uk
Feedback
Sele Enat Charitable Organization

Sele Enat Charitable Organization

Відкрити в Telegram

Sele Enat (SECO) is an indigenous, child-focused NGO in Ethiopia. Established in 2002, we empower vulnerable women and children.

Показати більше
298
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
+130 день
Архів дописів
አንድን ህጻን ስናበቃ፣ የማህበረሰባችንን የወደፊት ተስፋ እናለመልማለን። የእንክብካቤ፣ የትምህርት እና የድጋፍ እጆቻችንን ለነገው ተተኪ ትውልድ እንዘርጋ። ከስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በ
አንድን ህጻን ስናበቃ፣ የማህበረሰባችንን የወደፊት ተስፋ እናለመልማለን። የእንክብካቤ፣ የትምህርት እና የድጋፍ እጆቻችንን ለነገው ተተኪ ትውልድ እንዘርጋ። ከስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመሆን የልጆችን ህይወት በደስታ እና በተስፋ እንሙላ በጋራ ብሩህ ነገን እንገነባለን 💙💛 የአፍሪካ ህፃናትን ቀን ልናከብር 5 ቀናት ብቻ ቀረን ! #AfricanChildrenDay #SeleEnat #EmpowerAChild #TogetherWeCan #Advocacy ForChildren የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

አንድን ህጻን በፍቅር መንከባከብ፣ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት መስጠት እና እኩል እድል መፍጠር ማለት... ነገ የምታብብ፣ የበለጸገችና የጠነከረች አፍሪካን መትከል ማለት ነው። 🌳✨ ዛሬ በልጆቻችን ላ
አንድን ህጻን በፍቅር መንከባከብ፣ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት መስጠት እና እኩል እድል መፍጠር ማለት... ነገ የምታብብ፣ የበለጸገችና የጠነከረች አፍሪካን መትከል ማለት ነው። 🌳✨ ዛሬ በልጆቻችን ላይ የምንዘራው ዘር፣ ነገ ለመላው ማህበረሰባችን የሚተርፍ ትልቅ ጥላ ይሆናል። የአፍሪካ ህጻናት ቀን በጉጉት እየጠበቅን፣ ዛሬም እንደ ሁልጊዜው ለልጆቻችን ብሩህ ተስፋ በጋራ እንቁም! የአንድ ልጅ ፈገግታ ምክንያት ይሁኑ በአጋርነት ይደግፉን በበጎ ፈቃደኝነት ያግዙን አቅም በፈቀደ ይለግሱ የአፍሪካ ህፃናት ቀንን ልናከበር 6 ቀናት ቀሩን #AfricanChildrenDay #Day4 #NurtureToday #FlourishTomorrow #SupportChildren የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

እያንዳንዱ ልጅ በውስጡ ትልቅ ታሪክ፣ ብሩህ ተስፋ እና ሊገለጥ የሚጠባበቅ ታላቅነት አለው። ይህንን ታላቅነታቸውን ወደ ውጭ አውጥተው እንዲያበሩ ግን የእኛ እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ህጻናት የነገ ብቻ ሳ
እያንዳንዱ ልጅ በውስጡ ትልቅ ታሪክ፣ ብሩህ ተስፋ እና ሊገለጥ የሚጠባበቅ ታላቅነት አለው። ይህንን ታላቅነታቸውን ወደ ውጭ አውጥተው እንዲያበሩ ግን የእኛ እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ህጻናት የነገ ብቻ ሳይሆኑ የዛሬም ጭምር ውበቶቻችን ናቸው። ፍቅርን ስንሰጣቸው ደህንነት ይሰማቸዋል፤ ለትምህርትን  ስናግዛቸው አእምሯቸው ይከፈታል፤ በራሳቸው እንዲተማመኑ ስናደርጋቸው ደግሞ ነገን በድፍረት ይረከባሉ። አንድ ላይ በመሆን፣ የህጻናትን ብሩህ ተስፋ እውን ለማድረግ የበኩላችንን እንወጣ። ይደግፉ፣ በፈቃደኝነት ያግዙ፣ የአንድ ልጅ ፈገግታ ምክንያት ይሁኑ! ሰኔ 9 የአፍሪካ ህጻናት ቀን ልናከብር  የ 7 ቀናት ብቻ ቀረን  ⏳ #Advocacy #ChildDevelopment #SocialImpact #AfricanChildrenDay #SeleEnat #TogetherWeCan የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

የአፍሪካ ህጻናት ቀን ሊከበር 8 ቀናት ብቻ ቀሩት! "በትናንሽ ተግባራት፣ ትልቅ ለውጥ መፍጠር ይቻላል!" 🌟 የአፍሪካ ህጻናት ቀን (ሰኔ 9 / June 16) ሊከበር እነሆ 8 ቀናት ብቻ ቀርተዋል!
የአፍሪካ ህጻናት ቀን ሊከበር  8 ቀናት ብቻ ቀሩት! "በትናንሽ ተግባራት፣ ትልቅ ለውጥ መፍጠር ይቻላል!" 🌟 የአፍሪካ ህጻናት ቀን (ሰኔ 9 / June 16) ሊከበር እነሆ 8 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! እያንዳንዱ የምናሳየው ደግነት የምናስተምረው ትምህርት እና የምናደርገው ውይይት የልጆቻችንን ነገ ያደምቃል እኛ በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት በዋናነት በሦስት ምሶሶዎች ላይ እንሰራለን፡ 💙 መንከባከብ (Care) እያንዳንዱን ህጻን መጠበቅና መደገፍ 📚 ማስተማር (Educate) አእምሯቸውን መክፈትና ዕድሎችን መፍጠር። 💪 ማቅናት/ማብቃት (Empower) በነገው ተስፋቸው ላይ በራስ መተማመንን መገንባት በዚህ የቅድመ-ዝግጅት ጉዟችን ላይ ዛሬውኑ ይገናኙን በሃሳብ በጉልበት ወይም በበጎ ፈቃደኝነት የአንድን ህጻን የነገ ፈገግታ አብረን እንመልስ። ✨ አብረን፣ የተሻለ ነገን እንገንባ! #AfricanChildrenDay #Day2 #8DaysToGo #SmallActionsBigImpact #SeleEnat የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

የአፍሪካ ህጻናት ቀን ሊከበር 10 ቀናት ብቻ ቀሩት! 🌟 እያንዳንዱ ህጻን ልዩ ብቃት እና ችሎታ አለው። ግባችን ያንን እምቅ ችሎታ እንዲያወጡ መርዳት እና እንዲያበሩ ማድረግ ነው። ለአፍሪካ ህጻናት
የአፍሪካ ህጻናት ቀን ሊከበር 10 ቀናት ብቻ ቀሩት! 🌟 እያንዳንዱ ህጻን ልዩ ብቃት እና ችሎታ አለው። ግባችን ያንን እምቅ ችሎታ እንዲያወጡ መርዳት እና እንዲያበሩ ማድረግ ነው። ለአፍሪካ ህጻናት የወደፊት ተስፋ በጋራ እንቁም። #AfricanChildrenDay #10DaysToGo የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

እናትነት ወይም አባትነት የሚጀምረው ከየት ነው ከማህፀን ወይስ ከልብ ? በአሁን ሰዓት በፀደይ ሬድዮ ፀደይ ፕሮድካስት ፕሮግራም ላይ ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው የድርጅታችን Program Director አቶ
እናትነት ወይም አባትነት የሚጀምረው ከየት ነው ከማህፀን ወይስ ከልብ ? በአሁን ሰዓት በፀደይ ሬድዮ ፀደይ ፕሮድካስት ፕሮግራም ላይ ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው የድርጅታችን Program Director አቶ ትዕዛዝ አማረ እና የድርጅታችን Program Coordinator ወ/ሪ መቅደስ ታደሰ በቀጥታ ስርጭት ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው ከፀደይ ፕሮድካስት አዘጋጆች ጋር እየተወያዩ ይገኛል ታድያ ምሽት በMenahria f.m 99.1 እንዲሁም  በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት https://web.facebook.com/profile.php?id=61576215132054 የፌስቡክ ፔጅ በቀጥታ በምስል ተከታተሉን! ያላችሁን ሀሳብና ጥያቄ 0116392852 እና 0116393763 በቀጥታ ስልክ መስመር ማስተላለፍ ይቻላል። የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

እናትነት ወይም አባትነት የሚጀምረው ከየት ነው ከማህፀን ወይስ ከልብ ? ዛሬ በፀደይ ሬድዮ ፀደይ ፕሮድካስት ፕሮግራም ላይ ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው የድርጅታችን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ አብዱ እና
እናትነት ወይም አባትነት የሚጀምረው ከየት ነው ከማህፀን ወይስ ከልብ ? ዛሬ በፀደይ ሬድዮ ፀደይ ፕሮድካስት  ፕሮግራም ላይ ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው የድርጅታችን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ አብዱ እና የድርጅታችን ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ትዕዛዙ አማረ ስለ ጉዲፈቻ በሰፊው ከፀደይ ፕሮድካስት አዘጋጆች ጋር ይወያያሉ ። ታድያ ምሽት 1 ሰዓት በቀጥታ ስርጭት በMenahria f.m 99.1 እንዲሁም  በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት https://web.facebook.com/profile.php?id=61576215132054 የፌስቡክ ፔጅ በቀጥታ በምስል ይተላለፋል ተከታተሉን!ያላችሁን ሀሳብና ጥያቄ 0116392852 እና 0116393763 በቀጥታ ስልክ መስመር ማስተላለፍ ይቻላል። የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

ፎስተር ኬር ወይም የአደራ ቤተሰብ አንድ ህጻን ማደግ ያለበት የት ነው ? በተለያዩ ምክንያቶች የወላጅ ፍቅርና እንክብካቤ ያጡ ማረፊያ የሚፈልጉ ብዙ ልጆች አሉ ማሳደጊያ ተቋማት መጠለያ ሊሆኑ ይችላሉ ነገር ግን የቤተሰብን እቅፍ መተካት አይችሉም እዚህ ጋ ነው ፎስተር ኬር ወይም የአደራ ቤተሰብ  የሚለው የሚመጣው የአደራ ቤተሰብ መሆን ማለት አንድን ልጅ በህጋዊ መንገድ ለጊዜው ወደ ቤትዎ አስገብተው እንደ እራስዎ ልጅ ፍቅር ፣ እንክብካቤ እና ጥበቃ የሚሰጡበት የልብ ስራ ነው ህጻናቱ በቋሚነት በጉዲፈቻ እስከሚወሰዱ ወይም ወደ ወላጆቻቸው እስከሚመለሱ ድረስ የሚቆዩበት ነው የአንድን ልጅ ህይወት ለመቀየር የግድ ወላጅ መሆን አይጠበቅብዎትም በሩን እና ልቡን የሚከፍት የአደራ ቤተሰብ መሆን በቂ ነው  ፎስተር ኬር ወይም የአደራ ቤተሰብነት ማለት ወላጅ ለሌለው ልጅ ጊዜያዊ መጠለያ መስጠት ብቻ አይደለም ለዛ ህጻን ተስፋን መስጠት ማለት ነው ነው ዛሬ የምንከፍተው የአደራ በር ነገ የአገር እጣ ፈንታ የሚቀየርበት ትልቅ የፍቅር ማዕድ ነው አደራውን ለመቀበል ፍቅሩን ለመጋራት ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

🌙 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን የዒድ-አል አድሃ /አረፋ/ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🌙 እንኳን ለዒድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረስዎ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ፣ የራህመት
🌙 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን የዒድ-አል አድሃ /አረፋ/ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🌙 እንኳን ለዒድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረስዎ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ፣ የራህመት /የእዝነት/ እና የበረካ እንዲሆንልዎ ከልብ እመኛለሁ ይህ የተቀደሰ በዓል እርስ በእርስ የምንረዳዳበት፣ የተቸገሩትን የምናስብበት እና አብሮነታችንን የምናጠናክርበት እንዲሆን መልካም  ምኞታችን  ነው። 🌙 ዒድ ሙባረክ ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት🌙 የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

በጎ ፈቃደኝነት ማለት ትርፍ ጊዜን ማሳለፍ ብቻ አይደለም ለእናንተ ትንሽ የሚመስል ፍቅር ለሌላው ሙሉ ዓለም ነው ማህበረሰባችንን መለወጥ የሚጀምረው እኛ በምናደርገው ጥቃቅን መልካምነት ነው ከምንም በላይ ደግሞ ለአንድ ህፃን ፈገግታ ምክንያት መሆን የሚሰጠው የህሊና እርካታ በገንዘብ የማይገዛ ትልቅ ሀብት ነው                                                                                                                                                                                          የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

ህፃናትን በደስታና በአካል ብቃት ማሳደግ የነገዋን ጠንካራ ሀገር የመገንባት መሠረት ነው ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ሁልጊዜም ለህፃናት ሁለንተናዊ እድገትና ደህንነት ቅድሚያ ይሰጣል ይህ የመጫ
+3
ህፃናትን በደስታና በአካል ብቃት ማሳደግ የነገዋን ጠንካራ ሀገር የመገንባት መሠረት ነው ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ሁልጊዜም ለህፃናት ሁለንተናዊ እድገትና ደህንነት ቅድሚያ ይሰጣል ይህ የመጫወቻ ስፍራ ህፃናቱ ከአካዳሚክ እውቀታቸው ባሻገር በማህበራዊ ህይወታቸውና በፈጠራ ክህሎታቸው እንዲያድጉ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለን እናምናለን በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር እና በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት መካከል በተደረገው ዘላቂ ትብብር ለህፃናት ደስታና ስብዕና ግንባታ ትልቅ ሚና የሚጫወተው አዲስ የህፃናት መጫወቻ ስፍራ ተገንብቶ ተጠናቋል ይህ በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀው የመጫወቻ ስፍራ ግንቦት 08 ቀን 2018 ዓ.ም የወረዳው ከፍተኛ የሥራ አስፈፃሚዎች የስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት የሥራ አመራሮች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ይህ ፕሮጀክት ህፃናት ደህንነቱ በተጠበቀ እና ምቹ በሆነ አካባቢ እንዲጫወቱ አካላዊ ብቃታቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም እርስ በእርሳቸው እንዲቀራረቡ በማድረግ ረገድ የጎላ ድርሻ ይኖረዋል ለዚህ መልካም ስራ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከታችሁ ለስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጀት አመራሮች እና ለልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር  በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር እና ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ለህፃናት ደስታ የተሻለ  እድል በጋራ መስራታቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ። የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

በየቀኑ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ላይ የምናጋራቸውን ምስሎች ቪዲዮዎችና ታሪኮች ታያላችሁ የእኛ አላማ የድርጅታችንን ስራ እና የምናመጣውን በጎ ተፅዕኖ ለዓለም ማሳየት ነው ነገር ግን ኮንቴንት ስንቀርጽና ስንለቅ ሁልጊዜ ከምንም ነገር በላይ የምናስቀድመው አንድ ትልቅ ቀይ መስመር አለን እሱም የሕፃናት ጥበቃ በድርጅታችን የሴቭ ጋርዲንግ ፓሊሲ ዝም ብሎ በወረቀት ላይ የተቀመጠ ህግ አይደለም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለምንለቃቸው ቪዲዮዎች መመሪያችን ነው ይህ ፖሊሲ ለምን አስፈለገ ጥቅሙስ ምንድነው አንደኛ የልጆችን የወደፊት ህይወት እና ክብር ለመጠበቅ ዛሬ ሶሻል ሚዲያ ላይ የምንለቀው ምስል ወይም መረጃ አንድን ህፃን ለሳይበር ጥቃት ለስነ-ልቦና ጫና ወይም ለደህንነት ስጋት እንዳይዳርግ እንከላከልበታለን ሁለተኛ ፍቃደኝነትን ለማክበር ማንኛውንም ህፃን ከመቅረጻችን በፊት የልጆቹንና የወላጆቻቸውን ሙሉ እና ነጻ ፍቃድ ማግኘት ግዴታችን ነው ይህ ለሰዎች ያለንን ክብር ያሳያል እኛ የምንሰራው የሕፃናትን ህይወት ለመቀየር እንጂ የእነሱን ህይወት ለLike ወይም ለ View ብለን ለአደጋ ለማጋለጥ አይደለም ስለዚህ እናንተ ተከታታዮቻችን የተለያዩ የህፃናት ኮንቴንት ስናዘጋጅ ሆነ ስናጋራ ይህ ነገር በልጁ ላይ ምን ተፅዕኖ ያመጣል ብለን ሁልጊዜ ራሳችንን እንድንጠይቅ አሳስባለሁ ለህፃናት ደህንነቱ የተጠበቀ ዲጂታል አለም በጋራ እንፍጠር የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

" ወላጆች እባካችሁ ስልክ፣ ጌምን ለልጆች ዝም ማስባያ አታድርጉ። ዲጂታል ኦቲዝም መናገር እየቻሉ እንዳይችሉ እያደረገ ነው " - ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ልጆች ረጅም ሰዓት ስልክ ላይ ማሳለፋቸው በመና
+1
" ወላጆች እባካችሁ ስልክ፣ ጌምን ለልጆች ዝም ማስባያ አታድርጉ። ዲጂታል ኦቲዝም መናገር እየቻሉ እንዳይችሉ እያደረገ ነው " - ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ልጆች ረጅም ሰዓት ስልክ ላይ ማሳለፋቸው በመናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ መናገር እንዳይችሉ እያደረገ በመምጣቱ በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ " ለዲጂታል ኦቲዝም " እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የማህበሩ ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት፣ ልጆች ከስልክ ጋር ረጅም ጊዜ ማሳለፋቸው መናገር እየቻሉ እንዳይችሉ እያደረገ በመሆኑ፣ " ወላጆች እባካችሁ ስልክን፣ ጌምን ለልጆች ዝም ማስባያ መንገድ አታድርጉ " ሲሉ አስገንዝበዋል። ስልክ ላይ ረጅም ሰዓት በማሳለፋቸው የጂዲታል ኦቲዝም ተጠቂ በመሆን መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራችሁ የመጡ ልጆች አሉ ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ " አዎ! ቁጥሩን ይህን ያህል ለማለት ያስቸግራል፤ ግን የሚመጡ አሉ። ክልሎችም ላይ ስለምንሰራ ክልልም ላይ እንደዚህ አይነት ነገር አለ " ሲሉ ነግረውናል። ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ፣ ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘነትን እንደሚመረጡ አስረድተው፣ " ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው፥ ልጆች ከጌም፣ ከስልክ ጋር በተያያዘ ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው የተግባቦት ክፍተት እንዲፈጠር እያደረገ ነው " ብለዋል። በተፈጥሮ የሚመጣ ኦቲዝምም ቢሆን አንዱ ክፍተት የተግባቦት በመሆኑ በተፈጥሮ ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች የንግግር ችሎታ ላይ ክፍተት እንዳለባቸው ገልጸው፣ አሁን አሁን ደግሞ፣ " የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ማህበራዊ ግንኙነታቸው፣ ተግባቦት ላይ ትልቅ ክፍተት እየፈጠረ ነው " ሲሉም ተናግረዋል። " ምክንያቱም ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ከተጣዱ አያወሩም። ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ራሱ ዝም እያለ ነው የሚሄደው" ያሉት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፣ ስልክ ላይ ረጅም ጊዜ በማሳለፋቸው መናገር ያልቻሉ፣ በህክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም " ሆኖባቸው የተገኙ እንዳሉ ገልጸዋል። " ትልቁ ስራ የሚጠበቀው ወላጆች ላይ ነው። በተለይ ህፃናት ት/ቤት ከመግባታቸው በፊት ከ1 እስከ 4 ያሉት እቤት የሚውሉበት እድሜ ላይ ነው ትልቁ ሥራ መሰራት ያለበት " በማለትም የመፍትሄ ሀሳብ ጠቁመዋል። በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአረጋዊያንና ቤተሰብ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ሮብሌ በበኩላቸው፣ የቴክሎጂ አጠቃቀም የተስተካከለ ካልሆነ እንኳን በህፃናት አዋቂዎች ዘንድም በቤተሰብ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያስከትል አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም ወላጆች ልጄ ምን አጠና፣ ምን እያደረገ ነው ? የሚሉና መሰል ጉዳዮች ላይ ክትትል ያደርጉ እንደነበር አውስተው፣ " አሁን አሁን ግን ባልም፣ ሚስትም፣ ሌላውም ስልክ ከፍተው ጊዜያቸውን ያባክናሉ " ብለዋል። በተለይ የልጆች ስልክ አጠቃቀም ጨቅላ ህፃናትን ለዲጂታል ኦቲዝም ጭምር እያጋለጠ የሚገኝ ሲሆን፣ በውጭው ዓለም ያሉት ሀገራትም እንደ ቲክቶክ ያሉ ፕላት ፎርሞች አጠቃቀም ላይ እገዳና የእድሜ ገደብ እየጣሉ ናቸው፤ ከዚህ ረገድ በኢትዮጵያ የታሰበ ነገር እንዳለም አቶ ተስፋዬን ሮበሌን ጠይቀናቸዋል። አቶ ተስፋዬ በምላሻቸው፣ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ገደብ ለማስቀመጥ፣ "መነሻ ጥናት ያስፈልጋል። የተለያዩ ጥናቶች ለማድረግ አስበናል፤ በቀጣይ ጥናቱ ወደሚመራን ልንሄድ እንችላለን" ብለዋል። ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ደግሞ፣ "በኛም ሀገር ህግ ቢወጣ በጣም ጥሩ ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። "ምክንያቱም አሁን ቴክኖሎጂው ቀድሞናል፤ አጠቃቀሙን አልቻልንበትም። ሰው ቲክቶክ ለማየት ስልኩን አንሶላ ውስጥ ይዞ ነው የሚገባው፤ ከእንቅልፉ ሲነሳ ፀሎት ማድረግ ሲገባው ዓይኑን ሳይገልጥ ዲሶ ስልኩን ነው የሚያነሳው፤ ማህበራዊ ሚዲያ በጣም እየተቆጣጠረን ነው፤ የሚመለከተው አካል ትኩረት መስጠት አለበት" ሲሉ አሳስበዋል። በማህበራዊ ሚዲያ "የማይሆኑ መረጃዎች እየወጡ ማህበረሰቡን እያጋጩ ነው። ልጆቻችንም አጠቃቀሙን ስላልቻሉበት ስልክ ላይ ነው ስለሚውሉ አዕምሯቸውን እየተቆጣጠራቸው ነው" ብለው፣ "መንግስት እንደ ሌሎች ሀገራት ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ለኛም ገደብ ቢያበጅ መልካም ነው" ሲሉም መክረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia

እያንዳንዱ ልጅ አለኝታ የሚሆነው ቤተሰብ ያስፈልገዋል ዛሬ ግንቦት 7 ቀን (May 15) በዓለም አቀፍ ደረጃ የቤተሰብ ቀን ነው ዛሬ ሁላችንም ስለ ቤተሰቦቻችን ፍቅር ስለ ትስስራችንና ስለ ትዝታዎቻችን እናስባለን ነገር ግን በዚህች ሰዓት እናት/አባት ብሎ የሚጠራው ሲታመም የሚያቅፈው ሲደሰት አብሮት የሚፈነጥዝ የገዛ ደምና ስጋ የሌለው ስንት ህጻን እንዳለ ቆም ብለን የምናስብበትም ቀን ሊሆን ይገባል እያንዳንዱ ልጅ በቤተሰብ ፍቅር ውስጥ የማደግ ተፈጥሯዊ መብት አለው አንድ ህጻን ምግብና መጠለያ ብቻ ሳይሆን የነገ ተስፋውን የሚያለመልምለት አለው የሚለው በችግሩ ጊዜ የሚጠጋበት  ያስፈልገዋል ጤናማ ቤተሰብ የሌለው ልጅ የህይወት መሰረቱ የተናወጠ ነው ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ይሄንን ክፍተት ለመሙላት ሌት ተቀን እንተጋለን የወላጅና የቤተሰብ ፍቅር ያላገኙትን  እነዚህን የነገ ሀገር ተረካቢ ህጻናት ተቀብለን የተሻለ የልጅነት ግዜን አልብሰን ልክ እንደ እውነተኛ ቤተሰብ ሆነን እየደገፍናቸው እንገኛለን በእኛ ጥላ ስር ያሉ ልጆች ብቸኝነት እንዳይሰማቸው እንደማንኛውም ልጅ በደስታና በሙሉነት እንዲያድጉ የቻልነውን ሁሉ እያደረግን ነው ነገር ግን ይህ ስራ የእኛ ብቻ ሊሆን አይገባም ዛሬ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ቤተሰብ መሆን የግድ በደም መያያዝን አይጠይቅም ውድ የድርጅታችን ደጋፊዎች በጎ ፈቃደኞችና መላው ማህበረሰብ ለእነዚህ ልጆች ሁላችሁም ቤተሰብ ሁኗቸው በገንዘባችሁ በእውቀታችሁ በጊዜያችሁ አልፎ ተርፎም በመጎብኘትና ፍቅር በመስጠት የልጆቻችን ደጋፊ ሁኑ ዛሬን ለራሳችን ቤተሰብ ፍቅር ስንሰጥ ቤተሰብ ለሌላቸው ልጆች ደግሞ እኛ ቤተሰብ እንሁንላቸው ለንፁሃን ልጆቻችን ደጋፊ የምንሆንበት የፍቅርና የመተሳሰብ ቀን ይሁንልን  እናንተስ ዛሬ የልጆቻችን አለኝታና ቤተሰብ  ለመሆን ምን አቅደዋል ድርጅታችንን በመደገፍ የነገ ተስፋቸውን አብረን እንገንባ መልካም የዓለም አቀፍ የቤተሰብ ቀን የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

photo content

እያንዳንዱ ልጅ ከፍጥረቱ ጀምሮ አለኝታ የማግኘት የመታወቅ የመወደድ እና በቤተሰብ ደህንነት ውስጥ የማደግ ጥልቅ ፍላጎት አለው ደቦ አላያንስ ፎር ችልድረን ለሁለት ቀናት ስለ ወላጅ አጥ ልጆች ባዘጋጀ
+9
እያንዳንዱ ልጅ ከፍጥረቱ ጀምሮ አለኝታ የማግኘት የመታወቅ የመወደድ እና በቤተሰብ ደህንነት ውስጥ የማደግ ጥልቅ ፍላጎት አለው ደቦ አላያንስ ፎር ችልድረን ለሁለት ቀናት ስለ ወላጅ አጥ ልጆች ባዘጋጀው ስልጠና በተለይም ስለ ጉዲፈቻ በጥልቀት እና በስፋት የተወያየን ሲሆን እጀግ ሰፊ ሀሳብ ማግኝት ችለናል አለኝታ ጉባዬ ስለ ወላጅ አጥ ልጆች የቤተሰብ አስፈልጊነት ዳግም ለማጠናከር ማህበረሰብን ለማነሳሳት እና እያንዳንዱ ልጁ እውነተኛ አለኝታ እንዲያገኝ የሚነሳሳ መድረክ ሆኖል በድጋሚ ደቦ አላያንስ ፎር ችልድረን ስልጠናው ላይ ድርጅታችን ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት እንዲሳተፍ ስለጋበዛችሁ ከልብ እናመሰግናለን የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ አባቶቻችን ለሀገራችን ህይወታቸውን ሰጥተው ነፃነታችንን አውርሰውናል ዛሬ እኛም ይህንን ነፃነት ትርጉም ባለው መልኩ የምናከብረው የእነሱን
እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ አባቶቻችን ለሀገራችን ህይወታቸውን ሰጥተው ነፃነታችንን አውርሰውናል ዛሬ እኛም ይህንን ነፃነት ትርጉም ባለው መልኩ የምናከብረው የእነሱን አደራ ለቀጣዩ ትውልድ ስናስተላልፍ ነው በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጀት ውስጥ ያሉ ህፃናት እና ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች የእኛ የሁላችንም አደራዎች ናቸው የእነሱን ነገ ማሳመር ፍቅር መስጠት እና መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት የዘመናችን አርበኝነት ነው በዚህ ታሪካዊ ቀን ለእነዚህ ታዳጊዎች የፍቅር እጃችሁን በመዘርጋት አብረውን እንዲያከብሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

"እያንዳንዱ ሕይወት ዋጋ አለው"በሚል መሪ ቃል ለዓለም አቀፍ የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን ምክንያት በማረግ በዛሬው ዕለት በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ የእኛ ልጆች ኦቲዝም ማህበር
+7
"እያንዳንዱ ሕይወት ዋጋ አለው"በሚል መሪ ቃል ለዓለም አቀፍ የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን ምክንያት በማረግ በዛሬው ዕለት  በስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ የእኛ ልጆች ኦቲዝም ማህበር ጋር በድምቀት ተከበሮ ውሏል በዕለቱም  ከተለያዩ ተቋማት የመጡ የክብር እንግዶች የተገኙ ሲሆኑ ዕለቱን  አስመልክቶ የፖናል ውይይት ስለ ኦቲዝም በስፋት ተነስቷል በዚህ አጋጣሚ ከተለያዩ ተቋማት መጣችሁ የታደማችሁ እና ስለ እናት የበጎ አድራጎት ድርጅት የሚሰራቸውን ስራዎች የተመለከታችሁ እንግዶችን በልጆቻችን ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን #WorldAutismAwarenessDay2026 #AutismAndHumanity #SeleEnat #LoveAcceptance #Ethiopia #ኦቲዝም_ኃጢአት_አይደለም #ስለ_እናት #ሰብአዊነት የማኅበራዊ ሚዲያ አድራሻዎቻችን፦ Telegram |Facebook |LinkedIn |Instagram |TikTok |YouTube |X|Website 📍አድራሻ አዲስ አበባ ሳር ቤት ቫቲካን ኤምባሲ አካባቢ ዳማ  ትሬዲንግ ወይም ኢትዮጲካ ኮፊ ጎን ለበለጠ መረጃ +251 940656565 +251 921939393 ✨1000237880556 Sele Enat Mahiber CBE "የተሻለ የልጅነት ጊዜ ለሁሉም ህፃናት" A Better Childhood for every child

photo content