🇸🇦'"ከቦሩ ሠላሳ "" ዳዕዋ ሠለፍያ 🇸🇦
Відкрити в Telegram
✋ اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ ተውሒድ የሁለት አገር ብርሃን ነው .!!! التوحيد أولا ከሱፍያ ወደ ኢኽዋንያ ፣ ከኢኽዋንያ ወደ ጀምዒያ ፣ ያደረከው ጉዞ ለለውጥህ መነሻ ሊሆንህ ይችላል እንጅ ንፁኋን ሰለፍያን እስከምትይዝ ድረስ ገና አልተለወጥክም‼️
Показати більше2 183
Підписники
+824 години
+227 днів
-1730 день
Архів дописів
👌 .ስለ ጫት በውድ በይኻችን አቡ ኒብራስ
🔺-----------🔺------------🔺
👌..ቅጥቅጥ ነው ያደረገው ሱሀነክ ይተደሉታል እንጂ አይታገሉትም....❗️
-------
🔺ሸርር ይደረግ በየቤታችሁ ሰው ቲክቶክ ፌስቡክ ላይ ሀራም እና እርም ነገር ነሽር ያደርጋሉ ለወንጀል አጅር ለሌለው ነገር....
🔺እኛ ደሞ ኸይር ዳእዋ አጅር የምንመነዳበትን ነገር ለመነሸር ምን ያዘነጋናል አህባቦች በሉ ሸርርርር
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👇👇 👇👇 👇👇
https://t.me/boruselasa_22
https://t.me/boruselasa_22
🌿⚠️ ስለ ዝሙት ⚠️🌿
﴿ وَلَا تَقْرَبُوا الزِّنَىٰ ۖ إِنَّهُ كَانَ فَاحِشَةً وَسَاءَ سَبِيلًا ﴾
📖 [ሱረቱል ኢስራእ፡ 32]
✨ “ወደ ዝሙትም አትቅረቡ፤
እርሱ እጅግ መጥፎ ሥራ እና ክፉ መንገድ ነው።” ✨
🖋️ ኢብኑ ከሲር رحمه الله እንዲህ ይላሉ፦
“አላህ ‘ዝሙትን አትስሩ’ ብቻ አላለም፤
‘አትቅረቡ’ አለ።
ይህም ወደ ዝሙት የሚወስዱ መንገዶችን ሁሉ መከልከሉን ያሳያል።”
🔹 ሀራም እይታ
🔹 ከሴት/ወንድ ጋር መቀላቀል
🔹 ሀራም ውይይት
🔹 አሳፋሪ ምስሎችና ቪዲዮዎች
➡️ ሁሉም ወደ ዝሙት የሚያቀርቡ መንገዶች ናቸው።
🌱 ዝሙት ልብን ያጨልማል፣
ኢማንን ያዳክማል፣
ቤተሰብን ያፈርሳል፣
የአላህን ቁጣ ያመጣል።
ንፅህና ግን የአማኝ ውበት ናት።
የራሱን ነፍስ ለአላህ የጠበቀ ሰው
በዱንያም በአኺራም ይከበራል።
🤲 اللهم احفظ شباب المسلمين وبناتهم من الفواحش ما ظهر منها وما بطن.
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
https://t.me/boruselasa_22
https://t.me/boruselasa_22
🔴 ማስጠንቀቂያ❌
❌ ከመህረም ያልሆኑ ሴቶች ጋር መጨበጥ አይፈቀድም
📌 መህረም ያልሆኑ ሴቶች (ምሳሌዎች):
የአጎት ልጅ
የአክስት ልጅ
የኻል (የእናት ወንድም) ልጅ
የኻላ (የእናት እህት) ልጅ
የአጎት ሚስት
የኻል ሚስት
የወንድም ሚስት
የሚስት እህት
➡️ እነዚህ ሁሉ መህረም አይደሉም።
❌ ለሴቶችም እንዲሁ
ከመህረም ያልሆኑ ወንዶች ጋር መጨበጥ አይፈቀድም
📌 መህረም ያልሆኑ ወንዶች (ምሳሌዎች):
የአጎት ልጅ
የአክስት ልጅ
የኻል ልጅ
የኻላ ልጅ
የእህት ባል
የባል ወንድም
✅ አስታውስ 👉 ሰዎችን ለማስደሰት አልተፈጠርክም
👉 አላህን ለማስደሰት ተፈጥረሃል
👉 በኃጢአት ውስጥ ለሰው መታዘዝ የለም
📜 ከ ዐይሻ ረዲያላሁ አንሃ ተነግሮ፦
ነብዩ ﷺ እንዲህ አሉ፦
✨ “የአላህን ደስታ በሰዎች መቆጣት ቢሆንም የፈለገ፣
አላህ ይረካበታል እና ሰዎችን ያረካበታል።
✨ የሰዎችን ደስታ በአላህ መቆጣት ቢሆንም የፈለገ፣
አላህ ይቆጣበታል እና ሰዎችን ያቆጣበታል።”
🤲 አላህ በእውነት ያቁመን፣ በሀቅ ላይ ያጽናን
ሸርርርርር
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
🔺https://t.me/boruselasa_22
----------
🔺https://t.me/boruselasa_22
🌿رَبِّ ابْنِ لِي عِندَكَ بَيْتًا فِي الْجَنَّةِ🌹
🔺«ጌታዬ ሆይ! አንተ ዘንድ በገነት ውስጥ ለእኔ ቤትን ገንባልኝ።» (ሱረቱ-ተህሪም፡ 11)
👌➣አስተውለሽ ከሆነ... ይህች ታላቅ ሴት (አስያህ) በምድር ላይ የንግሥትነት ክብርና ድሎት ቢኖራትም፣ ያ ሁሉ አልበቃትም ነበር። በዙሪያዋ የነበረው ግፍና ጭቆና ሳይበግራት፣ የልቧን ጥንካሬ በዱዓ ለጌታዋ ገለጠች።
👌🌹ለ... አንቺም በዙሪያሽ ያለው ሁኔታ ምንም ይሁን ምን፣ ጠንካራ መሆን የምትችዪው ልብሽን ከአላህ ጋር ስታገናኚ ነው። የአንቺ ዋጋ ያለው አላህ ዘንድ ነው፤ ስለዚህ በጽናትሽ ቀጥዪ
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
https://t.me/boruselasa_22
-----------
https://t.me/boruselasa_22
🌹 🌿 ጁምዓ ሙባረክ! 🌿 🌹
﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِذَا نُودِيَ لِلصَّلَاةِ مِن يَوْمِ الْجُمُعَةِ فَاسْعَوْا إِلَىٰ ذِكْرِ اللَّهِ وَذَرُوا الْبَيْعَ ۚ ذَٰلِكُمْ خَيْرٌ لَّكُمْ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ﴾
«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በጁምዓ ቀን ለሶላት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ዝክር ፍጠኑ፤ ንግድንም ተዉ። ይህ ብታውቁ ለእናንተ የተሻለ ነው።»
📖 (ሱረቱል ጁሙዓ፥ 62:9)
🤍 የጁምዓ ቀን የሳምንቱ ምርጥ ቀን፣ የምሕረት፣ የዱዓ እና የበረከት ቀን ነው።
ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ عَلَيْهِ الشَّمْسُ يَوْمُ الْجُمُعَةِ»
"ፀሐይ ከወጣችባቸው ቀናት ሁሉ ከሁሉ የበለጠው ቀን የጁምዓ ቀን ነው።" (ሙስሊም)
እንዲሁም ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«إِنَّ فِي الْجُمُعَةِ لَسَاعَةً لَا يُوَافِقُهَا عَبْدٌ مُسْلِمٌ وَهُوَ قَائِمٌ يُصَلِّي يَسْأَلُ اللَّهَ شَيْئًا إِلَّا أَعْطَاهُ إِيَّاهُ»
"በጁምዓ ቀን አንድ ሰዓት አለ፤ ሙስሊም ባሪያ በዚያ ሰዓት ሶላት ላይ ሆኖ አላህን የሚለምነውን ሁሉ አላህ ይሰጠዋል።" (ቡኻሪና ሙስሊም)
🌺 በዚህ ቀን የሚመከሩ ተግባራት
• ወደ ጁምዓ ሶላት ቀድመህ ሂድ።
• ሱረቱል ከህፍን አንብብ።
• በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋትን አብዛ።
• ዱዓህን አብዛ፤ የመቀበል ሰዓት አለባት።
• ቁርአንን አንብብ፣ ዚክርን አብዛ፣ ተውባን አድስ።
🍃 ኢብኑል ቀይም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦
"የጁምዓ ቀን ከሌሎች ቀናት ጋር ያለው ልዩነት፣ የረመዳን ወር ከሌሎች ወራት ጋር እንዳለው ልዩነት ነው።"
🤲 ዱዓ
اللهم اجعل لنا في هذا اليوم المبارك نصيبًا من رحمتك، ومغفرتك، ورضوانك، ووفقنا لذكرك وشكرك وحسن عبادتك، وأصلح قلوبنا، واختم لنا بخير، واجعل الفردوس الأعلى دارنا. آمين.
"አላህ ሆይ! በዚህ የተባረከ ቀን ከምሕረትህ፣ ከይቅርታህ እና ከውዴታህ ፈንታ አድርግልን። በዝክርህ፣ በምስጋናህ እና በመልካም ኢባዳህ ላይ አግዘን፤ ልቦቻችንን አስተካክል፣ መጨረሻችንን በመልካም አድርግልን፣ ፊርደውስንም መኖሪያችን አድርግልን። አሚን።
🌿 ጁምዓ ሙባረክ!
اللهم صل وسلم وبارك على نبينا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين.
إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ
“እውነተኛ ምእምናን እነዚያ ናቸው፤ አላህ በተወሳ ጊዜ ልባቸው የሚፈራ፣ የአላህ አንቀጾች በተነበቡላቸው ጊዜ እምነታቸው የሚጨምር፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩ ናቸው።”
https://t.me/boruselasa_22
https://t.me/boruselasa_22
☀️ቁርአንን በመልካም ባህሪሽ እና ምግባርሽ ላይ አሳያቸው !
በመልካም ንግግርሽ ፣በአርቆ አሳቢነትሽ፣ በእርጋታሽ፣ በጥቡቅነትሽ ፣በልብሽ ንጹህነት……… የምትታወቂ ሁኚ
"ቁርአንን የሃፈዘች" ብቻ ሳይሆን "የቁርአንን ያማሩ ባህሪያት የተላበሰች ምድር ላይ የምትንቀሳቀስ ቁርአን" የምትባይ ሁኚ
https://t.me/boruselasa_22
ሞትን ረስተን በዱኒያ ጭንቆች ለምንኳትን ሰዎች ስለ ዱንያ ሁኔታ አንዱ ገጣሚ እንዲህ ሲል ፃፈ
أَفِي دَارِ الخَرَابِ تَظَلُّ تَبْنِي؟
وَتَعْمُرُ مَا لِعُمْرِكَ فِيهِ فَنَاءُ؟
أَرَى بَصَراً وَقَلْباً فِي عَمىً
وَنَفساً مَا لَهَا أَبَداً رِوَاءُ
تُجَمِّعُ مَا يُبَدِّدُهُ المَنَايَا
وَتَبْنِي مَا يَهُمُّ بِهِ العَفَاءُ
وَتَنْسَى المَوْتَ يَا مِسْكِينُ جَهْلاً
وَفِي عَيْنَيْكَ لِلْمَوْتِ الرُّوَاءُ
أَفِي دَارِ الخَرَابِ تَظَلُّ تَبْنِي؟
وَتَعْمُرُ مَا لِعُمْرِكَ فِيهِ فَنَاءُ؟
◈ በሚጠፋ ዓለም ላይ (ቤት) ትገነባለህን? እድሜህ እያለቀ ባለበት ቦታ ላይስ ቤትን ታድሳለህን?
أَرَى بَصَراً وَقَلْباً فِي عَمىً
وَنَفساً مَا لَهَا أَبَداً رِوَاءُ
◈ አይንንና ልብን የታወሩ ሆኖ አያለሁ፤ ነፍስም እንዲሁ መቼም የማይረካ ጥም አላት።
تُجَمِّعُ مَا يُبَدِّدُهُ المَنَايَا
وَتَبْنِي مَا يَهُمُّ بِهِ العَفَاءُ
◈ ሞት የሚበትነውን ትሰበስባለህ፤ ጥፋት የሚገጥመውንም ትገነባለህ።
وَتَنْسَى المَوْتَ يَا مِسْكِينُ جَهْلاً
وَفِي عَيْنَيْكَ لِلْمَوْتِ الرُّوَاءُ
◈ አንተ ምስኪን! ባለማወቅ ሞትን ትረሳለህ፤ ሞት ግን በዓይኖችህ ፊት በግልጽ እየታየ ነው።
رحماك يا ربي
Repost from 🇸🇦"" ከጦሳ ማዶ ደሴ "" أبو الناموس الأثري 🇸🇦
👌 👉 #አስቸኳይ_መልዕክት :- በደሴ እና በአካባቢዋ ለምትገኙ ሰለፊዮች በሙሉ:- ነገ ዕሁድ የ الله ቤት በጋራ የምናቆምበትና የምናዋቅርበት ታላቅ የኸይር ስራ እድል ይጠብቀናል። የነገው እሁድ ቀናችንን ለመስጅዳችን ልንሰጥ ቀጠሮ ይዘናልና በደሴና በአካባቢዋ ያላችሁ ወንድሞች በቦታው ላይ በመገኘት መስጅዳችንን እናስውባት በማለት ጥሪ አቅርበንላችኋል !!
ቀን፦ ነገ እሁድ ማለትም ሃምሌ
ቦታ፦ በመስጅደል አቅሷ
የስራው አይነት፦ መስጅዳችንን በጋራ በመተባበር ግንባታ ማቆምና ማዋቀር
✨ #ማሳሰቢያ፦ “የነገውን ማንኛውንም የግል ስራችሁን በጊዜያዊነት ወደ ጎን በመተው” ሁላችሁም በነቂስ እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።#አንድም ሰለፊ ወንድም# እንዳይቀር!! የበኩላችንን አሻራ የምናስቀምጥበት ሰዓት አሁን ነው። 👌👉 #መልዕክቱን ለሌሎች ወንድሞች ሼር በማድረግ #የኸይር ስራው ተካፋይ ያድርጉ !! ------------------ #የመስጅደል አቅሷ ግንባታ #አስተባባሪ ወንድሞቻችሁ ------------------ 👌👉 https://t.me/AbuNibrase_and_Namuse
🔺...باخينا سلحدين حفظه لله تعلي
ነስር መስጅድ የእስታቃማን ነገር አደራ ይለናል......❗️
ግቡ
https://t.me/boruselasa_22?livestream
«لا حَوْلَ ولا قُوَّةَ إِلَّا بِاللهِ»
ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«لا حول ولا قوة إلا بالله كنز من كنوز الجنة»
"«ላ ሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ» ከጀነት ውድ ሀብቶች አንዱ ነው።"
⚠️ ከስኬት ፊት ከሚቆሙ እንቅፋቶች መካከል አንዱ ወንጀል ነው!
ኢማም ኢብኑል ቀይም رحمه الله እንደሚገልጹት፣ ነገሮች እንዳይሳኩልንና በስኬት መንገዳችን ላይ እንቅፋት ከሚሆኑ ነገሮች መካከል አንዱ ወንጀል ነው።
አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ለማሳካት ተነስቶ ብዙ ጊዜ ቢሞክርም ሳይሳካለት ሲቀር፣ ዑለሞች እንዲህ ይላሉ፦
"ምናልባት የተጣበቀበት፣ ያልተወው፣ ሱስ የሆነበት ኃጢአት ሊኖርበት ይችላል፤ እሱን ይተው።"
እስኪ ቁጭ ብለን በወንጀሎቻችን ምክንያት ያጣናቸውን ፀጋዎች፣ የተዘጉብንን የሪዝቅ በሮች፣ ያልተመለሱልንን ዱዓዎች እና የዘገዩብንን መልካም ነገሮች እናስብ።
አላህ ወንጀሎቻችንን ይማርልን፣ የተዘጉብንን የኸይር በሮች ይክፈትልን። አሚን።
Repost from 🇸🇦 የኪታብ ሪከርዶች ስብስብ 🇸🇦
🔥--- ጥያቄና መልሶቻቸው ---🔥
--------------------------------------
💥 ቁጥር 5️⃣5️⃣💥
🎙️ፈተዋ በሸይኽ አቡ ኒብራስ
✍️...ያአንደድ ሰዎችን ያለፈ ወንጀላቸውን ደጋግመን እናነነሳለን ግን አላህ እኮ ምሮላቸዋል ይሆናል አይ የኛ ነገር!!!
🔺👇🔺👇🔺👇🔺👇🔺👇
በህይወት ውስጥ ፈተና ሲበዛብህ አትዘን ታገስ...የጨረቃ ውበት የሚጨምረው ጨለማ በዙሪያዋ በጨመረ ቁጥር ነውና።
ራህማኑም " ታጋሾችን አበስራቸው " ይላል
👌 አብሽር !! ሀቢቢ 👌 👆👆👆👆👆👆👆👆 http://t.me/boruselasa_22 http://t.me/boruselasa_22
⭕️ የአላህ ውሳኔ ሁሌም ከእኛ ምርጫ ይበልጣል።
በሕይወታችን የምንፈልገውን ነገር ለማሳካት ያለንን አቅም ሁሉ አሟጠን እንታገላለን፤ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ነገሮች እንደ ፍላጎታችን አይሆኑም።
በዚያ ጊዜ ልባችን ቢሰበርም አንድ እውነት ግን መዘንጋት የለብንም፦
ያልሆነው ነገር መሆን ስላልነበረበት ነው፤ የሆነው ደግሞ መሆን ስለነበረበት ነው።
ምናልባት እኛ የጠየቅነው ቢሳካልን ኖሮ የሚጎዳን ወይም የሚያሳጣን ነገር ሊኖር ይችል ነበር። አላህ ግን ከእኛ በላይ ለእኛ የሚበጀውን ያውቃል።
ስለዚህ በጥረታችን አንዘናጋ፤ ውጤቱን ግን ለአላህ እንተው።
አንድ ነገር ሳይሳካ ሲቀር፦
"አልሐምዱሊላህ፤ ጌታዬ ሆይ፣ ለእኔ የተሻለውን አንተ ታውቃለህ።" እንበል።
🍃 ያልተሳካልን ነገር ሁሉ፣ አላህ ለእኛ ካዘጋጀው የተሻለ እቅድ አንዱ አካል መሆኑን አንዘንጋ።
