uk
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Відкрити в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Показати більше
2 936
Підписники
+1424 години
+3877 днів
+38530 днів
Архів дописів
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛኮር 74ኛ ክፍለ ጦር ግዙፍ የፋኖ ሐይል አስመረቀ ============================= ........ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ‎የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አዲሱ የምስራቅ አፍሪቃ የነፃነት አዕማድ ተስፋ ሰጪ ድርጅት መሆን ከጀመረ ከጥር 2018 ዓ.ም ወዲህ ፋኖ ጨለማና የፀሐይ ሐሩር የደጋው ውርጭ እንዲሁም የተራራ ውጣ ውረድ ሳይበግረው በፅናት በየጦር ሜዳው አኩሪ ጀብድ እየፈፀመ ይገኛል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦር ባለፉት 3ወራት ከ450 በላይ ሰልጣኞችን በመቀበል እና በማሰልጠን ከባድ አካባቢያዊ እና የተፈጥሮ ፈተናዎችን በመጋፈጥ ብቃት ያለው ወታደራዊ ሐይል አሰልጥኖ አስመርቋል። ‎ ‎በዚህ ዘመን አማራ መሆን ‎በየአድራሻው በድሮን ያስጨፈጭፋል፣በሜንጫ አንገት ይቀላል፣ ሐብት ንብረት ይዘረፋል ፣ታግቶ የህይወት አድን ግብር በየመንገዱ እስከ 4.5ሚሊዮን ድረስ ይከፍላል፣በየከተሞች ይፈናቀላል፣የአምልኮቤተ ክርስቲያን እና መስጊዶቹ በሰደድ እሳት እንዲቃጠል ይደረጋል፣በአጠቃላይ የአማራ የሆነ ሁሉ ከገፀ-ምድር ይወድማል ፤ይህ ሁሉ የሚፈፀመው በአብይ አህመድ ትዕዛዝ ነው። አማራውን ከመኖር ወደ አለመኖር መቀየር አለብኝ -"የጥንቱን አጥፋ የአሁኑን አጥቃ"በማለት የተነሳው ጨፍጫፊው ድንገቴው አብይ አህመድ ነው [upstart and the Architect of Horrific genocide in 21thc]. በኢትዮጵያ ምድር ሞት የተፈረደበት አማራ ከደረሰበት ቅርቃር ለማውጣት ሁሉም አማራ ከመሪ ድርጅቱ ጋር በታሪክ ገፅ የተገለጠ አስደማሚ ገድል እየፈፀመ ይገኛል። ‎ የአብይ ጀኔራሎች እነ መሐመድ ተሰማ ሆነ ብርሀኑ ጥላሁን የአማራን ትውልድ በከባድ መሣርያ ለመጨፍጨፍ በተሠማሩበት በዚህ ወቅት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛኮር 74ኛ ክፍለ ጦር በየሳምንቱ ጀብጅ በሩብ አመቱ አዲስ የሰለጠነ ሐይል በማስመረቅ ላይ ይገኛል። ‎ ‎የአማራው ትግል እንደሰደድ እሳት ያለማቋረጥ እየተዛመተ ነው፤ በዚህ አጋጣሚ የአማራን ህዝብ መከራ ለማመን የዘገየ አዕምሮ የተገጠመላቸው ድልብ(የዘገየ) እዕምሮ የተገጠመላቸው _ድልብ-ብአዴናዊያን በሆዳችሁ የተገዛችሁ ፀረ ህዝብ የአብይ አማራዎች በዕለተ አርብ መስጊድ ትሰግዳላችሁ፣እሁድ-ሰንበት ቤተ ክርስቲያን ታስቀድሳላቹህ፤ረቡዕ በአማራ ህዝብ ላይ ድሮን ታዘንባላችሁ። እመኑኝ በሰደድ እሳት /በማዕበል ትጠረጋላችሁ፤ወዬ በሉ ለልጆቻችሁ [ለባንዳ ልጆች]!!! እኛ የእውነተኛ የአማራ ልጆችን ይዘን እንሻገራለን ፣ወደ ነፃነት  ተራራ ጫፍ በአንድነት እንጓዛለን ። መከራ የክብር መጀመርያ ነው። ‎"ክርስቶስ መከራን ተቀብሎ ወደ ክብሩ መመለሱን አስተውሉ" ፤ ‎ከየኛ የኢትዮጵያዊነት የትንሳኤው ተራራ አማራ ነው። ‎ወደፊትም እንሰባሰባለን እንሰለጥናለን እንታጠቃለን ለፍትህ ለነፃነትና ለሐገር ልዕልና በፅናት እንታገላለን። ‎አዲስ ትውልድ፣ ‎አዲስ አስተሳሰብ፣ ‎አዲስ ተስፋ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ‎

የቋራው አንበሳና የጎንደር ውህደት ​ፀሐይ በጎንደር ሰማይ ላይ ወርቃማ ጨረሯን ስታፈስ፣ የፋሲለደስ ግንብ በግርማ ሞገስ ቆሟል። በዚህች ታሪካዊ ምድር ላይ ግን ከግንቦቹ የጸና፣ ከድንጋዮቹ የጠነከረ አንድ ትልቅ ታሪክ ሊጻፍ ጫፍ ደርሶ ነበር። ​ካሳ ኃይሉ በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ቴዎድሮስ የተባሉት ከአብራካቸው የወጣውን ራእይ በዓይነ ህሊናቸው ያሰላስላሉ። የእሳቸው ስነልቦና ከተራ ቁጣና ፍላጎት በላይ ነበር፤ እርሱም የማይናወጥ የእምነት፣ የጽናትና የከፍታ መንፈስ ነው። በልባቸው ውስጥ የተቀረጸው ትልቁ ሕልም የኢትዮጵያ አንድነት ሲሆን፣ የዚያ ታላቅ ሕልም መነሻ ደግሞ የጎንደር ህዝብ ሙሉ በሙሉ በአንድ ዓላማ ስር መሰብሰብ ነበር። ​በአንድ ወቅት በዛፎቹ ጥላ ስር ከተሰበሰቡት የጎንደር ታላላቅ መኳንንት፣ የሃይማኖት አባቶችና የጦር አበጋዞች ፊት ካሳ ኃይሉ ቆሙ። ዓይኖቻቸው እንደ እሳት ይበራሉ፤ ቃላቶቻቸው ደግሞ የሰዎችን ልብ የመስረጽ ልዩ ኃይል ነበራቸው። ​"እኔ ካሳ ነኝ!" አሉ በቆራጥነት፣ ድምፃቸው በሸለቆው ውስጥ አስተጋባ። "ፍላጎቴ የግል ዙፋን አይደለም፤ ፍላጎቴ የተቀደሰችውን ሀገራችንን ከተበታተነችበት መሰብሰብ ነው! ክፍፍል ውርደት ነው፣ አንድነት ግን የበላይነትና አሸናፊነት ነው! ​በዚያች ቅጽበት በቦታው የነበረው ሰው ሁሉ የእሳቸውን አሸናፊ ስነልቦና ተጋባበት። የነበረው ልዩነትና ቅሬታ እንደ ጢስ ተበተነ። የታላቋን ሀገር ትንሳኤ ያዩት የመንደሩና የከተማው ህዝብ በአንድ ድምፅ፦ "አንድ ነን! ከጎንህ ነን!" እያሉ ጮሁ። ​ያ ቀን የጎንደር አንድነት በይፋ የተከናወነበት፣ የበላይ አሸናፊነት የታየበት ታሪካዊ ምዕራፍ ሆነ። ​ካሳ ኃይሉ የህዝቡን አንድነትና ፍቅር ሲያዩ ፈገግ አሉ፤ በልባቸውም አወቁ የተበታተነችው ሀገር የምትሰበሰብበት፣ የኢትዮጵያም አዲሱ ምዕራፍ በእውነት የተጀመረው በዚሁ በጎንደር ውህደትና አሸናፊነት ነበር ። በመጨረሻም ሆነ ተከናወነ የእናታለም ጎንደር ልጆች የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ የእናንተ አንድነት ከአባቶቻችሁ የተማራችሁት ውብና ማራኪ የአማራ ህዝብ የመኖር ነፃነቱን የሚያሳይበት አዲሱ ምዕራፍ ነው ክበሩልኝ! #Dave #Amhara

ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​በዛሬው ዕለት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቋ ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ የበርካታ ወገኖቻችን ሕይወት ማለፉና ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ለአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እንዲሁም ለጠቅላላው ሕዝባችን ጥልቅና እጅግ ከባድ የሆነ ሐዘንን ፈጥሯል። ​ይህ ታሪካዊና ቅዱስ ስፍራ የብዙዎች መጽናኛና የጸሎት ቦታ በሆነበት ቅጽበት ደረሰ የተባለው ይህ አሰቃቂ አደጋ፥ የ14 ወገኖቻችንን ሕይወት ቀጥፎ የሄደ፣ 5 ወገኖቻችንን ለከባድ አካል ጉዳት እንዲሁም 2 ወገኖቻችንን ለቀላል ጉዳት የዳረገ ልብ ሰባሪ ክስተት ሆኗል። የወገኖቻችን ድንገት ማለፍና መጎዳት ልብ ሰባሪ ክስተት ነው። ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማውን መራርና ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለገዳሙ ማህበረሰብ እና ለሙላው ሕዝባችን መጽናናትን ይመኛል። ​ልዑል እግዚአብሔር የሞቱትን ወገኖቻችንን ነፍስ በአብርሃም፣ በይስሐቅና በያዕቆብ አጠገብ በገነት ያኑርልን፤ በጽኑ ተጎድተው በሕክምና ላይ የሚገኙትን ወገኖቻችንን ፈጣሪ በቸርነቱ ቁስላቸውን ይዳብስልን፣ ፈጣን ምህረቱንም ያውርድላቸው። ​አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ታጋዮች ስብስብ ያለበት ነው  ።            አማራነት የጀግንነትና የብዙ ባለታሪክ ባለቤትነት ነው ።                          አማራ ያሸንፋል                ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም

ሐምሌ 27/2015 ዓ/ም ታላቅ የጀብድ ቀን (የተምጫ ጀብድ) ደምበጫ በኢንጂነር ክበር ተመስገን ልጆች ተከብሮ ዉሏል። ፶አለቃ ደጉ ፋንታሁን የኢንጂነር ክበር ተመስገን መስራችና አደራ ተቀባይ  በመድረኩ የሚከተለዉን መልዕክት አስተላልፏል። ።።።።።።።።።።። የተከበራችሁ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች የተከበራችሁ የሀይማኖት አባቶች የተከበራችሁ የሀገር ሽማግሌዎች የተከበራችሁ የሀምሌ 27/2015 ዓ.ም የተምጫ ድል ትንቅንቅን የመራችሁና የተሳተፋችሁ አርበኞች የተከበራችሁ የሀምሌ 27/2015 ዓ.ም የታሪክ ነጋሪና ዘካሪ የትግሉ ፈርጥ የኢንጅነር ክበር ተመስገን እንቁ የፋኖ አባላት ክቡራንና ክቡራት የአማራ ህዝብ በዓለም ታሪክ ጥንታዊ ስልጣኔና ሀገረ መንግስት ከገነቡ ህዝቦች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል ።የአማራ ህዝብ  ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ቋንቋ ፤  ቁጥር ፤ የሰከንድና የደቂቃ መቁጠሪያ :የቀንና የአመታት መቁጠሪያ ሥርአት  ፤ ባህል ፤ ወግ፤ ሀይማኖት ፤ ዜማ ፤ ሥርአተ መንግስት ፤ - ቋንቋ ስንል ግዕዝ እና አማርኛ - ቁጥር ስንል አንድ ሁለት ሶስት ወይም አሀዱ ክልኤቱ - የሰከንድና የደቂቃ መቁጠሪያ ስንል - የቀንና የአመታት ስንል አሁድ ሰኞ ፤ ሳምንትና ወር ማለትም መስከረም ጥቅምት - ባህልና ወግ  ስንል አለባበስ አመጋገብ  አነጋገር የማህበረሰብ መስተጋብር የጋብቻ የማህበረሰብ  መረዳዳታ ፤ - ሀይማኖት ስንል የፈጣሪን ፈጣሪነት የሰውን ተፈጠሮነት እንዲሁም የሰውን አምላኪነትና የፈጣሪ ተመላኪነት እምነትና አምልኮት ከነ ሥርአቱ - ዜማ ስንል የቅዱስ ያሬድን ሰማያዊ ህብረ ዝማሬ - ሥርአተ መንግሥት ስንል ሀገረ ገዥነትን ፤ ሀገር የምትመራበትን ጥበብና  ሀገረ መንግስት ግንባታን ለአለም ያስተማረ ወርቅ ህዝብ ማለታችን ነው ! - ይሁን እንጅ የአማራ ህዝብ በአለፉት 50 አመታት በተፈጠረው አማራ ጠል ትርክት የተነሳ ህልውናው አጣብቂኝ ውስጥ ይገኛል ። የአማራ ህዝብ   ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ና ፓለቲካዊ ጥያቄዎችን ለአመታት  በሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱት ሲጠይቅ የቆየ ቢሆንም ለረጅም አመታት ሥርአተ መንግስቱን ተቆጣጥሮት የቆየ ሥርአተ መንግስት አማራ ጠል በመሆኑ የተከበረውን ህዝብ መንግስታዊ መዋቅር ባለው አካሔድ መግደል ፤ማሳደድ እና ሀገር ፤ ታሪክ ፤ ሀይማኖት ፤ ወግና ባህል አልባ ለማድረግ መጠነ ሰፊ ግፍና በደልን ሲያስተናግድ እንዲኖር ተደርጓል ። ይህንን እልቆ መሳፍርት የሌለው የአማራ ህዝብ በደልና ግፍ በሰላማዊ መንገድ የማይፈታና የአማራ ህዝብ ከመጥፋት መታደግ የማይቻል በመሆኑ እንቁ የአማራ ወጣቶች ምሁራን እና የአማራ ህዝብ ራሱን በማደራጀት ወደ ነፍጥ ትግል እንዲገባና ህልውናውን እንዲታደግ ተገዷል ። በዚህ መሰረት  የተከበረው ሀገረ ሰሪና ሥርአተ መንግስት አስተማሪው አማራ  ከአማራ ጠል ከአብይ መራሹ ብልፅግና ጋር የብረት ትግል መፋለምን ከጀመረ  3 አመታትን ያሳለፈ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው ።        ተምጫ ወንዝ በዛሬው ዕለት የምናከብረው ሐምሌ 27 ቀን  የአማራን ህዝብ እጨፈጭፋለሁ ሴቶችን እደፍራለሁ አዛውንትን አዋርዳለሁ ሀይማኖትን አጠፋለሁ ብሎ በእብሪት  ተወጥሮ እየተግተለተለ የመጣን የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት  የአማራን ህዝብ ከተፈጠረበት የመጥፋት አደጋ ለመታደግ  በትላንቱ የነበላይ ዘለቀና የታላላቅ አርበኞች አባቶቻቸው ሀገርና ህዝብ አይደፈሩም ወኔና  የጀግንነት መንፈስ የተሞሉ የደምበጫ ጀገኖች አፈር ከድሜ የከተቱበትና የብልፅግና የግል ጠባቂ ነኝ ባዩ 72 ክፍለ ጦር ሰራዊት ሙሉ ለሙሉ የተደመሰሰበት የተምጫ ወንዝ ታላቅ የጀብድ እና የአማራ አሸናፊነት ሥነ ተፈጥሮ የተገለፀበት የአሸናፊነት በዓል ነው ። ይህንን ሐምሌ 27 የአሸናፊነት ዝክረ  ታሪክ እንኳንስ አብይና የመከላከያ ተቋም ይቅርና የእኛዎቹ የእንግዴ ልጆች የአማራ ባንዳዎች ሊሰሙትና ሊያስታውሱት የማይሹት የአገዛዙ ብልፅግና  የታሪክ ስብራት የአማራ ህዝብ የኩራት ቀን ነው  ።         ተምጫ ወንዝ ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም  ሙሉ መካናይዝድ የታጠቀ የኼውም  Bm ፤ ዙ-23 ፤ ሞርተር   ዲሽቃ የታጠቀ የብልፅግና መከላከያ 72ኛ ክፍለ ጦርን  የበላይ ትንፋሽ የአባቶቹ ልጆች የደምበጫ ፋኖ ኩራት የአማራ ህልውና የትግል ጎህ ቀዳጆች በ34 የነፍስ ወከፍ መሳሪያና በ3 መትረይስ የደመሰሱበት : አንድ ዙ -23፤  አንድ ኦራል ፤  5 ሞርተር  4 ዲሽቃ ፤ 16 መትረየስ ፤7 ስናይፐር በቁጥር የማይገለፅ አብይ ዋጋውን ያልከፈለው በዱቤ የተቀበለው ራሽያ ሰራሽ ጥቁር  የነፍስ ወከፍ ነፍጥ  ሙሉ ጠላትን ሰርዘን የተቀበልንበት ዕለት ነው ።         ተምጫ ወንዝ ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ሰብረነዋል ፤ አደናግረነዋል ፤አወዛግበነዋል የተባለው አማራ መሰበር መደናገር መወዛገበን ለጠላቶቹ በተግባር ያስተማረበት አራት ኪሎን ቅስሙን የሰበረበት ጠላቶቻችንን ያወዛገብንበትና ያደናገርንበት ፤  ከአምላኩ ጋር በፀሎቱ የሚነጋገረው ህዝብ ልክ እንደኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት ዕለት ከቀኑ 7:00 እስከ 10:00 ቀን የጨለመበት ፤  የሀይማኖት አባት ቄስና መነኩሳትን የገደለ የደፈረ ቤተክርስቲያንን ያወደመ ፤  መስጊድ ያፈረሰ ኢትዮጵያ ጠል የሆነ ታሪክ አልባው መከላከያ እንደቅጠል የረገፈበት ፤ 530 በላይ የአባታቸው የብርሀኑ ጁላ ልጆች እጅ ወደላይ ብለው በማዕበል የተማረከበት ፤ ነፍጥ እንደ እንጨት ተለቅሞ የታሰረበት ፤ በደምበጫ አማራ ህዝብ ላይ ሞርተር ፤ ዙ-23 ፤ BM  ዲሽቃና መትረይስ እንደ በረዶ የዘነበበት የአማራ የአልደፈር ባይነትና የድፍረት የጀግንነት ስነ ልክ ለአለም የተመሰከረበት የአሸናፊነት ምስክር ቀን ነው ።             ተምጫ ወንዝ ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ጀግኖች እነ ልዑል በርሔ  ፤ ፈቃዴ ቢተው ፤  እሱባለው ይሁኔ  የተሰውበት ፤  የአልሞ ተኳሾች 10 አለቃ ድረስ አላምነህ ፤የ10 አለቃ  ታደሰ ስመኝ  ፤ የሁነኛው  አንተነህ ፤  የ10 አለቃ እሱባለው ፤ የመዘመር ዘመኑ ፤  የአለባቸው የተበጀ ማተቤ የነይርሳው ደምስ ጀብደኝነት የተመሰከረበት የየበርሃ የደብረ ቀለሞና የየወበሽ በመከላከያ ጩኸት የተሞሉበት ዕልፍ ጀግኖች የተፈጠሩበት ዕልፍ ታሪክ የሚነቀስበት ፤ ዕልፍ ባንዳዎች የተሸኝበት የትግላችን የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበት በዓላችን ነው ። በመጨረሻም ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም በትግል ታሪካችን የምናተኩርበት አንኳር ነጥባችን ይሁን እንጅ የደምበጫ ፋኖ የትግል መነሻ ከ2011 ዓ.ም  የአማራ ወጣቶች ማህበር ጀምሮ   ለአለፉት 7 እና 8 አመታት ለአማራ ዘርፈ ብዙ የህልውና ትግል ሲያደርግ የቆየ  መሪና የትግል መሰረት ያለው የአማራ ትግል መስራች ነው የደምበጫ ፋኖ ትግል ተመስገን ቤዛ  ፤ ኢንጅነር ክበር ተመሰገንን ፤ ተሰማ ጌትነት ፤ ሽታሁን ዘበናይ ፤ ሳጅን ተፈራ ፤ አባ የሻነው ፤ ጥላሁን አርጋው ፤ መዘመር ዘመኑ ፤ መሰረት ዳኛው ፤ መምህር ላቃቸው ፤ መምህር ተሾመ የመሰሉ ብዙ እልፍ ጀግኖችን የገበረ ዛሬ ለአማራ ለክብሩ የሚመጥን ታሪክን የሚሰሩ  ብዙ እልፍ ጀግና ፋኖዎችን ያፈራ በአባታቸው በኢንጅነር ክበር ተመስገን የሚምሉና ለአማራ ህዝብ ነፃነት የሚሽቀዳደሙ ፈጥኖ ደራሽ ስመጥሮች ያሉት የአማራ ፋኖ ቴወድሮስ ዕዝ  አካል ሆኖ ያለና ወደፊትም ኢትዮጵያን እስከምንረከብ በፅናት የሚታገል ለ3 አመታት ተዘርዝሮና ተነግሮ የማያልቅ የፊት ለፊት አውደ ውጊያዎችን በድል የተወጣ መርህ አክባሪ ድርጅት መስራችና ድርጅት ጠባቂ  የእንቁና ውድ

አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ‼ የአማራ አብዮት የተጀመረበት 3ኛ ዓመት መታሰቢያ በቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለ ጦር በላይ ዘለቀ ሻለቃ በድምቀት ተከበረ። ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም በደብረ ኤሊ
+2
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ‼ የአማራ አብዮት የተጀመረበት 3ኛ ዓመት መታሰቢያ በቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለ ጦር በላይ ዘለቀ ሻለቃ በድምቀት ተከበረ። ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም በደብረ ኤሊያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም መነኮሳትን የጨፈጨፈውና ገዳሙን ያወደመው የጠላት "72ኛ ክፍለ ጦር"፤ በማቻከልና በደንበጫ ሕዝብ ብርቱ ክንድ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰበት ዕለት ነው። በዚህ ታሪካዊ ውጊያ 1 ዙ-23፣ 5 ዲሽቃ፣ 4 ሞርታር፣ 41 ብሬን፣ 13 ስናይፐር እና ከ3000 በላይ ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ከሙሉ ሎጅስቲክሱ ጋር የተማረኩበትና የጠላት የሰው ኃይል የደመሰሰበት ወቅት ነበር። የበላይ ዘለቀ ሻለቃ ይህንን የድል በዓል በድምቀት ስታከብር፣ ለቀጣይ ግዳጅና ተልእኮ ያላትን ወትሯዊ ዝግጁነትም በድጋሚ አረጋግጣለች።

የላስታ ወረዳ ጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር ዓመታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ በማድረግ መዋቅራዊ ሪፎርም አካሔደ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር ስር ከሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች መካከል አንዱ የሆነው የሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላስታ ወረዳ አንዱ ሲሆን ህዝብን የሚያገለግለው የጊዜያዊ ሲቪል መዋቅር የ2018 ዓ/ም ዓመታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል። በተደረገው ግምገማ ከወረዳው ስራ አስፈፃሚዎች እስከ ቀጠና አስተባባሪዎችና ቀበሌ ምድብተኞች ድረስ የተገማገሙ ሲሆን በመድረኩም ጠንካራ አፈፃፀሞች እንዲቀጥሉ፣ ክፍተቶች እንዲቀረፉና ለቀጣይ ተስተካክለው እንዲሄዱ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ከሐምሌ 25 እስከ 27/ 2018 ዓ/ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት የተካሔደውን ግምገማ የኮሩ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች የመሩትና የታዘቡት ሲሆን የተጓደሉ አመራሮችን በመተካካትና መዋቅራዊ አደረጃጀት ሪፎርም በመስራት የቀጣይ የስራ ዝርዝር ተልዕኮና አቅጣጫ በማስቀመጥ ግምገማው ተጠናቋል። ከሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ወረዳውን የሚመሩ የሲቪል አስተዳደር መዋቅር:- 1ኛ. ዋና አስተዳዳሪ:- አርበኛ አስር አለቃ ነጋ ፈንቴ 2ኛ. ም/አስዳዳሪ:- አርበኛ ቀሲስ እማኘ ጣፈጠ 3ኛ. የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ብርቁ ካሳው 4ኛ. ሰላምና ደህንነት:- አርበኛ ዋናሳጅን ሐብተማርያም አባተ 5ኛ. ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ:-አርበኛ ዲያቆን ምትኩ ደሴ 6ኛ. ህዝብ ግንኙነት መምሪያ:- አርበኛ አባይነው አለነ 7ኛ. መረጃና ደህንነት መምሪያ:- 𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥𝑥 8ኛ. የፋይናስ መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ሻምበል ወርቁ 9ኛ.  ሎጅስቲክ መምሪያ:- አርበኛ ትዛዙ አድሴ 10ኛ. ገንዘብ ያዥ:- አርበኛ ብርቁ ደምሌ 11ኛ.  ም/ሎጀስቲክ መምሪያ:- አርበኛ አበባው አርቄ 12ኛ.  ም/ሰላምና ደህንነት:- አርበኛ አምሳ አለቃ ፈለቀ መልኩ 13ኛ. ህግ ክፍል (ምርመራ) ኃላፊ:- አርበኛ ትዛዙ ጌታሁን 14ኛ. ፍርድ ቤት ሰብሳቢ:- አርበኛ አበበ ደጀን 15ኛ. ፍርድ ቤት ፀሐፊ:- አርበኛ መርጌታ ጌታዬ ክብረት 16ኛ. ፍርድ ቤት ገንዘብ ያዥ:- አርበኛ አድኖ አሰፋ ሆነው ተመርጠዋል ሲል የ303ኛ ግ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!     ሐምሌ:- 27/2018 ዓ/ም

ወደ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ ለከበባ የገባው የጠላት ኃይል በፋኖ ወታደራዊ ጥበብና ብልሀት በከበባ እየተመታ ይገኛል!! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መ
+2
ወደ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ ለከበባ የገባው የጠላት ኃይል በፋኖ ወታደራዊ ጥበብና ብልሀት በከበባ እየተመታ ይገኛል!! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወደ ሸዋ ምድር ሲግተለተል የገባን የአገዛዙን ጥምር ጦር በወታደራዊ ብልሃትና ጥበብ በገባበት እዳይወጣ አድርጎ እየመታው ይገኛል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ቀወትና ቆሎሚያ አካባቢዎች የገባው የጠላት ኃይል፣ በአርበኞቹ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር  ከገጠመው ጽኑ ምት የተነሳ ማምለጫ አጥቶ ወደ ሸዋሮቢት ለማፈግፈግ ተገዷል። ሆኖም ከገባበት ለመውጣት የተቸገረው ጠላት በቀወት/በኩርብሪና በዋጮ አካባቢዎች በሚገኙ (3) ንጹሃን አርሶ አደሮች ላይ  አሰቃቂ ግድያ ፈፅሟል ።በሌላ ግንባር ከመዘዞ አያበር ቀበሌ እስከ መሶቢት ተራራ ድረስ ባለው መሬት ላይ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክ/ር ከበባ ውስጥ የወደቀው የጠላት ጦር፣ ውድቀቱን በመስጋት ከሸዋሮቢት ተጨማሪ የሰው ኃይል ለማስገባት ቢሞክርም፡ ነገር ግን በሸዋሮቢት ቆቦና ውስቴንቧይ በሚገኙ በአርበኛ ታደለ ወርቁ ብርጌድ የአርበኞች ፋኖ ጦር በደፈጣ በመጠበቅ በጠላት ላይ ከባድ ጉዳት ያሳረፈ ጥቃቶችን በመፈፀም በርካታ የጠላት ኃይል መደምሰሳቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ሰዓት፣ የአስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ባካሄደው የተቀናጀ ወታደራዊ ስልት፣ የጠላትን ጦር ሙሉ በሙሉ መውጫና መግቢያ በማሳጣት በእሳት ወጥመድ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጎታል።በዚሕም የተነሳ ጠላት ጦር በአርበኞቹ የደፈጣ ጥቃት ክፉኛ የሰውና ቁሳዊ ኪሳራ ማስተናገዱ ተረጋግጧል ። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!   ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

ታሪክ የማይረሳው የቁርጥ ቀን ልጅ! ታሪክን ፈሪዎች አይጽፉትም፤ ታሪክን የሚጽፉት በፈተና ወቅት ህዝባቸውን ከፊት ሆነው የሚመሩ አርበኞች ናቸው! ​ህዝባቸው በታሪኩ አይቶት በማያውቀው አስጨናቂ ፈተና ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ ከህዝባቸው ጎን በመቆም ደማቅ ታሪክ እየጻፉ ያለው አርበኛ ዮሃንስ ንጉስ ሙጨ! ​በጎንደር አንድነት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰብሳቢ የሆነው ይህ ቆራጥ መሪ፤ የአማራን ህዝብ ከአብይ አህመድ አረመኔያዊና ጨቋኝ ስርዓት ነፃ ለማውጣት ያልከፈለው መስዋዕትነት፣ ያላየው መከራ የለም! ​ላመነት አላማ፣ ለህዝባቸው ነፃነትና ክብር ሲሉ ህይወቱን በግንባር ቀደምትነት ለመስጠት የወጣው አርበኛ ዮሃንስ፤ ዛሬም የብዙዎች የፅናትና የብረት እምነት ምልክት ሆነው ቀጥለዋል። የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉስ ሙጨ ከትግል ጓዶቹ ጋር በጎንደር ሰማይ ስር!! ​ነፃነት በዋጋ የሚገኝ እንጂ በነፃ የሚሰጥ አይደለም! #Dave #Amhara

የማይበገር ፅናት (ለ) የድል አዋጅ!! በጦርነት መካከል ድሮን፣ ሚግ(ጄት)፣ መድፍ፣ BM ሮኬት በሚዘንብበት ምድር ለአማራ ህዝብ ዘብ የሚቆም ተጨማሪ ሰራዊት ማሰልጠን ፤ በክህሎት፣ በአካል ብቃት፣ በውጊያ ስልት፣ ብቁ የሆኑ ኮማንዶዎችን በተለያዩ ኮርሶች ማብቃት የማይበገረው ፅናት (ለ)ድል አዋጅ መሆኑን የሚያስመሰክር ነው። የድል አዋጁ ዕለት በዕለት በምናስመዘግበው ድልና ስኬት የሚረጋገጥ ሲሆን የማይቋረጠው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና በጠላት ላይ ያለንን የስነ ልቦና ብልጫ፤ የማድረግ አቅም፤ የዓላማና ፅናት፤ የአሸናፊነት መንፈስና የበላይነት የሚያሳይ ስትራቴጂካዊ ድል ነው። ሽፍታ አድርገናቸዋል፤ በትነናቸው ተስፋ ቆርጠዋል በሚሉበት ቅፅበት "እኛ" ሰራዊት አሰልጥነን ለማስመረቅ የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ነበርን። * ስልጠና፦ በጠላት ላይ ያስመዘገብናቸውን ድሎች በማስጠበቅ ለመጨረሻው ድል ግዙፍ ኃይል በመገንባት የምንቀጥልበት ስልት ነው። * ስልጠና፦ ቀጠናውንን በዘላቂነት በመቆጣጠር አስተማማኝ አቅም መፍጠራችንን ያስመሰክራል። * ስልጠና ፦ ትግሉ ብቁ በሆነ መዋቅራዊ ሰንሰለት ተዋረዳዊ አንድነት በአለው ድርጅት የሚመራ መሆኑን ይመሰክራል። * ስልጠና፦  ትግሉ ግልፅ ሁኖ ለተቀመጠለት ፖለቲካዊ ግብ የሚደረግ እና ዓላማውን የማይለቅ ታጋይና አታጋይ የሚመራ ድርጅት መኖሩን በድጋሚ ያረጋግጣል። * ስልጠና ፦ ዘመኑን በዋጀ በሰለጠነ የሰው ኃይል የሚደረገው ትግል ስርዓትና ህግ የሚያከብርና የሚያስከበር ኃይል መፍጠሩን ያሳያል። * ስልጠና፦ በጠላት ላይ የወሰድነው ስትራቴጂካዊ ድል ነው። * ስልጠና ፦ ብቁ በሆኑ የወታደራዊና የፖለቲካዊ አሰልጣኞች የሚሰጥ በመሆኑ ሰልጣኞች የሚታገሉለትን አላማ ማወቃቸውን ያሳያል። * ስልጠና፦ በቀጠናው ላይ ያለንን ተደማጭነት ከፍ ያደረገና ትግሉን በፊታውራሪነት በመምራት ሌሎች ኃይሎች የትግላችንን ጥንካሬ ተመልክተው ትግሉን እንዲቀላቀሉ መነሳሳትን ፈጥሮላቸዋል። * ስልጠና ፦ የመጨረሻው የድል አዋጅ አሸናፊ ፋኖ መሆኑን ለዓለም ያሳያል። ያለ ዕረፍት በሁሉም ቦታ እንሰራለን፤ እናሰለጥናለን እናስታጥቃለን ፣በፈተናዎች ሳንበገር በፅናት ለአማራ ህዝብ ህልውና ዘብ እንቆማለን። የዚህ ዘመን! የመጭውም ዘመን! የኃይል ማሽኖች እኛ ነን!! አዲስ ትውልድ ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በሰሜን ኸዋ ሀገረ ስብከት በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ5 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሀገረ ስብከቱ አስታወቀ ። ምሥራቅ ሐረርጌ ,ኢትዮጵያ ሐምሌ ፳ ፯ ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በታላቋ ገዳም ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ በተከሰተው ከፍተኛ የዝናብና የመባርቅት ድምፅ በደረሰ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት ለጸበል ፣ ለሱባኤና ለመሳለም ከአራቱም አቅጣጫ በተሰበሰቡ በጻድቃኔ ማርያም ልጆችና ወዳጆች ላይ የደረሰው ድንገተኛ አደጋ እጅግ አስደንጋጭና ልብ ሰባሪ ኃዘን መኾኑ ተገልጧል። በዚህ ድንገተኛ አደጋም የ14 ወገኖቻችን ሕይወት ሲያልፍ በ5 ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛና በ2 ወገኖች ላይ መለስተኛ ጉዳት መድረሱም ተመላክቷል። የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው በመገኘት ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ። © የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ ለፈጣን እና ተአማኒ መረጃ ነው