uk
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Відкрити в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Показати більше
2 936
Підписники
+1424 години
+3877 днів
+38530 днів
Архів дописів
አሳዛኝ ዜና የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ተቃጠለ። ሐምሌ/ 24/2018 ዓ.ም የአማራ ህዝብን በመጨፍጨፍ፣ ሀብትና ንብረቱን ማውደም የዘወትር መገለጫው የሆነውና ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፣ የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆችን መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ማቃጠሉ ታውቋል። በራሱ ህዝብ ላይ ታንክ፣መድፍና አየር ኃይል አሰማርቶ ንፁሃንን የሚጨፈጭፈው፣ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ፣ መሀመድ ተሰማ ለምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሚያለም ለሚባል ቅጥረኛ ግለሰብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መኖሪያ ቤቱ መቃጠሉን ከመረጃ ምንጮቻችን ለማወቅ ተችሏል። በቃጠሎው የደጋ ዳሞት ወረዳ፣ የአገዛዙ ቅጥረኛ ካድሬዎችና የሚሊሻ አባላት እንደተሳተፉ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በቤቱ ውስጥ ይገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ሌሎች ጠቃሚ ንብረቶች በእሳቱ መውደማቸው ታውቋል። በፈረስ ቤት ከተማ፣ ቀበሌ 02 ይገኝ የነበረው ይህ መኖሪያ ቤት፣ የአርበኛው ወላጆች ኑሯቸውን መስርተው፣ማኀበራዊ ህይዎታቸውን ይመሩበት እንደነበረ ተገልጿል። ላለፉት 3 አመታት በተለያዩ የአማራ ቀጠናዎች ከፋኖ ጋራ ፊት ለፊት ተዋግቶ ማሸንፍ ያልቻለው አገዛዙ፣ የበቀል ዱላውን የሚያሳርፈው ንጹሃን ዜጎችን በመገድልና ሀብት ንብረታቸውን በማውደም እንደሆነ ይታወቃል። በአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች ቤት የደረሰው ቃጠሎ የዚህ አንድ አካል ነው። ከውጊያ ቀጠና ውጭ የሚገኙ የሰላማዊ ዜጎችን ሀብትና ንብረት ማውደም፣ በዓለም አቀፉ የጄኔቫ የጦር ስምምነት( Geneva War Convention) መሰረት በጦር ወንጀልነት ሊያስጠይቅ የሚችል መሆኑንን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያዎች ገልጸዋል። ቃጠሎውን አስመልክቶ፣ ፈረስ ቤት ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በስልክና በአካል ያነጋገርናቸው ሰላማዊ ዘጌጎች ድርጊቱን በጥብቅ አውግዘውታል። አንድ አገር እመራለሁ ከሚል አካል ፍፁም የማይጠበቅ "ወራዳ ተግባር" ሲሉ ኮንነው፣ አገዛዙ ምን ያህል የመንግስትነት ቁመናው እንዳጣና ተስፋ እንደቆረጠ ማሳያ ነው ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል። አገዛዙ በጎንደር፣ በወሎ፣ በሸዋና በጎጃም ላለፉት 3 ዓመታት የተለያዩ የፋኖ ቤተሰቦችን ሀብት ንብረት ሲያወድሙ እንደቆዩ ይታወቃል። ምስል- የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች መኖሪያ ቤት ከመቃጠሉ ጥቂት ቀደም ብሎ። ምስሉ የደረሰን ከመረጃ ምንጮቻችን ሲሆን ጣራውን፣ በሩንና መስኮቱን በመነቃቀል ለቃጠሎ ካዘጋጁት በኋላ ነው። የተቀረው ምስል- አርበኛ ዝናቡ ልንገረው ከወላጅ አባቱና ከወንድሞቹ ጋራ ።

ማንኛውም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን የ24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ አስታወቀ። ሐምሌ23/2018 ዓ.ም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ለአለፉት ሦስት አመታት በተደረገው ህዝባዊ ተጋድሎ አኩሪ ድል በማስመዝገብ ደማቅ ታሪክ የጻፈው የጮቄው ማማ ደባይ ጮቄ ሻለቃ የሦስት አመት የድል ግስጋሴውን በዛሬው ዕለት በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በደብረ ማርቆስ፣ቁይ፣ ሉማሜ፣ ደብረወርቅ ፣ቢቸና፣ ውሃበር፣ ሰዴ፣ መካነሰላም ፣የቦቅላ በተደረጉ ጠንካራ ውጊያዎች ተሳታፊ በመሆን ጀብድ የፈፀመው የ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ የአለፉ ድሎችን በማስጠበቅ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ቴዎድሮስ ዕዝ በመልሶ ማደረጃት አዲስ አመራር ማዋቀሩ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት የሻለቃ አመራሮችና የሰራዊት አባለት ህግና ስነ-ስርዓትን በማስቀደም ከድርጅታቸው ጎን እንደሚሰለፉ ገልጸዋል የአፋብን አመራሮች፣ የኮርና የክ/ጦር አመራሮች በተገኙበት የሦስት አመት የድል በዓል በድምቀት የተከበረ ሲሆን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሃግብሩ ተጠናቋል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት

ቀን 23/11/2018ዓ.ም     አፋብን ወለጋ -ቢዛሞ ቀጠና አንሻ ሰይድ እዝ ፦ ይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር ።      በአደረገው የተጠና ኦፕሬሽን በኪረሙ ወረዳ ስር የማገኙትን ቀበሌዎች፦ ቦቃ ቀበሌ  ፣ነጭሎ ቀበሌ ፣ወዴሳ ዲማ ቀበሌ እና ሀሮ አዲስ አለም ከተማን መቆጣጠር ተችሏል ።በዚህ በተጠና አውደ ውጊያ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት እና የክልሉ ጥምር ሃይል ሙት እና ቁስለኛ ሁኖ ወደ ኪረሙ ወረዳ ሸሽቷል ።       የጥላት ሃይል የተደመሰሰ 36 ሲሆን የቆሰለ 42ናቸው ።በዚህ አስደንጋጭ ምት የተበሳጨው የአገዛዙ ሰራዊት እንደለመደው ንፁሃንን በከባድ መሳሪያ ሲደበድብ ውሏል በልዩ ቦታዋ ወደሳ ዳማ ቀበሌ ላይ ሰወስት የ13፣የ15እና የ16አመት  ልጆችን በግፍ አማራ በመሆናቸው ብቻ እረሽኗቸው ሸሽቷል ።ውጊያውም  ቀኑን በሙሉ የዋለ ሲሆን ጥላትን አይበገሬወች የይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር አቀጡ ቅጣት ሲቀጣ ውሎ ጨለማ ገላግሏቸዋል ።         በተጨማሪም የአገዛዙ ስራዊት ከሆሮ ጉዱሩ አቤ ዶንጎሮ ተነስቶ ወደ ኪረሙ እገዛ ለማረግ በጉዞ ላይ ሳለ የጌጤ ግርማ መብረቁ ክ/ጦር መንደር 21 ቀበሌ ልዩ ቦታዋ አንገር መድሃኒያለም ላይ በደፈጣ በመጣል አምስት የአገዛዙን አሽከሮች አመድ አዲርጎ አስቀርቷቸዋል ጥላትም ወደ መጣበት ተመልሷል ።ዛሬ ጧት አነጋጉለይ የይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር እና የአንገር ጉቴን ክ/ጦር በጥምር ተቀናጂተው በኪረሙ ወረዳ ቆፍቆፌ ከተማን ተቆጣጥረዋል ።ጥላትም ወደ ጊዳ ወረዳ ሙት ና ቁስለኛውን ይዞ እግሬ አውጭኝ በማለት ሸሽቷል ።       ህልውናቺን በተባበረ ክንዳቺን        አፋብን ወለጋ(ቢዛሞ )አንሻ ሰይዲ እዝ  ምክትል እና         ይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር ዋና ቃል አቀባይ

🔴 ሰበር ዜና፡ በኤፍራታና ግድም ቀጠና የተሰማራው የጠላት ኃይል ክፉኛ እየተመታ ይገኛል!! ሀምሌ 24/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ኤፍራታና ግድም በትላትናው ዕለት በላይኛው አላላ ቀበሌ ልዩ
+2
🔴 ሰበር ዜና፡  በኤፍራታና ግድም ቀጠና የተሰማራው የጠላት ኃይል ክፉኛ እየተመታ ይገኛል!!     ሀምሌ 24/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ኤፍራታና ግድም  በትላትናው ዕለት በላይኛው አላላ ቀበሌ ልዩ ቦታው "ከሰያት" በተባለችው ስትራቴጂካዊ ምድር ለዘረፋና ለወረራ የተሰማራው የገዥው አገዛዝ ኃይል፣ በጀግኖቹ የትጥቅ ትግል አበጋዞች  የቃጠሎ ምት እያስተናገደ ይገኛል። በቀጠናው የወረራ ዓላማ አንግቦ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል የመከቱት የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በላቀ ወታደራዊ ሳይንስና ቅንጅት ሁለት አይበገሬ ሻለቆች በጋራ ደቁሰውታል። በዚሕም የ103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን ባልጠበቀው ሰዓትና ቦታ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር በማዋል፣ የመጣበትን ወታደራዊ የሰውና ቁሳቁስ ኃይል እያንበረከኩት ይገኛሉ። ስበር ሻለቃ እና ናሁ ሰናይ ሻለቃ በተለያየ አቅጣጫ ተሰልፈው ያሰበውን የወረራ እና ዘረፋ ዓላማ ከንቱ በማድረግ፣ በየአቅጣጫው የተበተነውን የጠላት ኃይል እያደኑ መብረቃዊ ምት እየሠጡት ይገኛሉ። ውጊያው ከቀኑ 6:30 ጀምሮ የተቀጣጠለ ሲሆን፣ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በከፍተኛ ወታደራዊ ብልጫና የበላይነት እየተካሄደ ይገኛል። ቀጠናውም በጀግኖቹ ፅናትና ብቃት በሚያሳይ መልኩ ሙሉ ቁጥጥር ስር እየዋለ ይገኛል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

3ኛ. በሴረኞች ክፉ ሃሳብ ሲሞሉ እየዋሉ እውነታውን በትክክል ለመረዳት እድል ያላገኙ ታጋዮችን፤ 4ኛ. እውነቱ ገብቷቸው ከቁም እስረኛ ባልተናነሰ መልኩ የመውጫ መንገድ የጠፋባቸው አካላት፤ በሴረኞች ተዘጋጅቶ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ/ም የሰጡት መግለጫ በትክክል ከአማራ ህዝብ ፍላጎት በተቃራኒ መሆናቸውንና የአማራ ህዝብ ተደስቶ የአማራ ጠላት ከሚከፋው የአማራ ጠላት ቢደሰት ይሻላል ብለው በህዝባችን ደስታ ላይ ውሐ ለመቸለስ ሲሞክሩ በግልፅ ታይቷል። በመሆኑም ብንታገስ ብንታገስ በህዝባችን የህልውና ትግል ላይ አንታገስምና ይህ ጉዳይ የመጨረሻ እልባት ያገኝ ዘንድ የሚከተለውን ጥሪ ለሚመለከታቸው አካላት እናቀርባለን። 1ኛ. የጠላትን አጀንዳ ተሸክማችሁ የጎንደርን አንድነት ለመበተን የምትጋጋጡ ተላላኪዎች:- ጉዳችሁ እንዲህ በአደባባይ እስኪገለጥ ድረስ በዙሪያችሁ ያሉ ንፁሐን ታጋዮች እውነቱ ሳይረዳቸው አብረው እንዳይሳሳቱ በማሰብ እንጂ የእናንተ ሴራ ድሮም ከሰራዊታችን የተሰወረ አልነበረም። ሆኖም በአደባባይ የህዝብ ጠላትነታችሁን ብታሳዩም ከአንድነት በተቃራኒ መሆናችሁን ብትገልፁም እኛ በዙሪያችሁ ስላሉ ንፁሐን ታጋዮች ሆደ ሰፊ መሆን የግድ ነውና ከዛሬ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ባሉ ተከታታይ 3 ቀናት ውስጥ በሚዲያ ለማደናገር የሞከራችሁትን ህዝብ ይቅርታ ጠይቃችሁ ወደ ተመደባችሁበት የስራ መደብ በፍጥነት ገብታችሁ ስራ መጀመራችሁን እንደየ ተጠሪነታችሁ ሪፓርት እንድታደርጉ የመጨረሻ ጥሪ አናቀርባለን። ይህ ሳይሆን ቢቀር በሰራችሁት ሴራ እና በፈጠራችሁት ከፍተኛ ስብራት የተበሳጨ ህዝብም ሆነ ስራዊት በሚወስደው ርምጃ ኃላፊነቱን እናንተው የምትወስዱ ይሆናል። 2ኛ. ለጠቅላላው የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ሰራዊትና አመራር:- በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት በየቀጠናችሁ ከነበሩበት መሰሪ የጠላት አጀንዳ ተሸካሚነት አመለካከት ወጥተው ወደ እናንተ ይቅርታ ጠይቀው የሚመጡትን ያለምንም እንከን በፍቅር ተቀብላችሁ እንድታስተናግዱ እያሳሰብን የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ካለቀ በኋላ የማይመለስና ከፀረ-አንደነቶች አስተሳሰቡ የማይፈወስ ካለ በድርጅትና በዕዙ በየደረጃው የሚወርድላችሁን ትዕዛዝ በተጠንቀቅ ሆናችሁ እንድትጠብቁ እናሳስባለን። 3ኛ. ለመላው የአማራ ህዝብ በተለይ በጎንደር አካባቢ ለምትኖሩ:- እስከ አሁን ድረስ ለምጣዱ ሲባል አይጧ ትለፍ ብለን ዝም በማለታችን አንድነት አዘግይተን ያደረስንባችሁን ፈተና የተራዘመ መከራ በማሰብ በተደጋጋሚ ይቅርታ መጠየቃችን ይታወቃል። ዛሬ ግን አስከመኸር በመታገሳችን ስንዴው ከእንክርዳዱ፣ ፍሬውን ከገለባ የሚለይበት ጊዜ ደርሶ የፈተናችሁን ምንጭ በአደባባይ አይታችኋል። እኛ ዛሬም እንደ ትላንቱ ችግሮችን በረቀቀ ጥበብ ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት እያደረግን እንገኛለን። ነገር ግን ከዛሬ ጀምሮ አንድነታችን በመደገፍ ከአንድነት በተቃራኒ የሚቆሙ ፀረ-አንድነት ግለሰቦችና የትግል ጎታቾች የመጨረሻ እድላቸውን ተጠቅመው ወደ ልቦናቸው ይመለሱ ዘንድ እንድትመክር በታላቅ አክብሮት ጥሪ እናቀርባለን። 4ኛ. ለትግሉ ደጋፊ ሚዲያ አካላት:- የአማራ ትግል ወደ ላቀ ደረጃ እንዲደርስ የሚዲያ ሚና ቀላል አይደለም። ለትግሉ ድጋፍ አውንታዊ ሚና እንደተጫወተ ሁሉ ለተንኮለኞች ልሳን በመሆን ለትግሉ ተግዳሮት በመሆንም ሚዲያው የራሱ ድርሻ አለው። በመሆኑም በዚህ ወቅት ከሚዲያ የምንጠብቀው የህዝቡን ፍላጎትና ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ትግሉ ከፍ እንዲል ታጋዩ እንዲግባባና አንድ እንዲሆን ከመስራት ባሻገር  ከፋፋይ የሆኑ የከሰሙ ስያሜዎችን ከመጠቀም እንድቆጠቡ ጭምር  እናሳስባለን። በአጠቃላይ የአማራ ጠላቶች እንደሚፈልጉት የሚሆንበትን የአማራ መከራ ለማሳጠር፤ የጠላትን ቅስም ለመስበር፤ የወገንን ክንድ ለማጠንከር ሲባል በአማራ ትግል ውስጥ የገቡ ትግል ጠላፊ ረጃጅም እጆች ይቆረጣሉ፤ በትግላችን ውስጥ የተሰገሰጉ ተላላኪ ባንዳዎች ተመንጥረው ይወጣሉ፤ ህዝባችን ማህበራዊ እረፍት የሚነሱ ዘራፊዎችና አጋቾች አደብ ይገዛሉ፤ የአማራ ፋኖ አንድነት ወደ አስገራሚ እምርታ ያድጋል። እስከዚያው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚችለውን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ እናቀርባለን። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የእዛችን ጥንካሬ ለድርጅታችን ዋስትና ነው! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ስራ አስፈፃሚ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ/ም

ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም “የጠላትን ቅስም በመስበር የአማራን ህዝብ የመከራ ጊዜ እናሳጥራለን” ከአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የሰማዕታት አንድነት ጉባኤ ''በድርኳዜ'' የተሰጠ የመዝጊያ መግለጫ። እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ በከበባ ውስጥ ገብቶ የህልውና አደጋ ተጋርጦበት ይህንን የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ከፍተኛ ትንቅንቅ እያደረገ ይገኛል። አጠቃላይ ስርዓቱን ለመጣል በሁም የአማራ አካባቢዎች ከፍተኛ ትንቅንቅ እየተደረገ ሲሆን፤  በቅርቡ የጎንደር አንድነት እውን ይሆን ዘንድ ደግሞ በደንቢያ ፣በጎንደር ዙሪያና ወገራ አካባቢዎች ዕልፍ ወንድሞችን ገብረናል። ይህ ትግል ከፍተኛ ዋጋ የተከፈለበትና እየተከፈለበት ያለ ቢሆንም በየጊዜው ከፍተኛ ለውጦችን እያመጣ እጅግ የተሻለ የእድገት ደረጃ ላይ መሆኑ ለማንም ግልፅ ነው። በዚህ የህልውና ትግል ውስጥ ጠላትን በተደጋጋሚ ማንበርከክ ተችሏል። የጠላትን ሎጅስቲክ በመማረክ የወገንን የትጥቅ አቅም በአስደማሚ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል። ከዚያም አልፎ በቀጠናው ተስፋ የሚጣልበት ተገዳዳሪ ኃይል እየሆነ ምጣቱ የአደባባይ ምስጢር ነው። ይሁን እንጂ የሀገሪቱን ባንክና ታንክ ይዞ በጦር ሜዳ የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው ጠላት ትግሉን በተለየ መልኩ ለመጥለፍና እድሜውን ለማራዘም በተደጋጋሚ ሲኳትን ይስተዋላል። ከዚህም በተጨማሪ ህልውናቸውን በአማራ ህዝብ ጥቅም ላይ ያደረጉ አማራ ጠል ግለሰቦችና ድርጅቶች የአማራ ፋኖን በዚህ ልክ መጠናከር እንደስጋት በመቁጠራቸው በመካከላችን ልዩነት በመፍጠር ያለዕረፍት ሲቃትቱ ይስተዋላል። እነዚህ የአማራ ህዝብ ጠላቶች በመናበብ በትግላችን ውስጥ ረጃጅም እጃቸውን እያስገቡ ለማደናቀፍና ትግላችን ለማክሸፍ ቢሞክሩም ትንሽ ጊዜ ጎተቱን እንጂ ውድ ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን የአማራ ትግል መድረስ ካለበት ከፍታ መድረሱ አልቀረም። ግለሰቦች ውስጣዊ አንድነት እንዳይኖር አንዱን በአንዱ ላይ ማስነሳትና የማይጠገኑ የሚመስሉ ስብራቶችን መፍጠር፣ እንዲሁም አንድነትና ውህደት እንዳይፈጠር ሰበቦችን እየፈጠሩ አጥብቆ መቃወም፤ ይህ ከእጃቸው የወጣ ሲመስላቸው ከፋፋይ መግለጫ በየሚዲያው በመንዛት ለአመታት ሲታገሉን ኖረዋል። ሰሞኑን ድርጅታችን አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ባወረደው ትዕዛዝ መሰረት  የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የአንድነት ምስረታ ላይ ለመፍጠር የሞከሩትም ይሔው ነበር። ትግሉ ከተጀመረ ጀምሮ ላለፉት 3 ዓመታት የተደረጉ የአንድነት ሙከራዎች ላይ ያደረሱብንን ፈተና ሳይጨምር ሰሞኑን ብቻ በአካል ተገናኝተን የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት የበላይ ዘለቀ እዝ አንድነት ምስረታ የተደረገውን ጉዞ ለማደናቀፍ ጠላቶቻችን ወገን ውስጥ አስርገው ባስገቧቸው አጀንዳ ተሸካሚ ግለበሰቦች በኩል እየተፈተነ ያሳለፋቸውን ፈተናዎች በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል:- ከአፋብን ምስረታ በኋላ በድርጅቱ አቅጣጫ መሰረት ሁሉም እዞች ውህደትና የስራ አስፈፃሚ ሽግሽግ እንዲደረግ በከፍተኛ ትኩረት ተሰርቷል። የድሮው የበላይ ዕዝም የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ባሉበት ጭምር ተደጋጋሚ የአንድነት ውይይቶችን አድርጓል። ብዙ ውሳኔዎች ተላልፈዋል ብዙ ቀጠሮዎችና ቀነ ገደቦች ተቀምጠዋል። ነገር ግን በልዩ ልዩ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቶ የመጨረሻ ውሳኔ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ በአንድ ማዕከል ለመገናኘት ወስኖ ሁሉም ጉዞ ጀምሯል። በዚህ ውሳኔ መሰረት በቃሉ የፀናውና ቁርጠኛ የሆነው ሁሉንም የመደበኛ ጠላት ከበባና የፀረ-አንድነቶችን ሴራ እያለፈ ወደ ተቀጠረው ቦታ ሲደረስ ጸረ-አንድነት ግለሰቦች የመንቀሳቀሻ ቦታዎችን ለጠላት በማመላከት ቢያሳድዱንም እኛ ግን  ከሚካኤል ደብር ወደ ሊቦ ከዚያም ወደ ባጃ በሚል ቦታውን በመቀየር ምክንያት እንዳይኖራቸው በማድረግ ተለዋጭ ቦታ ለመምረጥ  የአንድነት ፈላጊው  ወሰነ፡፡ በመጨረሻም የሚከፈለውን መሰዋዕትነት በመክፈል ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ/ም ምዕራብ በለሳ ወረዳ ባጃ ማዕከል የተገኘ ሲሆን ከተለያዬ ቦታ ለሳምንታት ተጉዞ የትግል ጓዱን ለመገናኘት የናፈቀው አካል ለአንድ ሌሊት እንኳን ረፍት ሳያደርግ ቦታው ላይ እንደገባ ፀረ-አንድነት ግለሰቦች ቦታውን በጠላት ከበባ በማስገባት በአመራር ላይ ጉዳት ለማድረስ ያደረጉት የሴራ እቅድ በአመራሮች ብቃት ጠላትን ሰብሮ መውጣት ተችሏል፡፡ በዚህ ሁኔታ የተመረጠው ቦታ ለፀረ አንድነቶችና ተልኮ ተቀባዬች ምቹ እንደሆነ የገባው አመራርና ሰራዊቱ ተወያይቶ የቀጠና ለውጥ አድርጎ ከሰኔ 25 እስከ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ሌላ 3ኛ መገናኛ ማዕከል (ገላ ማጠቢያ) በመሄድ አሁንም በትዕግስትና በሆደ ሰፊነት ከቀጠና ቀጠና ብንከራተትም በውሳኔአችን መሰረት ወደ ተመረጠው ማኢከል እንዲመጡ ያላሰለሰ ጥረት ቢደረግም በቅንነት ሊመጡ አልቻሉም፡፡ ነገር ግን ሁሉም የፋኖ ሰራዊት፣ የትግሉ ደጋፊና ማህበረሰባችን ወደዚህ ጉባኤ ሂደው ችግሮችን ገምግመው እንዲፈቱ ጫና ሲያደርግባቸውና አፍራሽነታቸው በሁሉም ዘንድ እየታወቀ ሲመጣ የአንድነት ኃይሉ ወዳለበት ቦታ ሰኔ 28 ቀን ጠላትን ጎን ለጎን አሰልፈው በመምጣት የተጀመረውን የአንድነት ጉዞ አሁንም ለማስተጓጎል ችለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ከ3ኛ የጉባኤ ማዕከል ወደ ሌላ 4ኛ የጉባኤ ማዕከል ለመሄድ ተገደናል፡፡ የነበርንበትን ቦታ በጠላት እንዲያዝ ካደረጉ በኋላ ፀረ-አንድነቶች ወደኋላ ሲመለሱ ትዕግስቱን አሟጦ የጨረሰው አመራር ከሰኔ 28 እስከ ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ/ም 4ኛ የጉባኤ ማዕከል መርጦ ድጋሜ ተገናኝቶ በመወያየትና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መገኘት ያልቻሉትን ነገር ግን አንድነቱ በአካል በተገኘው ጉባኤ እንዲጠናቀቅ የሚፈልጉትን በስልክ በማማከር ይሁንታ ተገኝቶበት ምልዓተ ጉባኤው የተሟላ መሆኑን በማረጋገጥ እና በመፈራረም የአንድነት ጉባኤውን ማስጀመር ተችሏል፡፡ እውነት ጠርቶ ይወጣ ዘንድና በሴረኞች የተሳሳተም ሆነ በጥርጣሬ ሲወዛገቡ የነበሩ አካላት ጊዜ ያገኙ ዘንድ አሁንም ከሀምሌ 6 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ተጠብቀው የፀረ-አንድነቱ ግለሰቦች ሴራ በመበጠስ የአንድነት ጉባኤውን ተቀላቅለዋል የስራ አስፈፃሚ ድልደላ የሚሳተፉ የቴክኒካል ኮሚቴ ውስጥም ተካተዋል። በዚህ ሁሉ እድል ከብዙ እርቀት ከፍተኛ መስዋዕትነት እየከፈሉ ከልብ አንድነት ፈላጊዎች የመጡና የተሳተፉ ቢሆንም ዋና የጠላት አጀንዳ ተሸካሚዎቹ ፀረ-አንድነቶች ግን በጣም ቅርብ ርቀት ሆነው እንኳን ለመምጣት ፈቃደኛ አልሆኑም። የአንድት ስራችን አሁንም በዚህ 5ኛ ጉባኤ ቦታ ላይ ስንጀምር ጠላት ከፀረ-አንድት ግለሰቦች በሚደርሰው መረጃ ሌሊት ከበባ በማድረጉ ምክንያት አላማችን አንድነቱን ማሳካት በመሆኑ ምክንያት አሁንም ወደ ሌላ 6ኛ ቦታ እንድንቀይር ተገደናል፡፡ በመጨረሻም ከሀምሌ 9 እስከ 18/2018 ዓ/ም ድረስ የተዋቀረው የቴክኒክ ኮሚቴ አካታች የሆነ ብቻ ሳይሆን ምክንያት እንዳይኖራቸው በማሰብ ከአንድነት ተፃራሪ ሐሳብ ያላቸውን ጸረ-አንድነት ግለሰቦች ጭምር ያካተተ የስራ አስፈፃሚ ድልድል አጠናቆ በስራ አስፈፃሚ አስወስኖ በጉባኤ አፀድቆ በድርጅቱ በኩል ይፋ አድርጓል። ነገር ግን ያደቆነ ሰይጣን -----እንዲሉ ምንም ቢደረግላቸው ከላኪወቻቸው የጠላት አጀንዳ መመለስ ያልፈለጉት እነዚህ የትግሉ እዳዎች፡- 1ኛ. አንድነቱ እንዳይመጣ ጠላት በተልዕኮ ያስቀመጣቸው አካላት፤ 2ኛ. በተለያየ ወንጀል የተዘፈቁና መዝረፍ የለመዱ ነገ በሰራነው ወንጀል እንጠየቃለን የሚል ስጋት ያለባቸው ግለሰቦች፤

ማንኛውም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን የ24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ አስታወቀ። ሐምሌ23/2018 ዓ.ም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ለአለፉት ሦስት አመታት በተደረገው ህዝባዊ ተጋድሎ አኩሪ ድል በማስመዝገብ ደማቅ ታሪክ የጻፈው የጮቄው ማማ ደባይ ጮቄ ሻለቃ የሦስት አመት የድል ግስጋሴውን በዛሬው ዕለት በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በደብረ ማርቆስ፣ቁይ፣ ሉማሜ፣ ደብረወርቅ ፣ቢቸና፣ ውሃበር፣ ሰዴ፣ መካነሰላም ፣የቦቅላ በተደረጉ ጠንካራ ውጊያዎች ተሳታፊ በመሆን ጀብድ የፈፀመው የ206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ደባይ ጮቄ ሻለቃ የአለፉ ድሎችን በማስጠበቅ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ቴዎድሮስ ዕዝ በመልሶ ማደረጃት አዲስ አመራር ማዋቀሩ እንዳስደሰታቸው የተናገሩት የሻለቃ አመራሮችና የሰራዊት አባለት ህግና ስነ-ስርዓትን በማስቀደም ከድርጅታቸው ጎን እንደሚሰለፉ ገልጸዋል ። የአፋብን አመራሮች፣ የኮርና የክ/ጦር አመራሮች በተገኙበት የሦስት አመት የድል  በዓል  በድምቀት የተከበረ ሲሆን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሃግብሩ ተጠናቋል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

64ኛ ክ/ጦር በእነማይ ወረዳ ደብረፅሞና ቀበሌ 8 የአገዛዙ ብልፅግና ካድሪ፣ ፖሊስና ሁለት ፖትሮል በቁጥጥር ስር በማዋል ትግሉን ያቀጣጠለበት ልዩ ቀን አከበረ!! ~~~~~ ሀምሌ 23/2015 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ደብረ ፅሞና ቀበሌ 8 የእነማይ ወረዳ የብልፅግና ካድሪ፣ ፖሊስና ከሁለት ፖትሮል ጋር በቁጥጥር ስር የዋሉበት፣ የእነማይ ወረዳ ብልፅግና ስረዓት ማፍረስ የተጀመረበት ልዩ ቀን ሲሆን 3ኛ አመት በአስቆጠረው ክብረ በአል በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ አደረጃጀት ኃላፊ አርበኛ እስቲበል አለሙ፣ የቴዎድሮስ ዕዝ ሚዲያ ባለሙያ አርበኛ ጎጃም አዝመረው፣ የ206 ኮር 34ኛ ክ/ጦር ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ ሀብቴ አደረው፣ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፂ ዘረያቆብ 1ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር አመራር፣ የ64ኛ ክ/ጦር አመራሮችና አባላት እንዲሁም የደብረፅሞና ቀበሌ ማህበረሰብ በተገኙበት ሀምሌ 23/2018 ዓ.ም በደብረ ፅሞና ቀበሌ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል። ሀምሌ 23/2015 ዓ.ም በደብረፅሞና ቀበሌ የተሰባሰቡ ፋኖዎች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመደራጀት በእነማይ ወረዳ የሚገኘውን የብልፅግና ካድሪዎች፣ ፖሊሶች በሁለት ፖትሮል ደብረፅሞና ቀበሌ በቁጥጥር ስር በማዋል ስረዓቱን በማፍረስ ታሪክ የሰሩበት ልዩ ቀን ነው። በእነማይ ወረዳ ከሚገኙ 29 ቀበሌዎች ውስጥ ደብረ ፅሞና ቀበሌ አንዱ ሲሆን የደብረፅሞና ቀበሌ የሚገኙ ፋኖዎች የአማራ ህዝብ በራሱ ሀገር፣ በራሱ እርስት በአገዛዙ እየደረሰበት ያለውን ግፍ፣ በደል ለማስቀረት ራሳቸውን በማደራጀት፣ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ይህንን አስከፊ ስረዓት ገርስሶ ለመጣል ከፍተኛ መስዋትነት በመክፈል ለመለው አማራ ህዝብ የትግሉን ችቦ በመለኮስ የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ የትውልድ ቅየ እነማይን በጀግንነት በማስጠራት ታሪክ የሰሩበት ምድር ነው።        ላናሸንፍ የጀመረነው ትግል የለም!! ድል ለአማራ ህዝብ🔥🔥🔥 ድል ለአማራ ፋኖ🔥🔥🔥 አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!              ሀምሌ 23/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ህዝብ ግንኙነት

ዛሬ በቀን 23/11/2018 ዓ.ም የ10ኛ ክፍለጦር የቃኝና ምሀዲስ ብሬን ተኳሺ የነበረው ወታደር ስማቸው ቃኘው 1ብሬን ከእነ ሙሉ ተተኳሹ በመያዝ የአፋብን ጎጃም/ጠቅላይ/ግዛት/ቴዎድሮስ/ዕዝ/የ206
+1
ዛሬ በቀን 23/11/2018 ዓ.ም የ10ኛ ክፍለጦር የቃኝና ምሀዲስ ብሬን ተኳሺ የነበረው ወታደር ስማቸው ቃኘው 1ብሬን ከእነ ሙሉ ተተኳሹ በመያዝ የአፋብን ጎጃም/ጠቅላይ/ግዛት/ቴዎድሮስ/ዕዝ/የ206ኛ/ኮር የ14ኛ/ክ/ጦር/የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃን ተቀላቀለ::

+3
✊ የቁርጥ ቀን ልጅ የአማራ ፋኖ!!! ​ይህ ታሪክ የሚያወራው ስለ ፍርሃት አይደለም፤ ስለ ክብር፣ ስለ ነጻነትና ስለ ማነንት እንጂ! ​ይህ የአማራ ልጅ ፋኖ ነው! የቀደሙትን የአባቶቹን አሻራ በመከተል—የዳግማዊ አጼ ሚኒልክን ጽናትና ጀግንነት የተላበሰ፣ የጀግናውን የብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌን ወኔና አጥንት ያነገሰ፣ የዘመነ ካሴን የማያወላውል የቆራጥነትን ወኔ በልቡ ያተመ የዘመኑ የነጻነት አርበኛ! ​ይህ ትውልድ በባርነትና በስጋት ለመኖር ፈቃደኛ ያልሆነ የአዲሱ ትውልድ አሻራ ነው። ከጎጃም ተራሮች፣ ከወሎ አምባዎች፣ ከሸዋ ሜዳዎችና ከጎንደር ሰንሰለታማ ተራራዎች ... ከአራቱ ከተለያዩ የማዕዘናት አውራጃዎች በጀግናው አሳምነው የነጻነት ጥሪና ድምፅ እንደ ንስር አሞራ በአንድነት የተሰባሰበ፣ በክብርና በነጻነት በገዛ ምድሩ በህይወት ለመኖር አልሞ የተነሳ ኃይል ነው። ​የዚህ ትግል ዓላማ ግልጽ ነው! በየትኛውም የኢትዮጵያ ማዕዘን የሚኖሩ አማራዎች ከታረዱበት፣ ከተፈናቀሉበትና ከተበደሉበት የሰንሰለት ግፍ ነጻ ማውጣት ነው። ውጊያውም ከዳግማዊ ግራኝ መሐመድ ፈለግ ተከታይ ከሆነውና ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የብልፅግና ሥርዓት ጋር ነው። ​ትላንት በየስበቡ ስም እየሰጣችሁ ህዝቡን ስታባሉ፣ ወገን ሲታረድ በዝምታ ስትመለከቱና ጥቅማችሁን ስታሳድዱ የነበራችሁ ሆዳም አማራዎች... እንግዲህ ከእንግዲህ ሆድ ግዙ! የነጻነት ጎህ ቀዷል፣ የአማራ ህዝብም መብቱን በራሱ ክንድ ለማስከበር ቆርጦ ተነስቷል! #Dave #Amhara

በኦሮሚያ_ክልል_ምስራቅ_አርሲ_ዞን_በተለያዩ_ወረዳዎች_በተፈጸሙ_የሰብዓዊ_መብቶች_260730_122950.pdf1.95 MB

Shared by One Read - an all-in-one file viewer: https://st.simplehealth.ltd/uAJjyu

ይህንን እውነት ላለመቀበል የፈለገ ሁሉ አይን አፍጥጦ ይዋሻል! አማራ መሆን በራሱ ጥበብ ነው! ​አማራ መሆን ዝም ብሎ ተራ ማንነት አይደለም፤ የታሪክ፣ የጽናትና የጥበብ ድርድር ነው። የዚህን ህዝብ
ይህንን እውነት ላለመቀበል የፈለገ ሁሉ አይን አፍጥጦ ይዋሻል! አማራ መሆን በራሱ ጥበብ ነው! ​አማራ መሆን ዝም ብሎ ተራ ማንነት አይደለም፤ የታሪክ፣ የጽናትና የጥበብ ድርድር ነው። የዚህን ህዝብ ጥበብና ምስጢር ያላወቀና ያልገባው አካል ግን “አባይ ወደ ኋላ ይፈሳል” ብሎ ቢከራከር አይገርምም። ምክንያቱም ተፈጥሮንና እውነታን መካድ የሚቻለው የነገሩ ስፋትና ጥልቀት ሲያቅታችሁ ነው! ​ለምን መሰላችሁ? እናንተ ገና የአማራ ህዝብ "የመኖር ነፃነት" ምን ያህል ውድና ጥልቅ እንደሆነ አልገባችሁም። የነፃነትና የክብር ትርጉም የሚገባው ዋጋ ለከፈለበት ብቻ ነው​ከውጭ ሆኖ ለማየትና ለመናገር ቀላል ነው፤ ነገር ግን የደረሰውን ሰቃይ፣ እንግልት፣ መከራና እንባ በቀጥታ የኖርኩበትና የማውቀው እኔ እንጂ እናንተ አይደላችሁም! ያለፍኩበትን እሳት ሳታውቁ ስለ መንገዴ ልታስተምሩኝ አትችሉም። ​የቱንም ያህል ውሸትና ማደናገሪያ ቢበዛ፣ እውነትና የዚህ ህዝብ ጥበብ ሁልጊዜ ጸንቶ ይኖራል! ​#አማራ #የመኖር_ነፃነት #እውነት #ጽናት #ኢትዮጵያ Dave Amhara