Mizan Tepi University MTU
Відкрити в Telegram
2 176
Підписники
+224 години
+137 днів
+1230 день
Архів дописів
ለ Exit Exam ስትመጡ ከተቻለ ነጠላ ጫማ እና ቀለል ያለ አለባበስ ለብሳቹ እንድትመጡ የጊቢው የፀጥታ አካላት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለፍተሻው ፍጥነት ነው
አስቸኳይ ማስታወቂያ
*******
ለሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተፈታኝ ዕጩዎች (ተማሪዎች) በሙሉ፤
የዘንድሮውን የፈተና ሲስተም ለመጠቀም ማንነትን ማረጋገጥ (Identity Verification) የግዴታ በመሆኑ፣ ማንነታቸውን ያላረጋገጡ ተፈታኞች የተጠቃሚ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) ማግኘት የማይችሉ መሆኑንና በዚህም ምክንያት ፈተናውን መውሰድ የማይቻል መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን።
ስለሆነም፣ ተፈታኞች በሙሉ አስቀድማችሁ የብሔራዊ መታወቂያችሁን (National ID) በመጠቀም ማንነታችሁን እንድታረጋግጡ በጥብቅ እናሳስባለን።
⚠️ ማሳሰቢያ፦ ይህንን ሳያደርጉ በመቅረታቸው ምክንያት ለሚፈጠር ለማንኛውም ዓይነት ችግር ወይም የፈተና መታለፍ ዩኒቨርሲቲው ምንም ዓይነት ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናስታውቃለን።
በተያያዥም፣ ማንነታችሁን ያረጋገጣችሁ ተማሪዎች የተጠቃሚ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
+9
በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለ2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች በኦላይን ፈተና መሰጠት ተጀመረ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚቴዩ ፣ግንቦት 27/2018 ዓ/ም
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዋናው እና ቴፒ ግቢ ለሚገኙ 2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች በኦላይን ፈተና በይፋ መሰጠት መጀመሩ ተገለጸ።
ፈተናው በሰላማዊና በተደራጀ ሁኔታ እንዲካሄድ አስፈላጊ ዝግጅቶች ሲደረግ መቆየቱም የተገለጸ ሲሆን ፈተናውን በተገቢው ደረጃ ለማስፈፀም የመፈተኛ አዳራሾችን ከማዘጋጀት ጀምሮ በርካታ ስራዎች ለፈተናው ስኬታማነት ስለመሰራቱም ተገልጿል።
ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ እንዲሰሩ ያሳሰቡት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ የፈተናውን ሂደት ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት ለተፈታኝ ተማሪዎች ስኬትን በመመኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።
መልካም ዕድል ለሁሉም የ2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች!
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ
Mizan-Tepi University
Arsenal 💪💪💪...............................................1:00 ፒኤስጂ ከ አርሰናል
ሰኞ ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው።
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ቦርዱ፦
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።
- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ እንዲያከነውኑ ፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት እንደማያስገድድ አሳውቋል።
- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ አረበታቷል።
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ ለእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ክቡር ዶ/ር ዋቆ ገዳ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆኑ መምህራን ፣ አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን በዓሉ የሰላም የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንም ተመኝተዋል።
መልካም በዓል !
ዋቆ ገዳ (ዶ/ር)
ፕሬዚዳንት
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-አድሐ (ዐረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን፡፡
የአርሰናል ደጋፊ የሆነው ውብ ጨዋታቸው ማርኮን እንጂ መቼም ዋንጫ ሲበላ አይተን አልነበረም !
እርሶን የአረሰናል ደጋፊ እነዲሆኑ ያደረጎት ተጨዋች ማን ነበር? let us Know in the Comments 👇
+2
👍የለውጥ ጉዞ እንደቀጠለ ነው!!!👍
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ አመራር ብዙ ለውጦችን እያሳየ መሆኑ ይታወቃል። ለአብነት ያክል በጭቃ ስንሰቃይ የነበረውን መንገድ አስፓልት ተሰርቶ ሳንሳቀቅ ግቢ ውስጥ መንቀሳቀስ ችለናል፣ የመመገቢያ አዳራሻችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተሰርተው በጽዱ አዳራሽ መመገብ ችለናል።
አሁን ደግሞ ፕሬዚዳንታችን ዶክተር ዋቆ ገዳ ባለፈው አመት ለተማሪዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት አዳዲስና ዘመናዊ ወንበሮች ገብተው ካፈው አሸብርቋል።
በሌላ በኩልም የምግብ ሁኔታን ሙሉ በሙሉ ለማሻሻል የእንጀራ ምጣድ እና ሌሎች ማሽኖች ዝርጋታ ተጠናቋል። በቀጣይ ሁሉንም ተማሪ የDigital library ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።
ለፕሬዚዳንታችን ዶ/ር ዋቆ ገዳና ማኔጅመንቱ ዩንቨርሲትያችንን ለተማሪዎች ምቹ ለማድረግ እየሰሩ ሲላሉት ነገር ሁሉ እጅግ አድርገን እናመሰግናለን። 🙏🙏🙏🙏
+4
ሚዛን አማን : የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች
በዛሬው ዕለት አካባቢ የማፅዳት መርሃ ግብር አካሄዱ
በሚዛን አማን ከተማ የሚኖሩ የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች የአካባቢያቸውን መልክ ለመቀየርና ማህበረሰባቸውን ለማገልገል በማሰብ የፅዳት ዘመቻ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
Repost from Mizan Tepi University Students Union Channel
ለመላው የጊቢያች የሀያሉ ክለብ አርሰናል ደጋፊዎች በሙሉ
ዛሬ ማለትም በቀን 16/9/2018 ታላቅ ድግስ አዘጋጅተናል
ስለሆነም መላው የአርሰናል ደጋፊዎች 4:00 ሰዓት ላይ እስታድየም አከባቢ የሙሽራውን ልብስ በመልበስ ሰርጋችንን በደማቅ ሁኔታ እናከብራለን
ዛሬ የሚዜነት ጊዜ አብቅቶ ንጉሱ ሚሞሸርበት ቀን ነው
ዛሬ የአርሰናል ሀያልነት የደጋፊው ፅናት ፍሬ ሚያፈራበት ቀን ነው
ስለዚ ሁላቹም የኑጉሱ ክለብ ደጋፊዎች መቅረት የተከለከለ ነው
አርስናል አርሰናል አርስናል🏆🏆🏆🏆🏆🔴🔴⚪️⚪️
🔔 ያረጋግጡ!
የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባቹ በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
ተከታዩን ሊንክ (https://verify.ethernet.edu.et/) ከተጫኑ በኋላ Remedial Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Start Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።
የሪሚዲያል ፈተና ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።
የትራንስፖርት ምዝገባ ቀን 14-15/9/2018 ብቻ
አዲስ አበባ........2600
1. ድሪባ
2. ማረኝ
ወሎ........3650
1.ኤርሚያስ
2.ሬድዋን
ሀዋሳ .......3350
1 ሙሴ ጋስ
2, አሻግሬ መሰረት
ወላይታ ......3550
1,አበባው
2, ሳኦል ሲኖር
ባህር ዳር .....4150, ደብረማርቆስ .... 3400
1 ,ፋሩክ
2, መንግስቱ ካጫ
3, ውብነህ
ማሳሰቢያ
የምዝገባ ቀን ዛሬ እና ነገ ብቻ
ምዝገባ በcash የምናስተናግድ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት
የጀግና መሪያችን ዶ/ር ዋቆ ገዳ ተማሪ በመሆኔ ሁሌ ኩራት ይሰማኛል።
እናንተስ👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/100087238861353/posts/965053869745900/?app=fbl
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
