ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 936
Підписники
+1424 години
+3877 днів
+38530 днів
Архів дописів
ጀብደኛው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ለተከታታይ 6ወራት ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ ሰራዊት አስመርቋል።
በምርቃ ስነ-ስርዓቱ የአፋብን ሊቀመንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክት አስተላልፏል!!
ሐምሌ26/2018 ዓ.ም
===================================
√ጤና ይስጥልኝ እንዴት ሰነበታችሁ?
በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ፥ ቴዎድሮስ እዝ፥ 206ኛ ኮር፥ 34ኛ ክፍለጦር የመጀመሪያ ዙር ኮማንዶ ተመራቂዎች ከስድስት ወራት ጠንካራ ወታደራዊ ስልጠና በኋላ ለምርቃት በመብቃታችሁ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ፥እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ። እናንተ የምትመረቁበት ዛሬ ሃምሌ 26 ቀን በአማራ የህልውና ትግል ውስጥ እጅግ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀኖች አንዱ ነው። ሃምሌ 26-2015 አም የባሶ ሊበን፥ የደብረ ኤልያስ፥ የአዋበል፥ የአነደድ፥ የጎዛመንና የደብረማርቆስ ጀግኖች በተቀናጄ አኳኋን ተወርውረው ደብረማርቆስ ከተማን በቁጥጥር ስር በማድረግ የጠላትን መዋቅር ፍርስርሱን ያወጡበት ቀን ነው።
የፋኖው የተደራጄ የህልውና ትግል ድፍን ሶስት አመት ሆኖታል።በነዚህ ሶስት አመታት ውስጥ ለቁጥር የሚታክቱ አውደ ውጊያዎች ተከናውነዋል፥ ቃላት የማይገልፃቸው ጀግንነቶች ታይተዋል፥ ብዙ ግዙፍ ድሎች ተመዝግበዋል። ፋኖ በመላው አማራ ከሌሎች የጠላት ታጣቂዎች ውጭ የጠላትን 10 ሙሉ እዝ መክቶ ለወረራ በመጣበት ጉልበቱ እያንበረከከው ይገኛል።ይህ የታሪክ ገፆች የማያውቁት አዲስ ገድል ነው። በአማራ ልጆች ለአለም የታዬ አዲስ ክስተት ነው። በነዚህ አመታት አንድም ቀን ሳንዋጋ አንድም ቀን ሳናሰለጥን፥ አንድም ቀን ሳናደራጅ፥ አንድም ቀን ሳናስታጥቅ ውለን አናውቅም። ይህ እስከ ድላችን የሚቀጥል የቀን ተቀን ስራች ይሆናል።
ጓዶች ሆይ፦በአማራ ህዝብ ማህበረሰባዊ ታሪክ፥ በኢትዮጲያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ፥ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ወሳኝ የታሪክ ምእራፍ ላይ እንገኛለን። በዚህ ምእራፍ መቀመጥ አይቻልም። በዚህ ምእራፍ አይንን ለአንድ ደቂቃ እንኳን መክደን አይቻልም። በዚህ ምእራፍ መሳሳት አይቻልም። መቀመጥም፥ መተኛትም መሳሳትም ዳግሞ እድልና ይግባኝ የሌላቸው መጥፊያዎች ሆነዋልና።ስለዚህ ለወርቃማው አላማችን ሌት ተቀን እንሰራለን፥ በስሌት እንጓዛለን።እናሸንፋለን።ቢስማርክ እንዳለው "እውነት በያዝነው መሳሪያ የተኩስ ርቀት ውስጥ ትኖራለች"ና በፍጥነት ማሸነፍ ስላለብን እንበርታ።በድል እንገናኝ።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለኢትዮጲያ ህዝብ!
አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ሃምሌ 26-2018 አም
አርበኛ ዘመነ ካሴ
ሐምሌ 26/2018ዓ.ም
በደምና በአጥነት የተመሰረተው የፋኖ አንድነት የሁሉም ቤት ነው።
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም የአንድነት መግለጫ ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም ደግሞ የአመራር መዋቅሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። አንድነት ለምርጫ የማይቀርብ ጉዳይ መሆኑን የተረዳው መላ ሰራዊታችንና አመራራችን ከአንድ ወር በላይ በፈጀ ምክክር እና ውይይት ለደጋፊዎቹና ለህዝባችን ይፋ አድርጓል።
ነገር ግን አንዳንድ ፀረ አንድነት ግለሰቦች በሚፈጥሩት ኃላፊነት የጎደለው አካሄድ ዕልፍ ዋጋ የከፈለውን ታጋይ ግራ በማጋባት ተጠምደው ሰንብተዋል። ይህን ፀረ አንድነት አካሄድ በውል የተረዳው ሰራዊታችንና አመራራችን ወደ ትልቁ አንድነት ቤታቸው ተመልሰዋል።በመሆኑም ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር አመራሮች ሙሉ አሀዳቸውን በመያዝ አንድነቱን ተቀላቅለዋል።
በዚህ መሰረት መላ ሰራዊታቸውን ወክለው መግለጫ የሰጡ አመራሮች :-
1ኛ.አርበኛ ጌትነት አለባቸው== ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር ሰብሳቢ
2ኛ.አርበኛ ጌታቸው መኩሪያ == ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር የአፄ ኢያሱ ክፍለ ጦር ምክትል ሰብሳቢ
3ኛ.አርበኛ ጌታዬ እሱባለው==ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ሁለተኛ ሬጂመንት ሰብሳቢ
4ኛ.አርበኛ በላያ ጌቴ==ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ሁለተኛ ሬጂመንት ምክትል ሰብሳቢ
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ !
በማጀቴ ቀጠና በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት የቀበሌዎች መዋቅራዊ ማሻሻያ ተደረገ!!
ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ማጀቴ ቀጠና የስራ ስምሪት የተሰጣቸው ከፍተኛ አመራሮች፣ ከአጼ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር እና ከአጼ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር አመራሮች ጋር በመቀናጀት በማጀቴ ቀጠና በሚገኙ ሶስት ቀበሌዎች ላይ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት በማድረግ የቀበሌዎች መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጉን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፀ።
እንደ ኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፃ፤ ይህ የመዋቅር ማሻሻያና የህዝብ ውይይት መድረክ የተካሄደው በአግላ ማጀቴ፣ በአንቃር ኮበኮብ እና በማጀቴ 01 ቀበሌዎች ውስጥ ሲሆን፤ የህዝቡን ተሳትፎና ውሳኔ ማዕከል ባደረገ መልኩ በስኬት መጠናቀቁን አክሎ ገልጿል።
በመድረኩ ላይ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች አማካይነት ስለ ትግሉ ወቅታዊ ቁመና ሰፊና ዝርዝር ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ህዝቡም ጥያቄዎቹንና ሀሳቦቹን በነጻነት አፀባርቋል። ይሕ የተደረገው አዲስ የድርጅታዊ መዋቅር ማሻሻያ በአካባቢው አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን የበለጠ ለማፋጠን፣ የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ለማጠናከር እንዲሁም ከህዝቡ ጋር ያለውን ቀጥተኛ ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ መሆኑ ተብራርቷል።
የየቀበሌው ነዋሪዎች በበኩላቸው በተካሄደው ውይይትና በተደረገው የአመራር ምርጫ ላይ ያላቸውን ደስታ ገልጸው፤ ከአዲሶቹ የቀበሌ አመራሮች ጋር በመተባበር ለአካባቢው ልማትና ሰላም እንዲሁም ትግሉን ለማፋጠን በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
በሶስቱም ቀበሌዎች በህዝቡ ሙሉ ፍላጎትና ነጻ መራጭነት አዳዲስ የቀበሌ መዋቅር አመራሮች ተመርጠዋል። አዲስ የተመደቡት አመራሮችም ህዝቡንና አካባቢያቸውን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝቡ ፊት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የደጋው ንስር፦ የወታደራዊ ሳይንስና የስልት አርክቴክት ኮማንዶ ያለው አዱኛ!
በእድሜ ለጋ በምድር ላይ እሳት፤ በስልት የበሰለ የቁርጥ ቀን አንበሳና የፅናት አርማ! የውጊያ ጥበብና የወታደራዊ ሳይንስ ሊቅነት ኮማንዶ ያለው አዱኛ በዘመናዊ የውጊያ ሜዳ ላይ የሚታየው በስሜት ወይም በዘልማድ ሳይሆን፣ በጠለቀ ወታደራዊ ሳይንስ (Military Science) በተቃኘ አመራር ነው የ9 ዓመታት የብረት እድሜ፦ በለጋ እድሜው በቀድሞው መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያሳለፋቸው ረጅም ዓመታት፣ የወታደራዊ ዲስፕሊንና የፅናት አጥር አድርገውታል።
በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የተማራቸው ከፍተኛ ስልጠናዎች፣ ጦርን በጥበብ የመምራትና የማሸነፍ ምስጢርን አስጨብጠውታል።የስልትና የቴክኖሎጂ ቅንጅት የወሰዳቸው አጫጭር የቴክኖሎጂ እና የወታደራዊ ኮርሶች የመረጃ፣ የፍጥነት እና የቴክኖሎጂ የበላይነትን በውጊያ ላይ በጥበብ እንዲተገብር አስችለውታል።
ጠላትን በስልት በማስጨነቅና የውጊያ ሀይልን በትንሽ መስዋዕትነት ታላቅ ውጤት በማስመዝገብ ረገድ የዘመናዊ አዋጊነት ጥበብ መግለጫ ነው። በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ በመሪነት ሚና በብቃቱ፣በስልታዊ እቅድ አውጪነቱ እና በተግባር በተረጋገጠ ወኔነት ይበል የሚያስብል ነው!
የዘመቻ አርክቴክት (Operational Architect)፦ ውጊያን ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው በፅኑ እቅድ የሚያንጽ፣ የጠላትን ሰንሰለት አስቀድሞ በማንበብ አቅጣጫ የሚያስቀይር፣ እና በሚመራው ሰራዊት ውስጥ የሞራልና የፅናት እሳት የሚይዝ መሪ ነው። የተዋጊና የአዋጊ ቅንጅት፦ ጦርን ከኋላ ሆኖ ብቻ የሚያዝ ሳይሆን፣ የውጊያው ሁኔታ ሲጠይቅ ከፊት መስመር የሚሰለፍ፣ መሪነቱና ተዋጊነቱ የተጣመሩበት የቁርጥ ቀን ጋሻ ነው።
ታማኝነት፣ የጽናት ታሪክ እና የከፈለው ዋጋ ጀግንነት የሚለካው በውጊያ ሜዳ ብቻ ሳይሆን፣ ለቆሙለት አላማ በሚሰጡት ታማኝነት እና በሚከፍሉት መስዋዕትነት ጭምር እንጅ! ከጀግናው የአማራ ልጅ ፋኖ አርማ ከሆነው ከአሳምነው ጎን የወጣትነት እድሜውን ታማኝ አጃቢና የፅናት ምልክት ሆኖ ያሳለፈ፣ የእምነትና የጽናት ትርጉም ምን እንደሆነ በተግባር ያሳየ ወጣት ጦረኛ ነው።
በመከራ የታሸ የፅናት ውጤት፦ ገና በወጣትነት እድሜው የተቀበለው እንግልትና ያሳለፈው መከራ አልበገረውም፤ ይልቁንም እንደ ብረት አጋለው ለወገኑ ህልውናና ነፃነት በፅናት የሚቆም ብረት የመሰለ ክንድ አደረገው። የነፃነትና የተስፋ አርማ ወጣት ኮማንዶ ያለው አዱኛ ለወገኑ መከታ፣ ለጠላቶቹ ደግሞ እንቅልፍ የሚነሳ የትግል አንበሳ ነው። በለጋ እድሜው የጀመረው ተጋድሎ ለቆመለት ህዝብና አላማ ሙሉ ነፃነትና ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ የሚቀጥል የፅናት ጉዞ ነው!
በእውቀት የታጠቀ አዋጊ—በወኔ የተሞላ ተዋጊ፣ ለሀገሩና ለወገኑ የቆመ የቁርጥ ቀን የቴዎድሮስ አንበሳ የበላይ ጀግንነት የተላበሰው አንበሳ! እድሜና ጤና ይስጥህ፤ የቆምክለት ዓላማ ለድል ያብቃህ!
ሻሎም ለሃገሩ ዘማች! #Dave #Amhara
በቅርቡ አማራነት ውብት ብቻ ሳይሆን ጀግንነት ጭምር ነው በሚለው የሚገራርሙ ስራዎችን ይዘን እንመጣለን ይወዳጁን!!
https://www.facebook.com/share/185EWPxuje/
https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
እረፍት የለሹ ክፍለ ጦር ዛሬም በድልና በልዩ ዝግጅት ተገልጿል።
ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር:
የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ሃይል ተመስርቶ በመላዉ የአማራ ክልል ጦርነት በታወጀበት 3ኛ አመት የድል ቀን፣ የብልፅግና ስርዓት ለመጨረሻ ተወግዶ የአማራ ህዝብ ህልዉና የሚረጋገጥበት፣ ለመላዉ ኢትዮጵያዉያን ሰላም፣ ፍትህና ነፃነት የሚያሰፍን ስርዓተ መንግስት ለመመስረት የመጨረሻዋ ፉሽካ በሁለት ሰሜናዊ ግንባር በተነፋበት ዛሬ ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ከሻለቃ ሶስት ጋር ልዩ የተሃድሶ ዝግጅት አድርጓል።
ጀብደኛዉ 44ኛ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ዝግጅቱን በጎን እያካሔደ በሌላ በኩል ደግሞ ፋኖን ለመምታት ደፈጣ የያዙ ሁለት የጠላት ሀይልን ቲሊሊ ከተማ አቅራቢያ በመማረክ ድል ተጎናፅፏል።
አይነኬ መሆኑን እያስመሰከረ የቀጠለዉ የቀጠናዉ ልዕለ ሀያል ክፍለ ጦር ቀጣይ ለየት ያሉ ጀብዱዎችን ለመስራት በብልፅግና ትኩስ መቃብር ላይ ቁሞ በልዩ ድምቀት የሻለቃ ሶስት ተሃድሶ ፕሮግራምን አካሂዷል።
ድርጅታችን አፋብን ያለሰለሰ አለማቀፋዊና ቀጠናዊ ግንኙነቶች በትኩረት እያካሄደ፤ ስነ መንግስትንነት በክብር ለመረከብ ሌት ቀን እየሰራ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ባለበት በዚህ ልዩ ሰሃት ነበልባሉ ክፍለ ጦርም በልዩ የስነልቦና እና ወታደራዊ ዝግጁነት ማረጋገጡን ቀጥሏል።
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት፡
በላስታ ወረዳ ከገለሶት(07) ቀበሌ እና ከእርፋ (08) ቀበሌ ማህበረሰብ ጋር የአማራን የህልውና ትግል አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ!
በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የህልውና ትግል ይበልጥ ለማጠናከር እና የትግሉን ህዝባዊ መሰረት ይበልጥ ለማስፋት ያለመ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት በላስታ ወረዳ ከገለሶት(07)ቀበሌ ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል።
በዚህ ወሳኝ የንቅናቄና የውይይት መድረክ ላይ የትግሉ ከፍተኛ ወታደራዊ እና የሲቪል አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤
በዚህም አርበኛ አሰፋ መለሰ — የምኒልክ ዕዝ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ ፣አርበኛ ኢንጅነር አራጋዉ ያለዉ — የምኒልክ ዕዝ እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ ፣የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ከፍተኛ አመራሮች ፣የ19ኛ (እሽት) ክፍለ ጦር አመራሮች፣ እንዲሁም የላስታ ወረዳ ጊዚያዊ አስተዳደር ሲቪል መዋቅር አመራሮች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ላይ በተደረገው ውይይት፤ የአማራን ህዝብ ህልውናና ክብር ለማስጠበቅ በሚደረገው ትግል ውስጥ ማህበረሰቡ ለሰራዊቱ እያደረገ ያለውን ደጀንነትና ያልተቋረጠ ድጋፍ ይበልጥ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በሰፊው ተመክሮበታል።
ወታደራዊና የሲቪል አመራሮቹ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱ ከህዝቡ ጋር ያለውን የማይበጠስ ትስስር በማጠናከር የትግሉን የመጨረሻ ግብ ለማሳካት በከፍተኛ ሞራል ቆርጦ መነሳቱን አብራርተዋል።
በውይይቱ የተሳተፉት የገለሶት ማህበረሰብ አባላት በበኩላቸው፤ "ትግሉ የሁላችንም የህልውና ትግል ነው" በማለት፣ ከሰራዊቱ ጎን በፅናት በመቆም ስንቅ ከማቅረብና ሎጂስቲክስ ከመደገፍ ጀምሮ ለትግሉ የሚያደርጉትን ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
ይህ አይነቱ ህዝባዊ መድረክ በትጥቅ ትግሉ፣ በጊዜያዊ አስተዳደሩ እና በማህበረሰቡ መካከል ያለውን መግባባት ከማሳደጉም ባሻገር፤ የህዝቡን አንድነት በማፅናት ለትግሉ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ሐምሌ:- 26/ 2018 ዓ/ም
#አሳዛኝ_ዜና ❗❗
በንፁሃን ዜጎች እና በዕድሜ ጠገብ አባት እናቶች ላይ የሚደርስ ማንኛውም ዓይነት እንግልት መከራ ስቃይ እና የህይወት ህልፈት እጅግ የሚያዝን ልብ የሚሰብር ነው። ሰላማዊ ሁነው በዕድሜ የገፉ ታላላቅ ሰዎች ላይ የሚፈፀም ጥቃትና ግፍ በማንኛውም አካል ቢፈፀም ሰብዓዊነትን የሚፃረርና ተቀባይነት የሌለው ነው።
እንደነዚህ ያሉ አሳዛኝ ዜናዎችን መስማት እና ምስሎችን ማየት ምን ያህል ልብ እንደሚነካ እንደሚያሳዝን ይታወቃል ።ተወልደው ባደጉበት ሀገር በራሳቸው ቅየ ተደብድበው የሚገደሉ ወጣቶች ብዙ ናቸው ከቀን ወደ ቀን እየባሰ የመጣው ይህ ስርዓት ወጣቱን እና እድሚያቸው የገፉትን ከማንምና ከምንም ነገር ነፃ ሁነው በሰላም የሚኖሩትን አማሮች በግፍ እየደበደበና እየረሸነ መጣሉን ቀጥሎበታል።
በጎንቻ ሲሶ እነሴ ጠጅ ባህር ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ እኒህ የ65 ዓመት እድሜ የሆኑት አባት በአማራነታቸው ብቻ በአገዛዙ ቅጥረኛ በጭካኔ በጥይት ተደብድበው ህይዎታቸው አልፏል።
ነፍስ ይማር 😢
+1
አርበኛ ዘመነ ካሴ እና የአፋር ኡጉጉሞ አመራር ተወያዩ!
"እንዲያ ምን ይሻላል ጎጃም ሲሉት ጎንደር ገብቶ አስቸገራቸው… መቀሌ ነው ቢሉት መተከል ጉምዝ ከች ብሎ አገኙት… ኤርትራ ነህ ሲሉት ሸዋ ተገኘባቸው… ጎንደር ነው ቢሉት አፋር ተገኘባቸው… እንዲያ ምን ይሻላል እሳት እርመጥ ሆኖ አስቸገራቸው የአብዮቱ ፎርሙላ አርበኛ ዘመነ ካሴ!
ትግል የቦታወሰን የለውም፤ የዓላማ እንጂ! ዛሬ ታሪክ ሌላ ምዕራፍ እየጻፈች ነው፤ ድንበርና አጥርን ያፈረሰ፣ የህዝቦችን እውነተኛ ወንድማማችነት ያበሰረ አዲስ መንገድ እየተጠረገ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከአፋር ኡጉጉሞ ሰብሳቢ ጋር ባደረጉት ታሪካዊ ውይይት፣ ሀገራዊና ቀጠናዊ የፖለቲካ አሰላለፉን ሙሉ በሙሉ የሚቀይር አዲስ የጋራ መሰረት ጥለዋል!
ይህ ውይይት የፖለቲካ ንግግር ብቻ አይደለም፤ የህዝቦች የእጅ ለእጅ ተያይዞ የመቆም ጽኑ ማረጋገጫ ነው! እሳት አርመጥ የሆነው የለውጥ እሳቤ ዛሬ ከአፋር በረሃ እስከ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋ እና ወሎ ድረስ የአንድነትና የነጻነትን ጥሪ እያስተጋባ ይገኛል።
የለውጡ አቅጣጫ ግልጽ ነው የተበታተነ ትግል የለም፤ የጋራ አላማ እና የጋራ ድል እንጂ! Dave Amhara
እኛ አማራዎች ነን! ለሰው ልጅ ያለን ፍቅር የጠለቀ፣ ሰብእናችን ወሰን የሌለው፣ እጃችን ለደግነትና ለእንግዳ ተቀባይነት ሁልጊዜ የተዘረጋ ነው! ይህ ፍቅራችን የዘመናት እሴታችን፣ የማንነታችን መሠረት ነው፤ ለምን ቢሉ... አማራ ሆነን መፈጠራችን ራሱ የፍቅር፣ የጽናትና የክብራችን ታላቅ ምስክር ስለሆነ!
የታሪክ ድርሳናት አንድ በአንድ ይገለበጡ፤ ብራናዎችና የገድል መጻሕፍት በጥቅስና በስም ይነበቡ! ትናንት ሀገርን በደም አጥንታቸው ያቆሙ አባቶቻችን የጀግንነት ምዕራፍ ዛሬም በደም ስራችን ውስጥ እንደ ወንዝ የሚፈስ። ከነባሩ የታሪክ ስር የበቀልን፣ የሀገር ምሰሶና ማገዶ ሆነን የኖርን ጠንካራ ህዝቦች ነን።
እኛ የጀግናው አሳምነው የማይበገር ፅናትና ቁርጠኛ መንፈስ የተላበስን፣ በታላቅነቱና በጥበቡ የዐፄ ሚኒሊክ አጥንት የተገነባን የማይናወጥ ማህበረሰብ የትናንቱ የነፃነትና የጀግንነት ታሪካችን ዛሬም በነፃነት ትግላችን ውስጥ ህያው ሆኖ የሚነድ ባልምጡቅ አዕምሮ ያደለን ፍጡር ጭምር እንጅ!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ድርጅታችን ከጽኑ መከራና ግፍ ነፃ የሚወጣበት፣ የታሪካችን የመጨረሻው የነፃነትና የክብር ነፀብራቅ የሆነ በጊዜ ሂደት የምንጠፋ ሳንሆን ታሪክ የወለደን፣ ታሪክን ከትናንት ወደ ዛሬ፣ ከዛሬ ደግሞ ወደ ነገ አሻግረን ለወደፊቱ ትውልድ እንድናስረክብ ተፈጥሮ ራሷ በልዩ ጸጋ ያደለችን ፍጡራን ነን! ፅናታችን አይበገሬ፣ ጉዟችንም ወደ ሙሉ ነፃነትና ክብር ነው!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ አስተዳደር መምሪያ አርበኛ ኤፍሬም ባዬ ታናሽ ወንድምህ #Dave #Amhara
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የቀድሞው 106ኛ ኮር የአሁኑ 16ኛ ኮር የተሳካ ኦፕሬሽን በፋሽስቱ ሰራዊት ላይ ወስዷል!!
የቀድሞዋ 34ኛ ክፍለጦር በአድሱ አደረጃጀት 163ኛ ክፍለጦር በ2ኛ ሻለቃ በጋዞ ምድር የጠላትን ሰራዊት ዶግ አመድ ተደርጓል!!
ትናንት ሀምሌ 24/2018 ዓ/ም 2ኛ ሻለቃ ጋዞ እስታይሽ ዋሮ ተብሎ በሚጠራ ቀበሌ፡ሲቀሳቀስ በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ቅስፈታዊ ጥቃት በመክፈት በርካታ የጠላት ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰዉበታል።
ማህበረሰቦች 08 የመከላከያ ሰራዊቶች መሳሪያ ደርበው ወደ መጡበት ቀጠና ሲመለሱ አይተናል ያሉ ሲሆን፤ከዚህ ዜና ጋር ተያይዞ ሶስት የተደመሰሱና አስከሬናቸውን ሳያነሳ ጥሎ የፈረጠጠ ሲሆን፤04 ከባድ ቁስለኛ ተደርገዋል።
✔️ቁስለኞቹን በስትሬቸር ተሸክሞ ወደ ጉሬው ተመልሷል!!
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል የ16ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሶናል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሀምሌ 25/2018 ዓ/ም
+1
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ‼ፋኖን ለመያዝ ደፈጣ የጣሉ የብልፅግና ወንበር ጠባቂ ሰራዊት አባላት በአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ቲሊሊ ከተማ አቅራቢያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። #Dave #Amhara
