ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 937
Підписники
-324 години
+3667 днів
+38130 днів
Архів дописів
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በኤፍራታና ግድም መነሻውን ከኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ያደረገው የብልፅግናን ተልዕኮ የያዘ የጥላት ሀይል ተገርፎ ወደመጣበት ተመለሰ !!
በቀን ሀምሌ9/2018 ዓ/ም መነሻውን ከይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ተቆርሶ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ከተባለው በጤ እና ሰንበቴ በማድረግ ወደ ጀግኖቹ ቀዬ አርሶ አንባና ዘንቦ ያቀናው የዘርጨፍጫፊው የብልፅግና ፖሊስ፣ሠላም አስከባሪ፣ሚኒሻ የሚባሉ ጥርቅም በንፁህን ገበሬ እርሻ ላይ ያሉ ገበሬዎች ላይ ተኩስ ከፍተውባችው ቢውልም የአባት አርበኞች ጦር እንዳለ ሻለቃ እና በ7ለ70 ክፋለጦር ሻንበሎች የተውጣጣ ኋይል ሊዘርፍና ቤት ሊያቃጥል የመጣውን ወራሪ የጠላት ሀይል መክተው ወደመጣበት ጎሬው መልሰውታል።
ከነባሩ የአማራ እርስት ተቆርሶ ወደ ልዩ የብሔረሰብ ዞኑ የተካለሉት በጤ፣ሰንበቴና እና ከሚሴ የአክራሪ አማራ ጠል ሀይሎች መፈልፈያ ብቻ ሳይሆን ትርፍ አማራቹን የይፋትን ገበሬን በመንግስት ስረዓት ተገን በማድረግ የሚዘርፉ የሚያወድሙ አክራሪ አማራ ጠል ሀይሎች የሚፈልፈያ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው በተደጋጋሚ ባሳዩት ጭካኔ የተሞላባቸው ዘረፋዎችና የዘር ማፅዳት ዘመቻውች ይህ ሃይል አማራ ጠል መሆኑን ያሳየ ቡድን ነው።
ድል ለአማራ ህዝብ !!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !!
ሀምሌ10/2018 ዓ.ም
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብግንኙነት መምሪያ !!
+3
ፈረስቤት ከተማን ለመቆጣጠር የአሰፈሰፈው የአብይ መራሹ ሰራዊት በአምስት አቅጣጫ ቢመጣም በአናብስቶቹ 99ኛ ክ/ጦር እየደቆሰ ይገኛል‼️
የደጋ ዳሞት ወረዳ ከተማ የሆነችውን ፍረስቤት ከተማን ለመቆጣጠር በሚል ከደምበጫ ወደ ገሊላ የተንቀሳቀሰው የብርሃኑ ሰራዊት በኢንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃ ሁለት ቀን ሙሉ ሲቀጠቀጥ ውሎ BM፣ዙ፣መድፍ እና ሞርተር በመጠቀም ተራራና ሸለቆውን እንዲሁም የአርሶ አደሩን ቤትና አዝመራ አውድሟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከደምበጫ ወደ አንጀኔ ፈረስቤት የተንቀሳቀሰው ይህ ወራሪ ሰራዊት ጨረቃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከባድ ምት አርፎበታል ።ይህንን ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግናው ሰራዊት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ከፊት አሰልፎ እስከ ምሽቱ 2:00 ደረስ በBM፣ዙ፣መድፍ፣ዙ-23 እና ሞርተር በመጠቀም የአርሶ አደሩን ቤትና ንብረት አውድሟል።
ይህ የብልፅግና ሰራዊት በሦስት ጀነራል፣ 3 BM፣ 3 መድፍ፣ 120m ሞርተር፣ ብረት ለበስ እና ዙ 23 በመጠቀም ወጊያ ቢከፍትም በክንደ ነበልባሎቹ 99ኛ ክ/ጦር በደጋዳሞት ሻለቃ ፣እንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃ፣ በላይ ዘለቀ ሻለቃና በአባት አርበኞች በተከፈተበት የተቀናጀ ፈጣን የማጥቃት ውጊያ ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል።
በበላይ ዘለቀ ሻለቃ ውስጥ ከፈንድቃ እስከ እንቡሊ ለማስፋት ቢሞክርም# የውላ ከተማ ላይ ከባድ ምት በማሳረፍ ሙሉ በሙሉ የበላይ ዘለቀ ሻለቃ ተቆጣጥሮት መዋሉን እና ከፋኖ ከድቶ የሄድን #መግባሩ ደምሌ እና አንድ ሌላ ሆድ አደር ሚሊሻ እርምጃም ተወስዶባቸዋል።
👉3ኛ ቀኑን በያዘው ከአገዛዙ ጋር እየተደረገ ባለው ትንቅንቅ 99ኛ ክ/ጦር በርካታ የአገዛዙን ሀይል በመደምሰስ በርካታ የነፍስወከፍ መሳሪያና ተተኳሽ ከአገዛዙ ጉሮሮ መማረክ ተችሏል።
10/11/2018 ዓ.ም
እስቲ ለአፍታ ቆም በሉና አስተውሉኝ...እኔን ስታዩኝ ምን ይታያችኋል?
በጥንቱ ታሪክ ማንነት ውስጥ ብቻ የሚቀዝፍ የትላንት ጥላ? ወይስ በትከሻው ላይ የታላላቅ አባቶቹን አደራ ተሸክሞ፣ ዛሬ በሚናወጠው ማዕበል መካከል በልበ-ሙሉነት የሚራመድ መንገደኛ?
እኔ የአማራ ልጅ ነኝ።
ስሜ ሲጠራ አንዳንዶች በስጋት ይቆማሉ፤ ሌሎች ደግሞ በትዝታና በኩራት ፈገግ ይላሉ። እኔ ግን የምነግራችሁ ስለ ስሜ ብቻ ሳይሆን፣ እዚህ ደረቴ ውስጥ ስለሚመታው ልብ እውነት ነው። እኔ የተሰራሁት ከደግነትና ከብርታት ነው። ዛሬ የምናገረው የትላንቱን ታሪክ ለመድገም ብቻ አይደለም፤ ዛሬ የምናገረው አሁን፣ በዚህች ሰዓት በዓይኖቼ ውስጥ የሚንቀለቀለውን እሳትና በነፍሴ ውስጥ የሰረገውን ፅኑ እምነት እንድታዩት ነው።
እኛን ማወቅ ማለት ማዕበልን መላመድ ምን ማለት እንደሆነ መረዳት ነው። እንደ ቆራጦቹ ተራሮቻችን፣ መከራ በረታ ብለን ጀርባችንን ሰጥተን አንሸሽም። ይልቁንም፣ ነፋሱ በበረታ ቁጥር እንደ ጥድ ዛፍ ስሮቻችንን ወደ መሬቱ በጥልቀት እንሰዳለን።
ነገር ግን ከዚህ እልከኝነት ጀርባ አንድ ትልቅ እውነት አለ—እኛ ሰላምን በጥልቅ እንወዳለን። የማንም ቤት እንዲፈርስ፣ የማንም ህልም እንዲጨልም አንመኝም። በእጃችን ላይ ያለው ጽናት ሌላውን ለመግፋት ሳይሆን፣ ራሳችንን፣ ወገናችንንና የምናምንበትን እውነት አቅፎ ለመጠበቅ ነው። እያንዳንዱ የከፈልነው ዋጋ የሚናገረው አንድ እውነት ብቻ ነው፦ ክብርና ነጻነት በፈቃድ እንጂ በድርድር አይገኙም!
አሁን ላይ መንገዱ አቀበት፣ ሰማዩም በዳመና የተሸፈነ ቢመስልም... እኔ ግን ተስፋ አልቆርጥም። እምነቴ ከላዬ ካለው ሰማይ፣ ጥንካሬዬ ደግሞ በቅድመ አያቶቼ ደም ከረጠበው ቅዱስ ምድር የመነጨ ነው።እኛ ሁልጊዜም ከመሬት እንነሳለን። ህመማችንን ወደ ብርታት፣ እምባችንን ወደ ዜማ እየቀየርን ወደፊት እንጓዛለን። እኔ የአማራ ልጅ ነኝ፤ ትላንት የነበርኩ፣ ዛሬም ያለሁ፣ ነገም ደምቄ የምኖር!" ሰላምህ ይብዛልኝ ደጉ ጀግናው ህዝቤ #Dave #Amhara
የአይበገሬዎች ትንቅንቅ ዛሬም ቀጥሏል‼️
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም
~
ሶስት መድፍ፣ ሶስት ዙ 23፣ ድሮን፣ እጅግ በርካታ ዲሽቃዎች እና ሌሎች የቡድን መሣሪያዎችን ከአያሌ ሠራዊት ጋር ይዞ በፋኖ የኃይል ብልጫ የተወሰደበት ፀረ-ዐማራው አገዛዝ የጀት ድብደባ ለማድረግ እያንዣበበ ነው።
በ102ኛ ኮር የ33ኛ ክፍለ-ጦር አካል የኾነችው እና በጀግናው ሰማዕት ሻለቃ ሽዋነህ ሙሉጌታ (ደምሰው ቱርኩ) ስም የተሰየመችው 3ኛ ሬጅመንት ወደ ደጋ-ዳሞት ለሚንገሳቀሰው ዘር አጥፊ ሠራዊት ደጀን ለመኾን ከኃላ በዳንዳን ተራራ የተሰለፈውን አረመኔ ቡድን እያናዘዘችው ነው።
ሌሎች የክፍለጦሩ ሬጅመንቶችና ከገነት አቦ እስከ ወይበይኝ_ዳንዳን አካልለው ከጠላት ጋር እየተናነቁ ነው።
በፋኖ እየተዋረደ የሚገኘው የሚገኘው ይህ ጨፍጫፊ የብልጽግና ቡድን የበቀል በትሩን በቋሪት ንፁሃን አርሶ አደሮችና ሕፃናይ ላይ እሳርፏል።
1. ተስፋሁን አልማው. አለሳት .... እርሻ ላይ እያለ በሬ ሳይፈታ በእጅ ይዘው ገድለ-ውታል።
2. ፈንታሁን አለሙ .... አለሳት ... በሕመም ኦፕሬሽን ተሠርቶ ቤቱ ከተኛበት ገብተው ገድለውታል።
3. እንየው አድማሱ ... ቤቱ ከተቀመጠበት በጥይት ደብድበውት ሞተ ብለው ቢመለሱም እስካሁን ቁስለኛ ነው።
4. ሕጻን ስማቸው ምናለ ... የ7 ዓመት ሕጻን ... ቁስለኛ ነው
5. ሕጻን ይደነቅ ... የ7 ዓመት ቁስለኛ ናት
በተጨማሪም በስም ያልታወቁ ንፁሃን የተሰዉ ሲኾን፤ እጅግ ብዙ አርሶ አደሮች ከመኖሪያ ቤታቸው እየተለቀሙ ለመንገድ ማስለቀቂያነት ታፍነዋል።
ድል ለዐማራ ሕዝብ‼💪💪💪
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም
10/11/2018 ዓ.ም
መካነሰላም ከተማ አቅራቢያ መቅደላ ታዳጊ ከተማ ውስጥ በንፁኃን ላይ ጉዳት ደረሰ!!
በሄሊኮፕተር ጭምር በርካታ ወታደሮችን ከሌላ ቦታ አምጥቶ ከመካነሰላም ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኝ ቀጠና ውስጥ የደፋው የጠላት ኃይል በንፁኃን ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ቀጥሎበት መቅደላ ታዳጊ ከተማ ውስጥ ከወላጆቹ ጋር የሚኖር ሀብቴ ደመቀ የተባለ ህፃን ልጅ በትናንትናው እለት መካነሰላም ከተማ ከሚገኘው የመቅደላ አምባ ዩኒቨርስቲ ካምፓስ ቅጥር ግቢ ውስጥ በተጠመደ ሞርተር ቅንቡላ ሆዱ ላይ ተመትቶ በሞት አፋፍ ላይ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሀብታሙ ጌታሁን የተባለ በልብስ ስፌት የሚተዳደር ግለሰብ እዚያው መቅደላ ታዳጊ ከተማ ውስጥ በተጣለ የሞርተር ቅንቦላ ተመትቶ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶበታል።
ለአመታት ከኖሩበት እና ሀብት ንብረት ካፈሩበት ቀያቸው በአገዛዙ ተላላኪዎች በተፈፀመባቸው ጥቃት ተፈናቅለው ወደ አማራ ክልል የመጡ ወገኖቻችን አሁን ላይ መድረሻ አጥተው የከባድ መሳሪያ እና ድሮን ጥቃት ሰለባ መሆናቸው እጅጉን ልብ ሰባሪ ክስተት ነው:: ሞትን ሸሽተው ቢመጡም ሊተርፉ አልቻሉም። አማራ ምን ያክል ተሳዳጅ እንደተደረገ ይህ የተፈናቃይ ወገኖቻችን ሁኔታ አስረጅ ነው። ህፃን ሀብቴ ደመቀ ከጥቃት ተርፎ ወደ አማራ ክልል ከወላጆቹ ጋር ቢመጣም የሞርተር ቅንቡላ ማረፊያ ሆኖ ጨቅላው ሰውነቱ የእሳት ማብረጃ ሆነ።
በመካነሰላም ቀጠና በተከታታይ ላለፉት ቀናት ተመሳሳይ ጥቃት ተፈፅሞ በንፁሀን እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
ሰሞኑን ጭምር ወደ አርሶ አደሮች መንደር ከባድ መሳሪያ በተደጋጋሚ ተተኩሶ በቤት እንሰሳት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን መግለፃችን ይታወቃል:: ከደረሰው ቁሳዊ ጉዳት ባሻገር ንፁኃን ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከፋኖ ጋር በሚደረግ ውጊያ እግረኛው ሲሸነፍበት የአየር ኃይሉ እና ሜካናይዝዱ ንፁኃንን እንድጨፈጭፍ የሚያዝዘው የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት በየእለቱ የሚፈፅመው ግፍ መላው አማራ ለትግል እንድነሳሳ የሚያደርግ መሆኑን በመረዳት ጠላትን አምርረን በመጥላት ለትግል ቆርጠን መነሳትና በተባበረ ክንዳችን ለህልውናችን መቆም አለብን የሚለው ወቅታዊ መልዕክታችን ነው ሲል የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ አስታውቋል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሀምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም
አባት አርበኞች ከህልውና ትግሉ ጎን ለጎን የሀገር መሠረተ ልማት ማከናወናቸው ተገለፀ!!
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መንገድና ኮንስትራክሽን ክፍል በራሳ ጉባ ክፍለ ጦር አባት አርበኞች ትብብር የተቀናጀ ጥረት በርካታ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የራሳ ክላስተር አስታውቋል።
በዚህም መሠረት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ ራሳ ክላስተር አባዬ አጥር ቀበሌ የሚገኘውን የመኪና መነሀሪያ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ሥራ ተጠናቋል። ይህ በ1 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የመኪና መነሀሪያ በሕብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎና የገንዘብ መዋጮ የተገነባ ሲሆን፣ በ330 ሜትር የጋቢዮን ሽቦና የብረት አጥር የመከለል ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።
ይህ የተጠናቀቀው የልማት ፕሮጀክት በይፋ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ለማድረግ የክላስተር አመራሮች የመክፈቻ መርሐ-ግብር ባዘጋጁበት ወቅት፣ የዕዝ፣ የኮር እና የአባት አርበኞች ከፍተኛ አመራሮች በቦታው ተገኝተው ሥራውን አስጀምረዋል።
የክላስተሩ አስተባባሪ አክሎ እንደገለጸው፣ ድርጅቱ ማኅበረሰቡን መሠረት ባደረገ መልኩ የሕዝብ መገልገያ የሆኑ ንብረቶችንና መሠረተ ልማቶችን በትብብር በማስጨረስ ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል ሲል ገልጿል። የኮንስትራክሽን ክፍል ኃላፊ በበኩላቸው አሁንም በመሠራት ላይ ያሉና በቀጣይ ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ ታላላቅ ሌሎች የልማት ሥራዎች መኖራቸውንና በጊዜው በዜና ይፋ እንደሚደረጉ አስታውቋል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+5
የብልፅግናን ጭካኔ የተመለከቱ ፓራኮማንዶወች በቃን በማለት ወድ ትክክለኛው ማንነታቸው ተመልሰዋል።
➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺➺
..............ሐምሌ09/2018 ዓ.ም
ከእናርጅ እናውጋ ወረዳ እና ከደብረወርቅ ከተማ ከስርዓቱ ጋር ሲያገለግሉ የነበሩ የአማራ ልጆች ሴራው ገብቶናል በማለት ወደ ፋኖ 74ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉት፦
1ኛ.ሸጋዉ አበበ....... ፓራ ኮማንዶ
2ኛ.ክንዱ አዳርጌ... ፓራ ኮማዶ
3ኛ.አስማማው ጫኔ......ሚሊሻ ከእናርጅ እናውጋ እና ከደ/ወርቅ ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል።
በክፍለ ጦር አመራር አቀባበል ተደርጓላቸው የተሀድሶ ስልጠና እየተሰጣቸው ሲሆን ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ በሚፈልጉት መንገድ ውሳኔያቸውን በማክበር የሚስተናገድ መሆኑን አሳውቀውናል።
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
በእነማይ ወረዳ የትመን ንዑስ ከተማ የ3 ልጆች እናት በብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደለች!!
64ኛ ክ/ጦር ሀምሌ 09/2018 ዓ.ም
~
በእነማይ እና ሸበል በረንታ ወረዳ የሚገኘው የብልፅግና ወንበር ጠባቂ አገዛዝ ሰራዊት ከፋኖ ጋር ተዋግቶ ማሸነፍ ሲያቅተው ንፁሀንን በአሰቃቂ ሁኔታ እየገደለ ይገኛል።
የአብይ አህመድ አገዛዝ እድሜ ለማራዘም ቅጥረኛ በመሆን የሚያገለግለው በባንዳ ተሾመ ሞላ የሚመራው የእነማይ ወረዳ ብልፅግና ገዳይ ቡድን ትዛዝ አማካኝነት #ሚሊሻ ባየ የተባለ የጠንብ ቀበሌ ተወላድ በየትመን ንዑስ ከተማ በቁርስ ቤት ተሰማርታ ልጆቿን ታሳድግ የነበረች የ3 ልጆች እናት ወ/ሮ ባንቹ አስቻለ ሀምሌ 07/2018 ዓ.ም በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉ ተረጋግጦል።
64ኛ ክፍለ ጦሩ በሚያስተዳድረው ቀጠና የአገዛዙ የጠላት ሰራዊት ሰፍሮ በሚገኝባቸው የወረዳ ከተማና የገጠር ቀበሌዎች ንፁሀንን በመረሸን፣ ሀብት ንብረታቸውን በመዝረፉ፣ በማውደም በህዝባችን ላይ ከፍተኛ በደልና ስቃይ እየፈፀመ ይገኛል። ይህ ገዳይ ቡድን በቢቸና፣ የዕድውሃ፣ መርገጭ፣ የትመን ከተማ፣ ወይራ ጠልማና በማህበረ ብርሃን ቀበሌ ከፍተኛ ዝርፊያ የተፈፀመ ይገኛል።
በማህበረብረሃን ቀበሌ በአገዛዙ ከፍተኛ ውድመትና ዝርፊያ ከተፈፀመባቸው አርሶ አደሮች ውስጥ:-
1ኛ.አቶ ሸጋው ዳመነ ሙሉ የቤት ዕቃ፣ የቤቱን ጣራ፣ የግቢ ቆርቆሮ አጥር እና የኩሽና ቆርቆሮ በመንቀል ከ145 በላይ የጣራ ቆርቆሮ ተዘረፎል
2ኛ.የአቶ ደባሱ አንዳርግ ከ185,000 በላይ የሱቅ ሸቀጣ ሸቀጥ ዕቃ፣ የመኗሪያ ቤት የጣራ ቆርቆሮ በመንቀል እና በመዝረፍ የንፁሀንን ቤተሰቦችን ከመኖሪያ ቤታቸው ሜዳ ላይ በመጣል አረመኔዊ ተግባር አሳይቷል።
በእነማይ ወረዳ የሚገኘው የብልፅግና አገዛዝ ገዳይ ቡድን በንግድ፣ በቁርስ ቤት፣ ሸቃጠ ሸቀጥ፣ ምግብ ቤት እና በግብርና ስራ ተሰማርተው የሚኖሩ ንፁሀንን በማስፈራራትና ዛቻ በመጠቀም እየዘረፈ ይገኛል። የእንደዚህ አይነት የመሳሰሉትን አረመ** ኔዊ ተግባር ከፊት በመሆን የሚመሩ ባንዳዎች ውስጥ:-
1ኛ.ተሾመ ሞላ
2ኛ.ባንዳ ገብሬ መኩሬው
3ኛ.ባንዳ ብናልፍ ሽፈረው
4ኛ.ባንዳ አለምነህ ውሏለም
5ኛ.ባንዳ አብረሃም ውባለ
6ኛ.ባንዳ ጌትነት በቀለ
7ኛ.ባንዳ አበዘው ቼሬ
8ኛ.ባንዳ ምንችል
9ኛ.ባንዳ አብርሃምና ሌሎችም በስም ያልጠቀስናቸው የብልፅግና ቀንደኛ ባንዳዎች ከፊት በመሆን ለአገዛዙ ሰራዊት ትዛዝ በመስጠት ህዝባችንን እያሰቃዩ ይገኛሉ። ከላይ በጠቀስነው ንፁሀን ጭፍጨፋ፣ ውድመት፣ ዝርፊያ እጃቸው የተጨማለቁ የብልጽግና አሳማ ካድሬዎች በሙሉ የአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላቶች መሆናቸውን የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት የሚዲያ ክፍል አሳውቋል። በህዝባችን ላይ በርካታ ግፎችንና በደሎችን እየፈፀማቹህ የምትገኙ የብልፅግና ወደል ባንዳዎች ላይ የክፍለ ጦሩ ቀኘ ሰራዊት አባላት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳሉ።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!!
ሀምሌ 9/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የአርበኛ ዮሐንስ ንጉሡ (የጆን) የትግል እንቅስቃሴ በጎንደርና አካባቢው የሚገኙ በርካታ ወሳኝ ቀጠናዎችን ያካለለ፣ ከባድ ዋጋ የተከፈለበትና የአማራን የህልውና ትግል አቅጣጫ ያስቀየረ ታላቅ የጦር ሜዳ ውሎ ነው።
የእርሱን የትግል እንቅስቃሴና ወታደራዊ ስምሪቶች በዝርዝርና በስፋት እንደሚከተለው እናየዋለን የትግሉ መነሻና የጥምረት ዘመን (የመጀመሪያው ምዕራፍ ከትግራይ ወራሪ ኃይል ጋር የተደረገ ፍልሚያ፦ የትግራይ ወራሪ ኃይል በሥልጣን ላይ በነበረበትና የአማራን ሕዝብ በማንነቱ ምክንያት ጥቃትና አፈና በጀመረበት ጊዜ ጆን ትግሉን ቀደም ብሎ ተቀላቅሏል። በአካባቢው የነበሩ የቁርጥ ቀን ልጆችን በማደራጀትና ግንባር በመፍጠር የአፈናውን መዋቅር ሲታገል ቆይቷል።
የቅርብ ጊዜው የወረራ ጦርነት፦ በቅርቡ በነበረው የሰሜኑ ጦርነት ወራሪው ኃይል የአማራን መሬት ጥሶ ሲገባ፣ ጆን ኃይሉን በማንቀሳቀስ በጠላት ላይ ከባድ የመልሶ ማጥቃት እርምጃዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውቷል። በየቀጠናው የተደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች አርበኛ ዮሐንስ (ጆን) በአንድ ቦታ ብቻ ተወስኖ የሚዋጋ ሳይሆን፣ በየአካባቢው ያለውን የጠላት እንቅስቃሴ እያጠና ፈጣን ስምሪት የሚያደርግ የተንቀሳቃሽ ጦር መሪ ነው። እንቅስቃሴዎቹ በተለይ በእነዚህ ቀጠናዎች ላይ ጉልህ ታሪክ ጥለዋል በአርማጭሆ፣ በጠገዴና በበለሳ ቀጠና፦ ይህ ቀጠና የጆን የትውልድና የአያቶቹ የአርበኝነት ምድር በመሆኑ፣ አካባቢውንና ተፈጥሯዊ ምሽጎቹን ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። በአርማጭሆና በጠገዴ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖችና ወንዞችን በመጠቀም ጠላት እንዳይንቀሳቀስ ደፈጣ ውጊያዎችን በመምራትና የስንቅና የትጥቅ መስመሩን በመቁረጥ ይታወቃል።
በመተማና በቋራ ቀጠና የድንበር ጥበቃና ትጥቅ የመተማና የቋራ መስመር ለትግሉ የስትራቴጂክ ጠቀሜታቸው እጅግ ከፍተኛ ነው። ጆን በእነዚህ ቀጠናዎች በመንቀሳቀስ የድንበር ደህንነትን ከማስከበር ባለፈ፣ ለታጋዩ ኃይል የሚያስፈልጉ የትጥቅና የሎጂስቲክስ መስመሮች እንዲከፈቱና በታማኝነት እንዲጠበቁ አድርጓል። በአለፋ፣ በደንቢያና በወገራ ቀጠና (የመከላከልና መልሶ ማጥቃት ጠላት የአማራን ከተሞች ለመውረርና ሕዝቡን ለመጨፍጨፍ ሲመጣ፣ ጆን ጦሩን በማስተማገን በአለፋና በደንቢያ ለጥ ያሉ ሜዳዎች ላይ እንዲሁም በወገራ ተራራማ ሰንሰለቶች ላይ ስትራቴጂካዊ ውጊያዎችን አድርጓል። ይህም ጠላት በዋና ዋና መንገዶች ላይ ያለ ምንም ስጋት እንዳይንቀሳቀስ እግር በእግር ተከታትሎ የመምታት ስልት ነበር።
ወታደራዊ ጥበቡና የአመራር ብቃቱ በደፈጣና ፈጣን ማጥቃት (Guerrilla Warfare) የጆን አንዱ ትልቁ የጦር መሪነት ብቃት ጥቂት የሰው ኃይልና መሣሪያ ይዞ፣ ሰፊ ዝግጅትና ዘመናዊ መሣሪያ የያዘን የጠላት ሰራዊት በድንገተኛ ጥቃት መበተን መቻሉ ነው። የንብረትና የትጥቅ ምርኮ፦ በጦርነቶቹ ወቅት ከመከላከያነት ባለፈ ጠላትን እያባረረ በመምታት፣ ከባድና ቀላል የጦር መሣሪያዎችን በመማረክ የራሱን ታጋዮች እንዲታጠቁና እንዲጠናከሩ አድርጓል።
ከሕዝብ ጋር መተሳሰር፦ ጆን የትም ቦታ ሲንቀሳቀስ በቅድሚያ የሕዝቡን አመኔታና ፍቅር ያተርፋል። ሕዝቡ ስንቅ እንዲያቀብል፣ ታጋዩን በማደራጀት እንዲህም የትግል እንቅስቃሴ መረጃዎች እንዲሰጥ በማድረግ ረገድ የነበረው የማሳመንና የመቅረብ ብቃት አስደናቂ ነበር። በአንድነት መዋቅር ውስጥ የነበረው ሚና የጆን የትግል እንቅስቃሴ በጦር ሜዳ ውጊያ ብቻ አያበቃም። እርሱ የነፃነት ታጋዮች በተናጠል መዋጋታቸው ለጠላት ጥቃት እንደሚያጋልጣቸው አስቀድሞ ከተረዱት የአማራ ልጆች አንዱ ነው።
ስለሆነም፦ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ የልዩነት ድልድይ መሆን፦ በተለያዩ የጎንደርና አካባቢው ኃይሎች መካከል የነበሩ አለመግባባቶችንና ጥርጣሬዎችን በትዕግሥት ፈቷል። ምሶሶው" መባል በተበታተኑት የትግል ክፍሎች መካከል እንደ ማሰሪያ ገመድ በመሆን፣ የጋራ የአዛዥነት መዋቅር (Command) እንዲፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። ለዚህም ነው ጓዶቹ “የአንድነታችን መሠረት” ወይም ምሶሶው” እያሉ የሚጠሩት።ባጭሩ፦ የጆን የትግል እንቅስቃሴ የነፍጠኝነት ጀግንነትን፣ የወታደራዊ ስልትንና የፖለቲካ ብስለትን አጣምሮ የያዘ ሲሆን፤ የአማራ ሕዝብ ዛሬ ላለው ፅናትና ለመብቱ በቆራጥነት ለመቆም ለደረሰበት ደረጃ ትልቁን አስተዋጽኦ ያበረከተ ታጋይ አታጋይ ወንድማችን ጀግናችን ፈጣሪ ይጠብቅህ #Dave #Amhara
"የአማራ ህዝብ ህልውና ጥያቄዎች ለድርድር የሚቀርቡ አይደሉም፡ ትግላችን ስር ነቀል የስርዓት ለውጥ እስኪመጣ ድረስ ነው" የምኒልክ ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ‼️
በአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሞገስ አባራው፡ የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የሚያነሳቸውን የማይታጠፉና የማይደራደርባቸውን መሰረታዊ የትግል ምሰሶዎች በሚል በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው ፅሁፍ፡ የአማራ ህዝብ ህልውና ጥያቄዎች ለድርድር የማይቀርቡና ስር ነቀል የስርዓት ለውጥ እስኪመጣ ድረስ ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅንኦት ገልጿል
አርበኛ ሞገስ የፋኖ ህዝባዊ ትግል መነሻ እነዚህ የህዝብ ጥያቄዎች መሆናቸውን በመጥቀስ፡ ዘላቂው መፍትሄ አራት ኪሎ ያለውን ፀረ-አማራ አገዛዝ ስርዓት በማስወገድ ህዝባዊ መንግስት መመስረት ብቻ እንደሆነ ነው የገለፀው።
አርበኛ ሞገስ አባራው በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ባስተላለፈው መልዕክት፡ የመጀመሪያውና ዋነኛው ጥያቄ የአማራ ህዝብ ሰብአዊ መብትና የህይወት ዋስትና መከበር ነው ብሏል።
ማንኛውም አማራ በሀገሪቱ ምድር በነጻነት የመኖር፣ የመንቀሳቀስ፣ የመስራትና ንብረት የማፍራት መብቱ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ሊከበር እንደሚገባ የገለጸው አርበኛው፡ በመንግስታዊ መዋቅር ጭምር የሚፈፀመው ስልታዊ ጥቃትና አድሎ በአስቸኳይ መቆም እንዳለበት አሳስቧል።
ይህንን መብት በዘላቂነት ለማስጠበቅ ደግሞ አማራውን እንደ ባዕድና ጠላት የሚፈርጁ፡ በፀረ-አማራነት መንፈስ የተቃኙ የፌደራልና የክልል ህገ-መንግስት፣ ፖሊሲዎችንና መመሪያዎችን ሙሉ በሙሉ መለወጥ ወይም መሰረዝ የሚያስችል የመዋቅርና የህግ ለውጥ መደረግ ይኖርበታል ብሏል።
በፖለቲካው ረገድ፡ የአማራ ህዝብ እንደ ታላቅነቱና እንደ ብዛቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ የኢኮኖሚና ማህበራዊ መዋቅር ውስጥ ተመጣጣኝ ውክልና ሊኖረው እንደሚገባ አርበኛ ሞገስ አስታውቋል።
ሀገር በመገንባት ሂደት ውስጥ የነበረው ሚና ታውቆ የሀገር ባለቤትነቱ በይፋ መረጋገጥ እንዳለበትም አክሏል።
ከፍትሕና ተጠያቂነት አንጻር ደግሞ፡ እስካሁን በአማራ ህዝብ ላይ ለተፈፀሙት ስልታዊ የዘር ፍጅቶች፣ የጅምላ ማፈናቀሎችና ውድመቶች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በሙሉ በህግ ተጠያቂ መሆን አለባቸው ያለው ኃላፊው፡ ተፈናቃዮች ካሳ አግኝተው በክብር ወደ ቀያቸው መመለስና እውነተኛ የሽግግር ፍትህ መረጋገጥ ይኖርበታል ሲል ገልጿል።
የህልውና ትግሉ ሌላኛው ምሰሶ ለአማራ ህዝብ መጠቃትና መፈናቀል ሰበብ የሆኑ፡ ለበርካታ አሥርት አመታት ሲሰበኩ የኖሩ ፀረ-አማራ ጥላቻዎችንና የሀሰት ታሪካዊ ትርክቶችን በህግ ወንጀል አድርጎ ማገድና እውነተኛ ታሪካዊ ትርክቶችን መገንባት እንደሆነ አርበኛው በመልዕክቱ ጠቅሷል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በቀድሞው ስርዓት በፖለቲካ ውሳኔና በኃይል ተነጥቀው የተካለሉትንና ህዝባችን በአራቱም አቅጣጫዎች ማለትም በራያ፣ ወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት፣ መተከል፣ ሸዋ ደራ፣ አዲስ አበባና ሌሎችም አካባቢዎች የሚያነሳቸውን የማንነትና የወሰን ጥያቄዎች ታሪካዊ እውነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ዘላቂና ህጋዊ ምላሽ መስጠት ይገባል ሲል ነው የምኒልክ ዕዝ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊው የገለፀው።
እነዚህን ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስ ደግሞ በፖለቲካ ሴራ የተፈጠረውን የክፍለ-ሀገር ክፍፍል በማስወገድ የአማራን ውስጣዊ አንድነት በጽኑ መመስረትና በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሰረተች እውነተኛ ህዝባዊት ሀገር መገንባት የመጨረሻው ግብ ነው ብሏል አርበኛው።
አርበኛ ሞገስ አባራው እነዚህ ጥያቄዎች የማይነጣጠሉና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን አስገንዝቧል።
አንዱን መርጦ ሌላውን መተው እንደማይቻልና ሰብአዊ መብት ያለ ህግ ዋስትና፣ የማንነት ጥያቄ ያለ ፖለቲካ ውክልና ሊረጋገጥ እንደማይችል ገልጿል።
የፋኖ ህዝባዊ ትግልም እነዚህን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ የተወለደ ቅዱስ ህዝባዊ እምቢተኝነት በመሆኑ፡ ጥያቄዎቹ ለድርድርና ለትርፍ-ኪሳራ ስሌት የማይቀርቡ የትግሉ ቀይ መስመሮች መሆናቸውን አረጋግጧል።
በመጨረሻም፡ የሁሉም ጥያቄዎች ዘላቂ መልስ የሚገኘው አራት ኪሎ ስልጣን ላይ ያለውን ፀረ-አማራ ስርዓት በማስወገድ ብቻ እንደሆነ ያስገነዘበው አርበኛ ሞገስ አባራው፡ አማራ ከህልውና አደጋ የሚወጣው ስር ነቀል የስርዓት ለውጥ በማምጣት ከለላ የሚሆን ሕግ በማውጣትና ህዝባዊ መንግስት በመመስረት የስልጣንና የውሳኔ ባለቤት መሆን ሲችል ብቻና ብቻ እንደሆነ በአፅንኦት ገልጿል።
ለአማራ ህዝብ ህልውና እና ነፃነት በድል ጓዳና ከሚገሰግሰው ፋኖ የሚጠበቁ ቁልፍ ነገሮች:-
**
በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ እኩልነት፣ ፍትሃዊነት እና ሰላም የሰፈነባት ሀገር እና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ድርጅታዊ አሰራርን በጠበቀ መንገድ ሁልጊዜም በጽናት መታገል እና አንድነት ወሳኝ ቁልፍ መሳሪያዎች ናቸው ።
ይህንን ታላቅ ህዝባዊ ዓላማ ዳር ለማድረስ ግን አሁን በትግል ላይ ያለው አመራርና እና ጀግናው ሰራዊታችን ወጥ አስተሳሰብ፣ የጋራ ራዕይ፣ ግልጽ ተልዕኮ እና የማይናወጥ ግብ ሊኖረው ይገባል።
👉 ወንዛዊነት ይውደም፤ ብሔራዊ አንድነታችን ይለምልም!
ጠላቶቻችን እኛን ለመደምሰስ የሚንቀሳቀሱት የአማራነት ማንነታችንን እንጂ የሸዋ፣ የጎንደር፣ የጎጃም ወይም የወሎ ልጆች መሆናችንን መርጠው አይደለም። ጠላት ሲገድለን በአማራነታችን ብቻ ነው። ስለዚህ የእኛ መዳኛም ሆነ ድላችን የሚረጋገጠው በወጥ አማራነታችን እና በአንድነታችን ብቻ ነው።
▸የወንዛዊነትን ጠባብ አጥር እንስበር!
▸ለጋራ ድርጅታዊ መርሆዎች እንገዛ!
▸የበታች ለበላይ መሪዎች ያለውን መከባበርና ወታደራዊ ዲሲፕሊን እናጥብቅ!
🔑ጠላታችን በሞራልም በተግባርም ውድቀት ላይ ነው።
የአማራን ህዝብ ህልውና ለመቅጨት የተነሳው የአገዛዙ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ህዝባዊ ቅቡልነቱን ያጣ፣ በሞራልም ሆነ በተግባር ክስረት ውስጥ የገባና የተሸነፈ ኃይል ነው። ይህንን የከሰረ ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማንበርከክ የሚያስፈልገን ብቸኛው መሳሪያ የተዋሃደ ሰራዊት እና በአንድ አቅጣጫ የሚመራ ጠንካራ አመራር መፍጠር ብቻ ነው።
እኛ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ታጋዮች በጉዟችን ሁሉ :-
⤵የወጣንለትን የተጨቆነ ህዝባችንን ከጥቃት መጠበቅና ማክበር ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
⤵የሌሎች ወንድም ህዝቦችን ባህል፣ ቋንቋ እና እምነት ማክበርና ማስከበር የአማራነት መለያችን ነው።
⤵ዋነኛ ጠላታችን የአማራን ህዝብ እያጠፋ ያለው ፣ ህዝብን እርስ በርስ የሚያጋጨው እና ሀገርን እያፈረሰ ያለው የብልጽግና አገዛዝ በመሆኑ፣ ትኩረታችንና መሣሪያችን ሁሉ ወደዚህ አምባገነን ሥርዓት ላይ በማነጣጠር ጉዟችንን ማፍጠን ይጠበቃል።
"አንድ ዓላማ፣ አንድ መስመር፣ አንድ አቅጣጫ!"
በአማራነት ወጥ በሆነ ራዕይና ተልዕኮ ወደፊት በመገስገስ የህዝባችንን ህልውና እናረጋግጣለን!
ድል ለአማራ ህዝብ! የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝት መምሪያ አርበኛ አከበር ስመኘው
