uk
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Відкрити в Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Показати більше
4 480
Підписники
-124 години
+147 днів
+3130 днів
Архів дописів
ከላይ የሚታዩት ትምህርት ሚኒስቴር አስተያየት ይሰጥበት ዘንድ ባስቀመጠው የስነ-ስርዓት ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ የተሰጡ ቅሬታዎች ናቸው:: ረቂቅ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎች ሰብዓዊ መብት ይጥሳልና ሁላች
+8
ከላይ የሚታዩት ትምህርት ሚኒስቴር አስተያየት ይሰጥበት ዘንድ ባስቀመጠው የስነ-ስርዓት ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ የተሰጡ ቅሬታዎች ናቸው:: ረቂቅ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎች ሰብዓዊ መብት ይጥሳልና ሁላችንም መመሪያውን አንብበን ሐሳባችንን በተቀመጠው ፎርም ላይ እናስፍር:: ፎርሙ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse ነው:: የላካችሁትን አስተያየት Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ:: ይህ ለዚህ ትግል ልናደርገው የምንችለው ትንሹ አስተዋፅዖ ነው:: በአላህ ፈቃድ በትብብር በቅንጅት በምናደርገው እንቅስቃሴ የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ከዚህ ትውልድ አያልፉም::

"አንዳንዶች ሂጃብና ኒቃብን ለመለየት ይሞክራሉ፤ ሂጃብና ኒቃብን የመለየት መብቱ የላቸውም፡ ማን ፈቀደላቸው.? ይሄ ጣልቃ ገብነት ነው። ሂጃብ ማለት ሁለመናን የሚሸፍን ማለት ነው። ያየድሮው ጭቆና መልኩን ቀይሮ ተመልሶ መቷል። በአንድ ሴክተር ግላዊ ግፍና ጭቆናን በፍጹም የማንቀበል መሆኑን ሊታወቅ ይገባል። ትምህርት ሚኒስቴር በገዛ ትምህርት ቤታችን፣ በገዛ ቤታችን የገነባነውን የግል አመለካከቱን ሊያንጸባርቅበት አይገባም።አንቀበልምም።" - ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ https://t.me/EHEMSU

ይህ ትምህርት ሚኒስቴር አስተያየት ስጡበት ብሎ ላወጣው የስነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ የተሰጠ አስተያየት ነው:: ሁላችንም አስተያየት ስንሰጥ ስነ-ስርዓት ባለው መልኩ የትኩረት አቅጣጫዎቻችንን በሚዳስስ
+3
ይህ ትምህርት ሚኒስቴር አስተያየት ስጡበት ብሎ ላወጣው የስነ-ምግባር ረቂቅ መመሪያ የተሰጠ አስተያየት ነው:: ሁላችንም አስተያየት ስንሰጥ ስነ-ስርዓት ባለው መልኩ የትኩረት አቅጣጫዎቻችንን በሚዳስስ መልኩ መሆን አለበት:: እነርሱም:- 1ኛ:- መመሪያው አንቀፅ 7(5) ላይ በጥቅሉ ሐይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን እና ተግባራትን መፈፀም መከልከሉን መግለፁ ለብዙ ጥሰቶች በር እንደሚከፍት በመጥቀስ ሊከበሩ ለሚገባቸው ሐይማኖታዊ መብቶች እውቅና በመስጠት ሊሻሻል እንደሚገባው መጥቀስ:: ለምሳሌ ሶላት ለመስገድ: ኒቃብ ለመልበስ እና ለመሠል ሐይማኖታዊ መብቶች ማለት ነው 2ኛ:- ሶላት ሲሰገድ እና ኒቃብ ሲለበስ ተደጋጋሚ የመብት ጥሰቶች እያጋጠሙ ስለሆነ በዚህ ረገድ የመብት ጥሰት የሚፈፅሙ የት/ቤቶች አመራሮችም ሆኑ ሰራተኞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ የሚገልፅ እና ለጥፋቱ የሚቀመጠውን ቅጣት መጠንም የሚገልፅ ድንጋጌ እንዲቀመጥ ማለት ነው:: በተቻለ መጠን ሐሳቦቻችንን በራሳችን አገላለፅ ለማስቀመጥ እንሞክር:: ድግግሞሽ እና የሐሳብ መመሳሰል እንዳይኖር ማለት ነው:: ላልሰሙት ላልደረሳቸውም እናድርስ:: የሐሳብ መስጫ ፎርሙ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse ነው:: የላካችሁትን አስተያየት Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ:: @MohammadamminKassaw

3. የትግራይ ክልል ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የእምነት አለባበስ ጉዳይ በተመለከተ፦ በትግራይ ክልል ያሉ ሴት ተማሪዎች በፌደራሉም ሆነ በክልሉ ህገ መንግስት እንዲሁም በሌሎች የአገሪቱ ህጎች የተፈቀደላቸውን የእምነት አለባበስ ለብሰው የመማር መብታቸው ተጥሶ ላለፉት 2 ዓመታት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የትምህርት ሚኒስተር ተማሪዎቹ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ምንም አይነት ጥረት አላደረገም፡፡ ይልቁንም የክልሉ መጅሊስ የተማሪዎቹ ህገ መንግስታዊ መብታቸው ለማስከበር በፍ/ቤት ክስ አቅርበው ጉዳዩ እስከ ክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረስ ደርሶ ፍርድ ቤቶቹ የተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው የመማር መብት እንዳላቸው ውሳኔ ቢሰጡም የክልሉ መንግስት የፍ/ቤት ውሳኔ ለመፈጸም አሻፈረኝ ብሎ ተማሪዎቹ እስካሁን ወደ ትምህርታቸው አልተመለሱም፡፡ በመሆኑም የክልሉ መንግስት በፍ/ቤቶቹ ውሳኔ መሰረት ሙስሊም ተማሪዎች ሀይማኖታቸው ግዴታ ያደረገባቸው ሂጃብ ለብሰው እንዲማሩ እንዲያደርግና የፍርድ ቤቶቹ ውሳኔ እንዲፈጽም እየጠየቅን የትምህርት ሚኒስተርም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ በመግባት ተማሪዎቹ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ እንዲያደርግና በህግ የተጣለበትን ሀላፊነት እንዲወጣ እናሳስባለን፡፡ በአጠቃላይ ከላይ የጠቀስናቸው የሙስሊም ተማሪዎች አሳሳቢ ጉዳይ እንደ መንግስት በዋናነት የትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ከችግሩ እንዲላቀቅ እና ችግሩን ከስሩ እንዲፈታው እየጠየቅን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው በመሆኑ በህግ የተጣለበትን ሀላፊነት እንዲወጣ እናሳስባለን፡፡ ሌሎች የሚመለከታችሁ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ጉዳዩ የሚመለከታችሁ በመሆኑ በዚሁ አጋጣሚ ጉዳዩ በልዩ ትኩረት እንድታዩት እና የሰላም መደፍረስ እንዳያስከትል እናሳውቃለን፡፡ በመጨረሻም እንደ ኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤቱ ጉዳዮቹን በቅርበት እየተከታተልናቸው የምንገኝ ሲሆን ከላይ የተጠቀሱት ችግሮችን ጨምሮ ሌሎች ህዝበ ሙስሊሙ የሚመለከቱ ችግሮች ከስር መሰረታቸው ለመፍታት እና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ይረዳ ዘንድ በዛሬው ዕለት ከተለያዩ ባለድርሻ ማለትም ከኡለማ፣ ከህግ ሙሁራን፣ ከማህበረስብ፣ ከሴቶችና ከወጣቶች እና ከሚዲያ ባለሙያዎች የተውጣጣ ከሚቴ በማዋቀር ወደ ስራ እንዲገባ ያደረግን መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ ቀን ህዳር 09 2018 ​አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ በአዳማ ከተማ በተካሄደው አገራዊ የትምህርት ጉባኤ ላይ በሂጃብም ሆነ በሰላት ጉዳይ ከመጅሊስ ሀላፊዎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል በሚል ያስተላለፉት ንግግር ከእውነት የራቀ ነዉ! ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህ ሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በጠቅላይ ም/ቤቱ ማቋቋሚ አዋጅ ቁጥር 1207/2012 እና በህገ መጅሊስ 2015 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ማንኛውም የመንግስት አካል የሚወስናቸው ውሳኔዎች እና የሚፈጽማቸው ተግባራት የህዝበ ሙስሊሙን ሀይማኖታዊ መብት የሚጋፉ/የሚጣረሱ መሆናቸው ሲያረጋግጥ እርምት/ማስተካከያ እንዲደረግ የማድረግ ሙሉ ሀላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ በዚሁ መሰረት የብዝሀ ሃይማኖት ባለቤት የሆነችው አገራችን ኢትዮጵያ በልዩነት ውስጥ ያለ መከባበርና መደጋገፍ ተምሳሌት እንደሆነችና ይህም ልዩ ውበቷ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እንደ መንግስትም ይህንን እሴት በመጠበቅና የህዝበ ሙስሊሙ ለረዥም ግዜ ሲጠይቃቸውና ሲታገልላቸው የነበሩ ጥያቄዎች እየተመለሱ መሆኑ እናምናለን፡፡ ቀሪ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉና እነዚህም በአላህ ፈቃድ ወደ ፊት እንደሚመለሱ ተስፋም እናደርጋለን፡፡ በተጨማሪም በመንግስት በኩል ከመቼውም ግዜ በላቀ ሁኔታ ከህዝበ ሙስሊሙ መሪ ተቋም ጋር ተግባብቶና ተናቦ አመርቂ ስራዎች እየሰራን እንገኛለን ለዚህም ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስተራችን ዶ/ር አብይ አህመድ እና ለመንግስታቸው እንደተለመደው ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ግዜያት በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የሚወሰኑ ውሳኔዎች፣ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና እየተወሰዱ ያሉ አቋሞች የህዝበ ሙስሊሙ መብት በእጅጉ የሚጋፉ ሆኖ አግንተናቸዋል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች ከግዜ ግዜ ይሻሻላሉ፣ ከመሪ ተቋሙም ጋር በውይይት ይፈታሉ በሚል በትዕግስት ብንጠባበቅም በተለያዩ ግዜያት በክቡር የትምህርት ሚኒስተሩ በኩል እየተወሰዱ ያሉ የተናጥል እርምጃዎችና የተያዙ አቋሞች የህዝበ ሙስሊሙን መብት በእጅጉ የሚጥሱ እና በተጨባጭ ከኢ.ፌ.ድ.ሪ መንግስት አቋም የተለየ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ እነዚህም፦ 1. የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የእምነት አለባበስ (ሂጃብ) ለብሶ የመማር መብት በተመለከተ፦ ከኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ መንግስት ጀምሮ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የተለያዩ ህጎች ብንመለከት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሀይማኖታቸው ግዴታ ያደረገባቸው ልብስ ለብሰው ትምህርት እንዳይማሩ የሚከለክል ህግ የለም፡፡ ቢኖር እንኳን በህግ መንግስቱ አንቀጽ 27 የተደነገገው የሀይማኖት፣ የእምነትና የአመለካከት ነጻነት መብት ጋር የሚጋጭ በመሆኑ እና የህገ መንግስቱ አንቀጽ 9(1) መሰረት የማንኛውም የመንግስት አካል/ባለስልጣን ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚጋጭ ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም ይላል በመሆኑም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሀይማኖታቸው ግዴታ ያደረገባቸው ልብስ ለብሰው መማር አይችሉም የሚል የባለስልጣን የግል ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር በቀጥታ የሚጣረስ በመሆኑ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም፡፡ ነገር ግን ህገ መንግስቱ በዚህ ልክ ግልጽ ሆኖ እያለ የትምህርት ሚኒስቴር እንደ ተቋም እና ሚኒስተሩ በተለያየ ግዜ በሚያደርጓቸው ንግግሮች እና በሚሰጧቸው ማብራሪያዎች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሀይማኖታቸው ግዴታ ያደረገባቸው ሂጃብ የተሳሳተ ትርጉም ሲሰጡ እና ለብሰው መማር አይችሉም የሚል አንድምታ ያለው ንግግር ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡ ይህ ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ህዝበ ሙስሊሙ እና የህዝበ ሙስሊሙ መሪ ተቋም እያሳዘነ ያለ ጉዳይ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስተር ወቅቱ በሚመጥኑ በተለያዩ የትምህርት ጥራት ሊያመጡ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር በሚጠበቅበት በዚህ ወሳኝ ወቅት በየግዜው የሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ጉዳይ ለምን አጀንዳ እንዲሆን እንደፈለገ እና የተፈለገው ውጤት ምን እንደሆነ መገመት አይሳነንም፡፡ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሌላውን መብት ሳይነኩ እና በትምህርት ቤት ውስጥ ሊከሰቱ የሚችሉ የቅድመ ጥንቃቄ የደህንነት ጉዳዮች በሌሎች አማራጮች መከላከል እየተቻለ ሀይማኖታቸው ግዴታ ያደረገባቸው ልብስ ለብሰው እንዳይማሩ መከልከሉ ህጋዊ ያልሆነ እና በምንም አመክንዮ ተቀባይነት ያለው አይደለም፡፡ በዚህ ረገድ ሚኒስተሩ ጨምሮ አንዳንድ አካላት የኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 11 እና አንቀጽ 90(2) የሚረዱበት መንገድ ከድንጋጌዎቹ አውድ ውጪ እና ከህገ መንግስቱ አጽዳቂ ጉባኤ አባላት ሃሳብና ፍላጎት ውጪ በመሆኑ ተቀባይነት ያለው አይደለም፡፡ በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ በተመለከተ እየወሰደው ያለው እርምጃ እና የያዘው አቋም ከህዝበ ሙስሊሙ መሪ ተቋም ውይይት ያልተደረገበትና መግባባት ላይ ያልተደረሰበት በመሆኑ በኛ በኩል አጥብቀን እንቃወመዋለን፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ በ02/03/2018 በአዳማ ከተማ በተካሄደው አገራዊ የትምህርት ጉባኤ ላይ በሂጃብም ሆነ በሰላት ጉዳይ ከመጅሊስ ሀላፊዎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል በሚል ያስተላለፉት ንግግር ከእውነት የራቀ እና እንደ መጅሊስ ከሚኒስተሩ ጋር የተግባባንበት ምንም አይነት ነገር እንደሌለ እየገለጽን በሚኒስተሩ በኩል ተቋማችን በሚመለከት ለተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ በግልጽ ማስተካከያ እንዲደረግ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ 2. በአማራ ክልል ሙስሊም ተማሪዎች ግዕዝ በግዳጅ እንዲማሩ በትምህርት ቢሮው በኩል የተወሰነው ውሳኔ በተመለከተ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ሁሉም የ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከወላጆች እና ከህዝበ ሙስሊሙ መሪ ተቋም መጅሊስ ጋር ውይይት ሳይደረግበት ሙስሊም ተማሪዎች ያለፍላጎታቸው በግዳጅ ግዕዝ እንዲማሩ የወሰነው ውሳኔ መላው የክልሉ ህዝበ ሙስሊም እና በተለያየ እርከን ያሉ የክልሉ መጅሊስ ተቃውመውታል፡፡ ስለሆነም እንደ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትም የክልሉ ህዝበ ሙስሊም እና መሪ ተቋሙ ያልተቀበለው፣ ምክክር ያልተደረገበት እና ህጻናትን በግዳጅ ለማስተማር ሊያደርግ የሚችል የህግ መሰረት በሌለበት ግዕዝን በግዳጅ ለማስተማር ያሳለፈው ውሳኔ ክልሉ ያለበትን ውስብስብ ችግር በበለጠ የሚያባብስ እና ውጤቱም እጅግ በጣም አደገኛ ሊሆን የሚችል በመሆኑ እንደ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትም ውሳኔው የምንቃወመው ሲሆን የክልሉ ት/ቢሮም ውሳኔው በድጋሚ እንዲያጤነው እና የእርምት እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡ የክልሉ ት/ቢሮ ውሳኔ ከአገራዊ የትምህርት ፖሊሲው እና ከአጠቃላይ የትምህርት አዋጅ ቁጥር 1368/2016 አንቀጽ 28 እና አንቀጽ 29 ጋር የሚጋጭ በመሆኑ እና ይህንን የማስቆም ሙሉ ሀላፊነትና ጉዳዩም በቀጥታ የሚመለከተው የትምህርት ሚኒስተር በመሆኑና ትምህርት ሚኒስተር በጉዳዩ ላይ ጣልቃ በመግባት ጉዳዩ እንዲያስቆመውና በህግ የተጣለበትን ሀላፊነት እንዲወጣ እናሳስባለን፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለው ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ የማራቅ ዘመቻ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል 📎 የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ -ሀሩን ሚዲያ፥ ሕዳር
በትምህርት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለው ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ የማራቅ ዘመቻ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል 📎 የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ -ሀሩን ሚዲያ፥ ሕዳር 9/2018 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በትምህርት ሚኒስትር በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለው ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት የማራቅ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም ጠይቋል፡፡ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባበሳቸው ምክንያት በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለው በደል የሀገራችንን ተካባብሮ የመኖር እሴት የመናድ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ አክለውም ሂጃብም ሆነ ኒቃብ የሙስሊም ሴቶች መግለጫ መሆኑን በማንሳት አንዱን ፈቅዶ አንዱን መከልከል እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ ሀገር ወዳድ የሆነው ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በትምህርት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ ጊዜ እየተፈፀመ ያለውን በደል በትግስት ማሰለፉን አንስተው የሚመለከተው የመንግስት አካላት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ 17 አባላት ያሉት ኮሚቴ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተፈፀመ ያለውን በደል እንዲያጠራ መቋቋሙንም ገልፀዋል፡፡ - ሀሩን ሚዲያ የጠቅላይ ምክር ቤቱን ሙሉ መግለጫ ከቆይታ በኋላ ምናደርስ ይሆናል፡፡ © ሀሩን ሚዲያ @MohammadamminKassaw

የትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ አስተያየት እንዲሰጥ የአስተያየት መስጫ ፎርም አዘጋጅቷል:: በምን መልኩ አስተያየት መስጠት አለብን በሚለው ላይ የምናሳውቅ ሆኖ እስከዚያው ግን የተለ
+1
የትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ አስተያየት እንዲሰጥ የአስተያየት መስጫ ፎርም አዘጋጅቷል:: በምን መልኩ አስተያየት መስጠት አለብን በሚለው ላይ የምናሳውቅ ሆኖ እስከዚያው ግን የተለቀቀውን ረቂቅ መመሪያ በማንበብ ጠብቁን:: ጥያቄ አለን ! ! !

ይሰራጭ ! ! ! ይህ የትምህርት ሚኒስቴር ለውይይት ያቀረበው አዲስ የስነ- ምግባር መመረያ ረቂቅ ነው ... ከኒቃብ እና ሒጃብ ጋር ተያይዞ ምንም ያነሳው ጉዳይ ባይኖርም መመሪያው በ7.5 ላይ ግን ማንኛውም የሐይማኖት አምልኮ ስርዓት በትምህርት ቤቶች ውስጥ መፈፀም ክልክል ነው ሲል ያስቀምጣል:: ይህ ማለት ከሶላት ጀምሮ ያሉትን ሊከለክል ማለት ነው:: በመመሪያው ላይ አስተያየት እንዲሰጥ ያስቀመጠ ስለሆነ ሁላችንም ተናበን ቅሬታችንን ማስቀመጥ አለብን:: ለአሁን ለሁሉም share ይደረግ ... እውቅናም ይፈጠር ... Let us be prepared ! ! ! @MohammadamminKassaw

ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርታችሁና ከሀይማኖታችሁ ምረጡ የሚለዉ ሴራ በአስቸኳይ እንዲቆም አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት ገለፀ፡፡ በትምህርት ሚ/ር ከፍተኛ ኃላፊዎች ወቅት እየተጠበቀ ሙ
ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርታችሁና ከሀይማኖታችሁ ምረጡ የሚለዉ ሴራ በአስቸኳይ እንዲቆም አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት ገለፀ፡፡ በትምህርት ሚ/ር ከፍተኛ ኃላፊዎች ወቅት እየተጠበቀ ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ለማፈናቀል የሚካሄደውን የባለስልጣናት ሰውር ሴራ በድር _ አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት አጥብቆ ያወግዛል ብሏል:: የመግለጫዉ ሙሉ ቃል እንደሚከተለዉ ቀርቧል:- ባለፉት አመታት በተለያዩ የሐገራችን ክፍሎች የፈተና ሰዓት እየተጠበቀ ሆን ተብሎ ሙስሊም ተማሪዎችን ከዩኒቨርስቲ ጭምር እንዲስተጓጎሉ ሲደረጉና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሆን ተብለው ከሙስሊም በዓላት ጋር በማገናኘት ከፍተኛ በደሎችን ሲፈፅም የቆየው ት/ሚ/ር አሁን ደግሞ ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ለማፈናቀል እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ ሕዳር 2 ቀን 2018 አዳማ ላይ የሁሉም ክልሎች የትምህርት ሀላፊዎች፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የሁሉም ዩኒቨርስቲ ዲኖች እና የትምህርት ጉዳይ የሚመለከታቸው ከፍተኛ ሀላፊዎች በተገኙበት በሴኩላር ሰም እስላማዊ አለባበሶች መከልከላቸውና ት/ቤቶች ይህን መመሪያ እንዲያሰከብሩ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ በድር ኢትዮጵያ መንግስት ከለውጡ ወዲህ ትምህርትን ለተመለከቱ ከፍተኛ ጥረቶች ያለውን አድናቆት እየገለፀ እነዚህ ሀገርን ከፍ የሚያደርጉና ችግሮቻችንን ሊፈቱ የሚችሉ ጅምር ስራዎች እንዳይደናቀፉ ስጋቱን እየገለፀ ይህ ድንበር ያለፈና ቀስበቀስ እያደገ የመጣ ሙስሊሞችን ከሀይማኖትህና ከትምህርትህ ምረጥ በማለት የማስገደድ ዘመቻ በድር ኢትዮጵያ አጥብቆ እያወገዘ ከዚህ የሚከተሉትን የአቋም መግለጫዎች አውጥቷል፡፡ 1ኛ/ በህዳር ሁለት የአዳማው ሀገራዊ የትምህርት ጉባኤ ላይ የትምህርት ሚ/ሩ ከመጅሊስ ሀላፊዎች ጋር ተነጋግሬ ተስማምተዋል ባሉት ጉዳይ መጅሊስ ማብራሪያ እንዲሰጥ 2ኛ/ሚኒስትሩ የተናገሩት ሀሰት ከሆነ መጅሊሱንና ሙሰሊሙን ለማጋጨት ሴራ ሊሆን ስለሚችል መጅሊስ ድርጊቱን በብርቱ እንዲያወግዝና በህግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ 3ኛ/መንግስት የተለያየ ስውር አላማ ያላቸው _ ከፍተኛ ባለስልጣናት ህዝብና መንግስትን ለመለያየትና ሁከት ለማስነሣት የሚያደርጉትን ጥረት በማጣራት የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ፡፡ 4ኛ/ ባለፉት ጊዜያት በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ሲባረሩና በትምህርት ሀላፊዎች ከፍተኛ መገፋት ሲፈፀምባቸው በተበታተነ ሁኔታ መጮሁ በደሉን እያከፋው በመምጣቱ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም እንዲቃወመው ጥሪ ያደርጋል። በድር ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት

We have a question! We do want an answer!! @MohammadamminKassaw
We have a question! We do want an answer!! @MohammadamminKassaw

የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች የዚህ ትውልድ አማና ናቸው ... በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ወደ ቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ እዳ መኖር የለበትም !!! https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU) በአአዩ የስነ-ስርዓት መመሪያ ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥሰው ድንጋጌ እንዲሻሻል ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ አስገባ
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU) በአአዩ የስነ-ስርዓት መመሪያ ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥሰው ድንጋጌ እንዲሻሻል ለሰላም ሚኒስቴር ደብዳቤ አስገባ ! •••••••••••••••••••••••••••• ህዳር 05 / 2018 ዓ.ል •••••••••••••••••••••••••••• ህብረቱ በዛሬው እለት ባስገባው ደብዳቤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተደረገ ያለውን የመብት ጥሰት አስመልክቶ ከዚህን በፊት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ደብዳቤ ማስገባቱን ጠቅሶ በዩኒቨርሲቲው እየተደረገ ያለው የመብት ጥሰት አሁንም መቀጠሉን አሳውቋል። የህብረቱ ተወካዮችም ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ከዩኒቨርሲቲው ሀላፊዎች ጋር ውይይት ለማድረግ ጥረት እንዳደረጉና የዩኒቨርሲቲው አካላትም ከተወካዮቹ ጋር በመወያየት መፍትሄ ለማምጣት ፍቃደኛ አለመሆናቸውን ጠቅሷል። ህብረቱም ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በጉዳዩ ላይ በቀጥታ ጣልቃ ገብቶ ለውይይት ፍቃደኛ ያልሆኑትን የዩኒቨርሲቲው አካላትን ከህበረቱ ተወካዮች ጋር ቀርበው እንዲወያዩ እና በሕገ-መንግስቱ የተረጋገጠውን የተማሪዎቹን የሀይማኖት ነፃነትን የሚሸረሽሩትን መመሪያዎችና ተግባራትን በዘላቂነት እንዲሻሻሉ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጫና እእንዲያደርግ በደብዳቤው ላይ አሳውቋል። @aaumsu

በትምህርት ተቋማት ውስጥ የኢስላማዊ አልባሳትን ለይተው በሚከለክሉ አካላት ላይ መንግስት ተገቢ የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
+4
በትምህርት ተቋማት ውስጥ የኢስላማዊ አልባሳትን ለይተው በሚከለክሉ አካላት ላይ መንግስት ተገቢ የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሕዳር 04/2018 ዓ.ል ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አርባ ምንጭ | አምስተኛው ሀገር አቀፍ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ "ሀይማኖቶች ለሰላም፣ ለአንድነትና ለአብሮነት" በሚል መሪ ሃሳብ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ግግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ጌታችን አላህ በቅዱስ ቃሉ "እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ የማተገብሩትን ለምን ታወራላችሁ" ማለቱን አስታውሰው ስለ ሰላም የተናገርነውን እና የሰማነውን ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም አክለውም የሀይማኖት አባቶች ለሠዎች ወደ ሰላም ጥሪ የምናደርገውን ያህል እራሳችን ተግባራዊ እናደርገዋለን ወይ ሲሉም ለተሳታፊዎቹ ጥያቄ አዘል ግግግር አድርገዋል። በትምህርት ተቋማት ውስጥ የኢስላማዊ አልባሳትን ለይተው በሚከለክሉ አካላት ላይ መንግስት ተገቢ የእርምት እርምጃ እንዲወስድ የጠየቁት ፕሬዝደንቱ በተለያዩ ምክንያቶች አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በውይይት መፍታት ይገባልም ብለዋል። በአምስተኛው የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የፌዴራልና የክልሉ መንግስታት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉበት ይገኛል። •••••••••••••••••••••••• የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት https://t.me/EHEMSU

‎"ምሑራን" ጉባኤ ተቀመጡ አሉ••• ‎ለምን ቢባል?! ‎"ሰው መሆኗን ሊያረጋግጡ። ‎ ‎ሆኖም ሳይስማሙ ተለያዩ! ‎ ‎• አንዳንዶቹ የአምላክ ስሕተት አሏት (ጌታችን ከሚናገሩት ሁሉ ጠራ)። ‎ ‎• አንዳንዶቹ በጅምር የቀረች ፍጥረት እንደሆነች አስቀመጡ (ስትቋጭ ወንድ ልትሆን መሆኑ ነው)። ‎ ‎• አንዳንዶቹ እንደማንኛውም ቁስ ከመጠቃቀሚያነት በዘለለ ምንም ሚና እንደሌላት ተናገሩ። ‎ ‎~ ~ ~ ~ ~ ‎ ‎ውዱ መልዕክተኛችን (ሰ.ዐ.ወ) መጡ። ‎ ‎ያ ማንበብና መጻፍ የማይችሉት ነቢይ! ‎ ‎ሴት ልጅ በቦታዋ ተቀመጠች። ‎ ‎ሰውነቷ ከአጠያያቂነትም አለፈና፤ የክቡርነትን ደረጃ ተጎናጸፈች። ‎ ‎"የአካሌ ክፋይ ነች፥ የሚያስከፋት ያስከፋኛል" ሲሉ የነፍሳችን ተወዳጅ ሰው (ሰ.ዐ.ወ) ስለርሷ ተናገሩ። ‎ ‎አማናቸው አደረጓት። ‎ ‎ጀነት በእግሮቿ ስር ተደረጉላት። ‎ ‎የጀነት መግቢያ ሰበብም ሆነች። ‎ ‎ፍጥረት እርሷን በመጠበቅ ላይ ኃላፊነት ተሰጠው። ‎ ‎~ ~ ~ ~ ~ ‎ ‎አላህ ሴትን ልጅ ካከበረበትና ከሚጠብቅበት ነገር አንዱና ዋነኛው ሒጃብ ነው። ‎ ‎በርሱ ውስጥ ክብሯን፣ ደህንነቷን፣ ማንነቷን... ለመጠበቅ ዋስትና አለበት። ‎ ‎ይህንን የተረዱ ብዙዎች የማይደፈረውን ሁሉ ደፍረው ጠብቀው አቆይተውታል። ‎ ‎የለበሱትና ዋጋውን የተረዱት፥ አቅልን በሚያስት በሽታ ውስጥ እንኳን ሆነው ስለመገፈፉ ተጨንቀውለታል። ‎ ‎በነርሱ ላይ ጠባቂ የተደረጉት ሌሎች፥ ስለተከበሩበት እህቶቻቸው ሲሉ ህይወታቸውን ከፍለው ህያው አድርገውታል። ‎ ‎በአጭሩ፦ ተከፍሎበታል። ‎ ‎~ ~ ~ ~ ~ ‎ ‎ዛሬም ከዚያ የተለየ ነገር አይኖርም። ‎ ‎እስከማይቆጠር ዘመን እንድትለብሰው የሚያደርግ ዋጋ የተከፈለበትን ኒቃቧን እንደቀልድ አናየውም። ‎ ‎ትለብሳለች። ‎ ‎ትማራለች። ‎ ‎ትሰራለች። ‎ ‎በቀደምቶቿ የከበረ መስዋዕትነት የነጻነት ዘውዷን እስከመጨረሻው እንደደፋች ትኖራለች። ‎ ‎ ‎#ስለኒቃቧ_የተከፈለውን_አንረሳም! ‎#ኒቃብ_የመስዋዕትነት_ሰንደቅ_ነው!! ‎#እንደለበሰች_መማሯን_ትቀጥላለች!!! https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU) እና የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (EHEMSU) ከኢትዮጵያ ሙስሊም የህግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር ተወያዩ! •••••••••••••••••••••••••••• ጥቅምት 22 / 2018 ዓ.ል •••••••••••••••••••••••••••• ህብረቶቹ በትላንትናው እለት ከኢትዮጵያ ሙስሊም የህግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በተሳካ ሁኔታ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱም በጠቅላላ በሀገራችን የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በሚደረጉ የህግ ጥሰቶች እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ በሚለብሱ በሙስሊም እህቶቻችን ላይ እየተደረገ ስላለው የመብት ጥሰት በህጋዊ አግባብ እንዴት መሄድ እንደሚቻልና  ለወደፊቱም ይህንና መሰል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በሚደረጉ የመብት ጥሰቶች ላይ እንዴት አብሮ መስራት እንደሚቻል ከማህበሩ ጋር ተወያይተዋል። በነዚህና መሰል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በሚደርሱ የመብት ጥሰቶችና እነዚህን መብቶች ለመገደብ በተቀመጡ ህጎች ላይ በሰፊው ከተወያዩ በኋላ ተቋማቱ ለወደፊቱ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ አብረው ለመስራት ተስማምተዋል። @aaumsu

የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተደረገ ስላለው የመብት ጥሰትን አስመልክቶ ለኢትዩጵያ ሙስሊም የህግ ባለሙያዎች ማህበር ደብዳቤ አስገባ። •
+1
የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተደረገ ስላለው የመብት ጥሰትን አስመልክቶ ለኢትዩጵያ ሙስሊም የህግ ባለሙያዎች ማህበር ደብዳቤ አስገባ። •••••••••••••••••••••••••••• በትላንትናው እለት የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ኒቃብ ለባሽ እህቶች ላይ አየተደረገ ያለውን የመብት ጥሰት አስመልክቶ እስከ አሁን ድረስ የሄደባቸውን ሂደቶች እና ከዚህ ጋር በተያያዘ ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ ህጋዊ ምክርና አስተያየት እንዲሰጥና ህብረቱ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ላለው የህግ ጥሰት በፍርድ አካላት ለማስጠየቅ የሚያግዘውን ጠንካራ የህግ ሰነድ በማዘጋጀት ላይ ህጋዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ለኢትዮጵያ ሙስሊም የህግ ባለሙያዎች ማህበር ደብዳቤ አሰገባ። ©️ aaumsu @MohammadamminKassaw

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከፌደራል መጅሊስ ኡለሞች ም/ቤት ለተማሪዎች ይሆን ዘንድ የተቀበለውን በአፍሪካ አካዳሚ የተዘጋጀ 105 የቁርዓን ተፍሲር ለአዲስ አበባ ዩ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከፌደራል መጅሊስ ኡለሞች ም/ቤት ለተማሪዎች ይሆን ዘንድ የተቀበለውን በአፍሪካ አካዳሚ የተዘጋጀ 105 የቁርዓን ተፍሲር ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አበርክቷል:: ይህ እንዲሳካ ያገዙትን ሁሉ በአላህ ስም እናመሠግናለን:: በአላህ ፈቃድ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች እንዲጠናከሩ እንሰራለን::

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ኒቃብን በሚለብሱ ተማሪዎች ላይ በሚፈጸሙ ተቋማዊ እገዳዎች ዙሪያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት የኡለማ ምክር ቤት ይፋዊ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ኒቃብን በሚለብሱ ተማሪዎች ላይ በሚፈጸሙ ተቋማዊ እገዳዎች ዙሪያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት የኡለማ ምክር ቤት ይፋዊ አቋሙን እንዲያሳውቅ ጠየቀ:: እንደሚታወቀው በተለያዩ የትምህርት ተቋማት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው አድልዎ የቀጠለ ሲሆን የትምህርት ተቋማቱ ለጭቆናቸው ከሚያቀርቡት ምክንያት መካከል ኒቃብን ሐይማኖታዊ አለባበስ አይደለም የሚለው ድፍረት የተሞላበት ሰበብ አንዱ ነው::

"የተማሪዎቻችንን ሐይማኖታዊ መብት ማክበር ስለሚገባን ጁምዓ ከጧት እስከ 5:30 ብቻ እንዲሁም ከሰዓት ከ7:30 ጀምሮ እንዲማሩ ይደረግ!" - AAU ጤና ሳይንስ ኮሌጅ AAU ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ክብር
"የተማሪዎቻችንን ሐይማኖታዊ መብት ማክበር ስለሚገባን ጁምዓ ከጧት እስከ 5:30 ብቻ እንዲሁም ከሰዓት ከ7:30 ጀምሮ እንዲማሩ ይደረግ!" - AAU ጤና ሳይንስ ኮሌጅ AAU ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ክብር ይገባዋል ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ ከሶላት ጋር በሚጋጭ መልኩ ፕሮግራም የሚያወጡ ዲፓርትመንቶች እንዲያስተካክሉ ደብዳቤ ፅፏል ደብዳቤው "የተማሪዎቻችንን ሐይማኖታዊ መብት ማክበር ስለሚገባን ጁምዓ ከጧት እስከ 5:30 ብቻ እንዲሁም ከሰዓት ከ7:30 ጀምሮ እንዲማሩ ይደረግ!" ይላል:: ይህ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተምሳሌት ይሁን ይህ ለሁሉም ትምህርት ቤቶች አርዓያ ይሁን ጁምዓ ቀን ትምህርት ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ ነው:: ይህ ደግሞ በአዋጅ የተደነገገ መብት እንጂ ሌላ አይደለም:: ተማሪዎች:- መብታችሁን ጠይቁ ት/ቤቶች:- የተማሪዎችን መብት አክብሩ @MohammadamminKassaw

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአአዩ የስነ-ስርዓት መመሪያ ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት የሚጥሰው ድንጋጌ እንዲሻሻል ጠየቀ ! •••••••••••••••••••••••••••• ጥቅምት 18 / 2018 ዓ.ል •••••••••••••••••••••••••••• ህብረቱ በዛሬው እለት ለዩኒቨርሲቲው ዲን ፅ/ቤት በፃፈው ደብዳቤ ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ል ባወጣው የስነ- ስርዓት መመሪያ አንቀፅ 6(6) ላይ "በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ፊትን ሙሉ ለሙሉ የሚሸፍኑ አለባበሶችን መልበስ የተከለከለ ነው!" በማለት የሙስሊም ተማሪዎቹን ሕገ- መንግስታዊ መብት የሚጥስ ድንጋጌ በማውጣት ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን አለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶችንም ጭምር እንደጣሰ ገልፇል:: ይህ ድንጋጌ ከወጣበት ጊዜ አንስቶም በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ ትንኮሳ እና የመብት ጥሰቶች እየደረሱ እንደሆነ ገልፇል።    ይህ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከደረሰበት ጊዜ አንስቶ በሰላማዊ መንገድ ለአመታት የጠየቀ መሆኑን በመግለፅም ዩኒቨርሲቲው በሳምንት ውስጥ በተማሪዎቹ የመብት ጥያቄ አመርቂ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቋል:: በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የወጣው መመሪያ ተሻሽሎም:-   • በአንቀፅ 6(6) ላይ የሰፈረው ድንጋጌ ኒቃብን መልበስ ሰብዓዊ መብት እንደሆነ በመግለፅ እንዲሻሻል • በዩኒቨርሲቲው የፀጥታ አካላት በነቃብ ለባሽ ተማሪዎች ላይ የሚያደርሱት ትንኮሳ እንዲቆም • በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የሚያደርሱ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች እና የደህንነት አካላት ተጠያቂ የሚሆኑበት አውድ እንዲካተት ጠይቋል። ይህ እንዲሳካ ከዩኒቨርሲቲው ጀምሮ መጅሊስ እና የሰላም ሚኒስቴር አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ የተጠየቀ ሲሆን ይህ ሳይሆን ቀርቶ የሙስሊም ተማሪዎች መብት መጣሱ የሚቀጥል ከሆነ ወደ ፍርድ ቤት ከማምራት ጀምሮ ሕጋዊ እና ሰላማዊ የሆኑ የመብት ጥየቃ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እንደሚገባ በደብዳቤው ላይ ተገልፇል።