uk
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Відкрити в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Показати більше
2 929
Підписники
+224 години
+3727 днів
+36730 днів
Архів дописів
#ክተት_መክት_አንክት ምኒልክ ዕዝ ክተት ብሎ የግል መሣሪያ ያላቸው ታጣቂዎችን ጠረነ የዕዙ ሰብሳቢ አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ በተገኘበት የግል ባለመሣሪያዎች ጋር ውይይት ተካሂዶ ነው እንዲጠረነፉ የተደረጉት። 11/12/2018 ዓ.ም

በግሸን ደብረከርቤ አምባሰል ወረዳ 023 ቀበሌ ማህበረሰብ ጋር ህዝባዊ መድረክ ተካሄደ! ​ በታሪካዊቷ ግሸን ደብረከርቤ "የአማራ ህዝብ የሀገር ህልውና በመጠበቅ የነበረው ሚና እና አሁን የገጠመው የህልውና አደጋ መውጫ መንገድ" በሚል መሪ ርዕስ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። ነሐሴ 11/2018ዓ.ም በአምባሰል ወረዳ 023 ቀበሌ በተካሄደው በዚህ ህዝባዊ መድረክ ላይ የምኒልክ ዕዝ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ አርበኛ መምህር ፍቅሩ ፈንታው፣ የዕዙ ህዝብ አስተዳደር መምሪያ አርበኛ አበበ ቀዮ፣ የዕዙ ም/ትል ት/ት እና ስልጠና መምሪይ አርበኛ ዘሪሁን ደምሴ፣ የዕዙ ምክትል ፖለቲካ ጉዳዮች መምሪያ አርበኛ ስንታየሁ ተስፋው እና የ104ኛ ኮር አመራሮች ተገኝተው ከነዋሪቹ ጋር በወቅታዊ ፣አገራዊና አካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ተወያይተዋል። ​በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት አመራሮቹ ግሸን ተተኪ የኢትዮጵያ ነገስታት የሚቀመጡባትና በሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ ያላት ታሪካዊ ቦታ መሆኗን አውስተዉ  አሁንም ቢሆን የህዝቡን ህልውና በማስጠበቅና ወቅታዊውን አደጋ በመመከት ረገድ ከአካባቢው ታሪካዊ ገጽታ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚገባ አስምረውበታል። ​በተጨማሪም ለአማራ ህዝብ ህልውና አደጋ የዳረጉ ዋና ዋና ምክንያቶችና ከዚህ ፈታኝ ሁኔታ ለመውጣት ህዝቡ ሊጫወተው የሚገባው ሚና ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። አመራሮቹ አክለውም፦ "ትግላችን ፍትህና ዲሞክራሲን ለማምጣት እንዲሁም የራሳችንን ህልውናና ጥቅም ለማስከበር እንጂ የማንንም ጥቅም ለመጋፋት አይደለም" ሲሉ የትግሉን መሰረታዊ አላማና ፍትሃዊነት አብራርተዋል። ​በውይይቱ ወቅት ከአካባቢው ህዝብ የተለያዩ አስተያየቶችና ስጋቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ነዋሪዎቹ ከዚህ ቀደም የአካባቢው ጥበቃ በመላላቱ ቀበሌያቸው ለሌቦችና ለዘራፊዎች ተጋልጦ መቆየቱን ገልጸዉ አሁን በይፋ የተጀመረው ስርዓት የማስያዝ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና አካባቢው ሙሉ በሙሉ ከአጸያፊ ድርጊቶች እንዲጸዳ ጠይቀዋል። ​በመጨረሻም ነዋሪዎቹ ከመካከላቸው የበቀሉ የጠላት ተላላኪዎችንና ባንዳዎችን በጋራ በመታገል ለማስወገድ፣ እንዲሁም ጠባቂ አጥታ የማንም መጫወቻ ሆና የቆየችውን ግሸን ደብረከርቤ ወደ ሙሉ ሰላምና ስርዓት ለመመለስ ከሰራዊቱ ጋር በቅንጅት ለመስራት መወሰናቸውን አስታውቀዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን  መምሪያ! ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም

ለከበባ የመጣው የብልፅግና ጥምር ጦር፤ በከበባ ድባቅ ተመታ!!      ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም ራሱን አየር ወለድ ኮማንዶ ነኝ ብሎ የሚጠራው የብልፅግና ወንበር ጠባቂ ጥምር ጦር መነሻውን ከአረርቲ ከተማ፣ በተላላኪው ሚሊሻ እየተመራ ወደ ፋኖ ቀጣና እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በነበልባል ክፍለ ጦር ድባቅ መመታቱ ታወቀ። ለከበባ የመጣው የጠላት ኃይል በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር  መመታቱን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት አስታወቀ። ክፉኛ የተመታው የጠላት ኃይል መውጫ ቀዳዳ በማጣቱ ሽፋን እዲደረግለት ጠይቆ፣ በዙ-23 ታግዞ ከባልጭ ወደ ክርስቶስ ሳምራ ያቀናውን አባዳሌ በተባለ ቦታ በተዘጋጀለት ቦታ ገብቶ በተናዳፊወቹ ፋኖዎች በተወሰደበት የደፈጣ እርምጃ ክፉኛ መመታቱ ተረጋግጧል። ከ300 በላይ የሚሆነው የአገዛዙ ጥምር ጦር ለከበባ ቢንቀሳቀስም ራሱ ከበባ ውስጥ ገብቶ በርካታ ኃይሉ ወደ ማይመለስበት ተሸኝቷል ። በዚሕም አውደ ውጊያ ድንቅ የተባለ የደፈጣ ኦፕሬሽን የተካኑት ነበልባሎቹ የፊት ማጥቃታቸውን እንደቀጠሉ ይገኛሉ። ሙትና ቁስለኛውን በአንቡላስና አይሱዚ መኪና ጭኖ መመለሱ ሲረጋገጥ፣ ሙትና ቁስለኞች ቁጥራቸው በውል አልታወቀም ሲል የግንባር መረጃችን አክሎ ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ነሐሴ 11/2018 አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ጀነራል ኃይሌ ዘ-ወባንተ ክፍለ ጦር የዕዝና የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ከሰዴ ሙጃ ወረዳ ህዝብ ጋር በሮቢት ከተማ ውይይት አደረጉ። የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አንድነት ሂደት፣ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግል ስኬት፣ ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎች፣ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ስላለው የደጀንነትና የትግሉ አጠቃላይ ሂደት በተመለከተ ጥልቅ ውይይት ተደርጎል ። በህዝባዊ የውይይት መድረኩ የሮቢት ከተማ ነዋሪዎች፣ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት የጎንደር ፋኖ ወደ አንድነት መምጣቱን አስመልክቶ  ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን፣ በቀጣይም ዕዙ ሁሉንም ኮሮችና ክፍለ ጦሮች በማዋሀድ በጋራ ጠላታቸው ላይ እንዲዘምቱ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስትራቴጂዎችን መንደፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል። ባለፉት ጊዜዓት በርካታ የአደረጃጀት ክፍተት የነበረበት ቀጣናው አሁን ላይ በሽሎ ሬጅመንት እራሱን ካለፉት ስህተቶቹ በመማር እራሱን ለተሻለ ወታደራዊ ግዳጅ አዘጋጅቶ የወረዳውን  ማህበረሰብ በቅንነትና በሀቀኝነት እያገለገለ እንደሚገኝም ተጠቁሟል። በተጨማሪም ዘረኛውንና ጨፍጫፊውን ሥርዓት እድሜ ለማሳጠር ትግሉን ህዝባዊ ማድረግና በአጭር ጊዜ መቋጨት በሚያስችሉ ሁለተናዊ ዝግጁነቶች መገኘት እንዳለበት  የከተማዋ ነዋሪዎች አሳስበዋል ። በህዝባዊ ውይይቱን የመሩት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አበበ መልኬን ጨምሮ ሌሎች የዕዙና የክፍለ ጦር አመራሮች እንዲሁም ከበሽሎ ሬጅመንት አመራሮች ጋር በጥምረት ጠንካራና ገንቢ ሀሳቦች ተነስተው የትግሉ ደጀንና ባለቤት ህዝቡ  መሆኑን በማረጋገጥ አስተያየት ተሰጥቶበት መግባባት ላይ ተደርሶ ውይይቱ በስኬት ተጠናቋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ለመቄት ወረዳ ጊዚያዊ ህዝብ አስተዳደር አመራሮች ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ! ​በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሃይል (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ አደረጃጀት ዘርፍ መምሪያ እና በዕዙ ህዝብ አስተዳደር መምሪያ አማካኝነት ዉክልና በተሰጣቸዉ የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ፖለቲካ ዘርፍ እና አደረጃጀት ዘርፍ አማካኝነት ለመቄት ወረዳ ጊዚያዊ ህዝብ አስተዳደር አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የአቅም መገንቢያ ስልጠና በስኬት በዛሬዉ ዕለት ተጠናቋል። ​ስልጠናው በወረዳው የሚገኙ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች የወቅቱን የትግል ሁኔታ በመረዳት፣ ህዝባዊ አገልግሎትን በብቃት እና በስነ-ምግባር ማቅረብ የሚያስችላቸውን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል። ​በስልጠናው ወቅት በርካታ ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች የተዳሰሱ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ​*የህዝብ አስተዳደሩ ተግባር እና ኃላፊነት፡- ጊዚያዊ አስተዳደሩ በአካባቢው ሰላምና ጸጥታን ከማስከበር ባሻገር የህዝቡን ዕለታዊ እንቅስቃሴዎች የመምራት ድርሻ፤ * የአማራ ትግል መሰረታዊ መነሻዎች እና የደረሰበት ደረጃ የትግሉ ታሪካዊና ወቅታዊ ምክንያቶች እንዲሁም አሁን የደረሰበት ምዕራፍ፤ ​*ተቋማዊ ዲሲፕሊን፡ -ህዝባዊ አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት አመራሩ ማሳየት የሚገባው ከፍተኛ ስነ-ምግባር፣ ታማኝነት እና ተቋማዊ አሰራር ​*ከወታደራዊ ክንፉ ጋር ያለው ግንኙነት፡ በስቪል አስተዳደሩ እና በሰራዊቱ መካከል ሊኖር የሚገባው የተቀናጀ አሰራር እና የስራ ክፍፍል በስፋት ተዳሰዋል። ​ይህን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና የሰጡት የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ እና የኮሩ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ጋሻው አበበ ናቸው። ​አሰልጣኞቹ በመልእክታቸው አመራሩ ከህዝቡ የተጣለበትን አደራ በግንባር ቀደምትነት ለመወጣት ተቋማዊ ዲሲፕሊንን መጠበቅ እና ከወታደራዊ ክንፉ ጋር ያለውን ቅንጅት ማጠናከር አስፈላጊ እንደሆን አሳስበዋል። ሰልጣኝ አመራሮቹ በበኩላቸው ያገኙት ግንዛቤ በቀጣይ ስራዎቻቸው ህዝቡን በቅንነት እና በብቃት ለማገልገል ትልቅ አቅም እንደሚሆናቸው ገልጸዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም

ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አካል የሆነው ጥቁር አንበሳ ክፍለ ጦር ድንዛዝ ላይ በጠላት ኃይል ላይ ጠንካራ ክንዳቸው አሳርፈውበ
+1
ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር አካል የሆነው ጥቁር አንበሳ ክፍለ ጦር ድንዛዝ ላይ በጠላት ኃይል ላይ ጠንካራ ክንዳቸው አሳርፈውበታል። ከደጎማና ከበለሳ በአፈሳ የሰበሰበውን ወጣት በበርካታ ተሽከርካሪዎች ጭኖ በማጀብ ላይ እያለ በአርበኛ ልባርግ ሙላት እየተመራ በእጀባ ላይ የነበረውን ከ20 በላይ ተሽከርካሪ እግር አውጭኝ ጥሎ የፈረጠጠ ሲሆን ከማክሰኝትና ከጠዳ እንዲሁም ከደጎማም የሚያግዝ ኃይል ወደ ፋና ድንዛዝ አቅጣጫ በማንቀሳቀስ እራሱን ለማትረፍ ጥረት አድርጓል። ከተለያዩ ከተሞች በአፈሳ የሰበሰባቸው ወጣቶች ወዲያውኑ ሲበተኑ ከፍተኛ ሀይሉ ደግሞ ከባድና ቀላል ቁስለኛ አስተናግዷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ሰበር የድል ዜና:- የመሃመድ ተሰማ የእብሪት ጎማ ጮቄ ላይ ተንፍሷል። ^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^ ......ነሐሴ11/2018ዐዓ.ም #ቢቡኝ_አባ_ደሞ_ሻለቃ የአማራ ህዝብ የራሱን አሳልፎ የማይሰጥ የሌሎችን የማይነካ ኩሩ ህዝብ ነው። ነገር ግን ጊዜ የሰጠው ቅል ሆነና ነገሩ ብልፅግና መራሹ የአብይ አህመድ ስርዓት የአማራን ህዝብ እርፍት በመንሳት በትውልድ ቀዬው መታወቂያ እየተጠየቀ ሰራዊት አዝምቶበት በዕርስቱ እንዳይኖር ንብረቱን እየዘረፈ ድፍን 3ት ዓመት ሞልቶታል። ‎ይሁን እንጂ ይህንን የሚቀበል አማራዊ ማንነትና ስነልቦና በታሪክም ዛሬም የለም። ይህ እብሪተኛ ስርዓት 6 ክ/ጦር ሰራዊትና በሜካናይዝድ ታጅቦ ወደ ጎጃም ጮቄው ቀጠና አሰማርቷል። የጮቄዋን ከተማ ዋብርን መቀመጫ አድርጎ ወደ ደባይ ፤ሰዴና ስናን በሜካናይዝድ እየታጀበ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል። ይህንን የተመለከቱ ከቢቡኝ ወረዳ የወጡ ጀግኖች ስለጉዳዩ መነጋገርና ማቀድ ጀመሩ። ጠላት ወገን ላይ እያደረሰ ያለው በደል እጅግ አበሳጭቷቸዋል። ጠላት ጠዋት ሞቶ እኔ ልሙት ማታ፤ ‎ከሺ ቀን ይበልጣል የአንድ ቀን ደስታ። በማለት 50ዓለቃ ስማቸው ቢሻው (ዝግባው) ፤ ፋኖ አይናዲስ ዓለሙ (የ54ኛ ክ/ጦር ወ/አዛዥ) ፤ አርበኛ እሱባለው ባምላክ፤ ፋኖ እንዳላማው ስለሽ (የሻለቃዋ ሰብሳቢ) ፤ ፋኖ ጌታው አያሌው(የሻ/ም/ሰብሳቢ) ፤ መቶ አለቃ አንሙት መርሻ (ዘመቻ) እና ፋኖ አስናቀው ስዬ (የሻለቃዋ ም/ዘመቻ) ፊትአውራሪነት የቢቡኝ አባደሞ ሻለቃን በመያዝ ዋብር ላይ ጀብድ መስራት ተችሏል። በአውደ ውጊያ የተገኘ ድል ➺1ድሽቃ ➺1ብሬን ➺1ስናይፐር ➺5የሞርተር ቅንቡላ ➺42ክላሽ ➺1icom መገናኛ ➺18f1 ቦንብ ➺64የክላሽ ካዝና ➺32ወተደራዊ ሻንጣና በርካታ የድሽቃና የብሬን ጥይት እንዲሁም በርካታ የክላሽ አስቃጥላ ጥይትና ወታደራዊ ቁሳቁሶች #የተማረከ ሲሆን #የ10ኛ ክ/ጦር #4ኛ ሬጅመንት አመራር ከእነ ሙሉ አባሉ ሙሉ በሙሉ ተደ-ምስ_ሷል። ‎ አንድነታችን በተባበረ ክንዳችን ድል ለአማራ ህዝብ አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ አፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

ሰበር ዜና! በራያ ግንባር በግዳጅ ላይ የሚገኙት የጠላት ብልፅግና ሰራዊት ከስምሪት ቀጠና በመጥፋት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮርን ተቀላቀሉ። ዛሬ ነሐሴ 11/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ የጠላት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር 48ኛ ክፍለጦር የ4ኛ ሻለቃ ኦፖ ከነ ሙሉ ትጥቁ ወደ ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ የ102ኛ ኮርን ከጓዶቹ ጋር ተቀላቀለ። ከተቀላቀሉት የጠላት የሰራዊት አባላት አማኑኤል ዳምጠው አዳነ እና ክንዱ ጌትነት ደመላሽ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር 48ኛ ክፍለጦር 4ኛ ሬጅመንት ይገኙበታል። በተጨማሪም ዋክሹም ተስፋየ ኦላና ፣ሸለማ ጌታቸው ሹማ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር 58ኛ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ 2ኛ ሻምበል አባል እና ክንዱ ጌትነት ደመላሽ 48ኛ ክፍለጦር የ4ኛ ሻለቃ ኦርድናንስ ትናንትና አመሻሹን በጀሌ(ያለመሳሪያ) የ102ኛ ኮር ፋኖን ተቀላቀሉ። ወደ ፋኖ ከመጡት የብልፅግና 4 የሰራዊት አባላት መካከል 1 ጥቁር ክላንሽ ኮፍ መሳሪያ፣120 የክላሽ ጥይት ተተኳሽ እና 2 ኤፍ ዋን ቦንብ በመያዝ ተቀላቅለዋል። ሰሞኑን ከራያ ግንባር እስከ ወልድያ፣ ደሴና ኮምቦልቻ ድረስ ከባድ ውጥረት መንገሱን ተከትሎ በየቀኑ ቢያንስ ከ35 በላይ የሚሆኑ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በራያ ግንባር ከስምሪት ቀጠናቸው እየወጡ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም

በአገዛዙ ሚሊሻዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ~~~~~~~~~~~ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም በአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር በአገዛዙ ጋሻ ጃግሬዎች ላይ በደፈጣ ድል ተቀዳጅተዋል።ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም መነሻውን ከደባይ ጥላት ግን ወረዳ በማድረግ ለዝርፊያና ለጥፋት እየከነፈ የነበረውን የአብይ አህመድ ዙፋን አስጠባቂ የእናት ጡት ነካሽ ባንዳዎች ላይ የ24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ተርቦች የባባት ከሚባል ቀበሌ ላይ ደፈጣ በመጣል አሸናፊ የተባለው ከዳተኛን ጨምሮ በሌሎች አባሎች ላይ መብረቃዊ እርምጃ ተወስዷል። አሸናፊ የተባለው ባንዳ በፋኖ መዋቅር ታቅፎ ድሽቃ ምድብተኛ ሆኖ ሳለ በወርሐ ጥር ወር ላይ ፋኖን በመክዳት ወደ ጠላት የተቀላቀለ የነበረ ሲሆን ዛሬ በራሱ አሐዶች እርምጃ ተውዶበት ሞቱ የውሻ ሞት ሆኗል።ሌላው ጠብደል የአገዛዙ ሎሌ የነበረው ባንዳ ምትኩ ቢያድግልኝ ባሳደገው ቀዬና በተወለደበት አካባቢ የፋኖ አልሞ ተኳሾች ቅልጥሙን በመሥበር የሀፍረት ማቅ ያለበሱት ሲሆን ሆስፒታል በመግባት በሞትና በህይወት መካከል እያጣጣረ ይገኛል። የአገዛዙ የብርሐኑ ጁላ ጉጅሌ ጦር ከሰኔ 29/ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ያለ የሌለ ሐይሉን አሟጦ በደባይ ጥላት ግን ወረዳ 2 መድፍ፣ 3 ዙ-23 ፣4 ኮሎኔል እና ለቁጥር የሚያታክት የቡድን መሳሪያ ይዞ ቢያሰልፍም ጀግኖቹን የበላይ ትንፋሾች ደባይ ጮቄ ሻለቃን አይደለም መደምሰስ ለማሰብ ከብዶት በንፁሃን ሐብት ዘረፋ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል። አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!!!!!! 24ኛ ክ/ጦር ሚዲያ ክፍል

🔥 ሰበር የድል ዜና - ከጮቄ ማማ! 🔥 "የአንበሳ ግሣት ከዋብር የጮቄው አናት!" 🦁 ገና ሳይነጋ የጮቄዋ አናት ዋብር በድል ተንበሽብሻለች! የቁርጥ ቀን ልጆቻችሁ፣ የ54ኛው ክ/ጦር መዝገበ ዋለልኝ ሻለቃ ተርቦች፣ የብርሃኑ ጁላን ሰራዊት አይቀጡ ቅጣት ቀጥ*ተውታል። የጠላት ኃይል ጢባጢቤ ተጫውተውበት፣ መፈናፈኛ አሳጥተው ወደማይመለስበት ሸኝ*ተውታል። 🛡 የተማረኩ የጦር መሳሪያዎች፦ 🔹 ድሽቃ 🔹 ብሬን 🔹 ስናይፐር 🔹 ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች የጠላት ሰራዊት የዝናብ ልብሱን እንኳ ሳይለብስ ተጨብጦ ተመትቷል። ዝርዝር መረጃዎችን የክላሽ ቆጠራው እንደተጠናቀቀ ይዘንላችሁ እንቀርባለን። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ! 📅 ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም 📍 አፋብን | ቴዎድሮስ ዕዝ

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጣናዎች ሕዝባዊ አስተዳደር መዋቅር በመዘረጋት ትግሉን እያፋጠነ መሆኑኑ ተገለፀ !!             ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተቆጣጠራቸውና ነፃ ባወጣቸው አውራጃዎች ዘላቂና ጠንካራ አደረጃጀት የመመስረት ተግባር በከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት እያፋጠነ ይገኛል።  ይሕ ሕዝባዊ አደረጃጀት ኩታገጠም የሆኑ ቀበሌዎችን ያቀፈ የክላስተር አወቃቀር ለወታደራዊ ግብ ስኬትና ቀዳሚ ከመሆናቸውም ባሻገር፣  የሕዝቡን የዕለት ተዕለት የአስተዳደርና የደህንነት ጥያቄዎች በባለቤትነት ለመመለስ አልሞ የተካሄደ ነው ሲል የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት አስታወቀ።  የክላስተር ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሕዝቡን ነፃ ፍላጎት መሠረት በማድረግ የተከናወነ ሲሆን፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩን የሚመሩ ስራ አስፈፃሚዎች በመመደብና ግልጽ የአስፈፃሚዎች መምሪያ በማዘጋጀት ሕዝባዊ መዋቅሩ ሙሉ በሙሉ ሥራውን እንዲጀምር ተደርጓል ብሏል። ይህ የተቀናጀ ህዝባዊና ወታደራዊ እርምጃ የትጥቅ ትግሉ ከወታደራዊ ድል ባለፈ የሕዝብን ስልጣን ባለቤት የሚያረጋግጥና የነፃ አውጪነቱን ዓላማ በተግባር የሚያሳይ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑ ተረጋግጧል ሲል አክሎ ገልጿል። በስነ-ስርዓቱ ማጠናቀቂያ ላይም የተመደቡት አመራሮች የተጣለባቸውን የትግልና የሕዝብ አደራ በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በእኩልነትና በነፃነት ለማገልገል በቁርጠኝነት ቃለ-መሀላ ፈፅመዋል ሲል አጠቃሎ ገልጿል።  "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ