ Electrical Power and Control Engineering ተማሪዋ ሩት አባተ፣ አጠቃላይ ውጤት 4.00 CGPA ውጤት በማምጣት ትምህርቷን አጠናቃለች። በዚህም የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች። በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ከወሰደቻቸው 60 ኮርሶች መካከል 47ቱን A+ እንዲሁም የቀሩትን 13 ኮርሶች A በማምጣት እጅግ የላቀ ውጤት አስመዝግባለች። "ለትምህርቴ ልዩ ትኩረት በመስጠቴ የላቀ ውጤት አምጥቻለሁ" የምትለው ሩት፣ በቀጣይ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቷን የመቀጠል እቅድ እንዳላት ለኢዜአ ተናግራለች። አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 1,387 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ አስመርቋል። የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።   የ2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች፦   224,234 ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች 287 ➫ የቅድመ-ምረቃ የፈተና ዓይነቶች 47 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የፈተና ዓይነቶች 88 የፈተና ማዕከላት >5000 ➫ የፈተና አስፈጻሚዎች     የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከ53 ሺህ በላይ ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከ53 ሺህ በላይ ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።   የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና አኃዛዊ መረጃዎች፦   53,620 ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች   61 የፈተና ማዕከላት >2,000 የፈተና አስፈጻሚዎች     የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ተጠናቋል፡፡ ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን እንደወሰዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች
+2
ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ተጠናቋል፡፡   ከ224 ሺህ በላይ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን እንደወሰዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡   ከነዚህ ተፈታኞች መካከል ግማሽ ያህሎቹ ፈተናውን በድጋሚ የወሰዱ (Re-sitters) መሆናቸው ተገልጿል፡፡   የመውጫ ፈተናው በ88 ማዕከላት እና በ287 የፈተና አይነቶች ተሰጥቷል። ከፈተናው አሰጣጥ ጋር የሰዓት እጥረት ችግር፣ ከፋርማሲ ፈተና ጋር የተያያዘ ችግር፣ ከብሉ ፕሪንት ጋር ያልተጣጣሙ ፈተናዎች መኖር እና ሌሎችም ቅሬታዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል። በአጠቃላይ የፈተና አሰጣጡ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የሚያወጣውን መግለጫ የምናደርሳችሁ ይሆናል። ምስል፦ አክሱም፣ እንጅባራ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች   የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep

#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና
#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና አስቀድሞ ተሰርቋል" ያሉት ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርጉ ቢቆዩም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ ገልፀዋል። ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን የጎደለው ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል። ጉዳዩ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማኅበር በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው ተፈታኞቹ ጠይቀዋል። ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተፈታኝ ተማሪዎች የቀረበውን ይህንን ቅሬታ መነሻ በማድረግ፣ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። ተጨማሪ ማብራሪያ እንዳገኘን የምናደርሳችሁ ይሆናል። ምስል፦ ተፈታኝ ተማሪዎች ወጥቷበማለት ያጋሩን የመልስ ማውጫ የ University  መረጃ የምታገኙበት  👉 @Exit_Exam_prep